ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ 1197.60 ሣንቲም የጡረታ አበል እንዲከፈላቸው ተወሰነ

የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ 1197.60 ሣንቲም የጡረታ አበል እንዲከፈላቸው ተወሰነ። የመጀመርያ የጡረታ አበላቸውን ትላንት ጥቅምት 17 ቀን 2003 ዓ.ም የተቀበሉት ዶክተር ነጋሶ በቀድሞ ፕሬዝዳንትነታቸው ሊያገኙ የሚገባቸውን ሕጋዊ ጥቅማ ጥቅም እስከ አሁን ማግኘት እንዳልቻሉ ለአዲስ ነገር ገልጸዋል። በተከበረላቸው የጡረታ ገንዘብ ላይ አስተያየታቸውን ለአዲስ ነገር የሰጡት ዶክተር ነጋሶ “በዚህ የኑሮ ውድነት እንዴት ተደርጎ ነው በ1197 [...]

Negaso_Gidada_Et_339025gm-a

የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ 1197.60 ሣንቲም የጡረታ አበል እንዲከፈላቸው ተወሰነ። የመጀመርያ የጡረታ አበላቸውን ትላንት ጥቅምት 17 ቀን 2003 ዓ.ም የተቀበሉት ዶክተር ነጋሶ በቀድሞ ፕሬዝዳንትነታቸው ሊያገኙ የሚገባቸውን ሕጋዊ ጥቅማ ጥቅም እስከ አሁን ማግኘት እንዳልቻሉ ለአዲስ ነገር ገልጸዋል።

በተከበረላቸው የጡረታ ገንዘብ ላይ አስተያየታቸውን ለአዲስ ነገር የሰጡት ዶክተር ነጋሶ “በዚህ የኑሮ ውድነት እንዴት ተደርጎ ነው በ1197 ብር ከስድሳ ሣንቲም የሚኖረው፤ ይህ አንድ በፕሬዝዳንትነት አገሩን ሲያገለግል የኖረ ሰውን ኹኔታ እና ፕሮቶኮል ታሳቢ ያደረገ አይደለም” ሲሉ ተናገረዋል።

ዶክተር ነጋሶ በተጨማሪ እንዳብራሩት የፓርላማ አባላት ጥቅማ ጥቅምን ለማስከበር በወጣው የዜጎች የጡረታ ሕግ መሠረት አምስት ዓመት ብቻ ያገለገሉበትን ስሌት ውስጥ በማስገባት እና የፓርላማ ቆይታቸውን የጡረታ ተመን መነሻ በማድረግ ከሚያገኙት ሦስት ሺሕ ብር ላይ ተሰልቶ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል። ይኹንና ላለፉት 18 ዓመታት በልዩ ልዩ መንግሥታዊ ሐላፊነቶች እና በፕሬዝዳንትነት ያበረከቱት አገልግሎት በሙሉ “የአገልግሎት ዘመን” በሚል በደረቁ እንደተቀመጠ እና መፍትሄ እንደላገኘም አብራርተዋል።

እንደ ዶክተር ነጋሶ አገላለጽ ከጡረታ ሕጉ አኳያ ሲታይ የማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ ምንም ያጠፋው ነገር የለም። በሕግ የተቀመጠለትን ነው ተፈጻሚ ያደረገው። ነገር ግን ከ1987 እስከ 19994 ዓ.ም ድረስ በፕሬዝዳንትነት፣ ከ1994 እስከ 1997 ዓ.ም ደግሞ በቀድሞ ፕሬዝዳንትነት ያገኙት የነበረውን ጥቅማ ትቅም እንዲያጡ የተደረጉት “በግልህ ወደ ምርጫ ለምን ገባህ” በሚል እንደኾነም ይናገራሉ። “በግልህ ምርጫ ውስጥ በመግባት ወገናዊ ኾነኻል በሚል ከሐምሌ 1997 ዓ/ም ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ጥቅማ ጥቅሞቼን ከልክለውኛል፤ በጡረታ አበሌም ላይ ታሳቢ እንዳይደረግ አድርገዋል” ይላሉ።

የማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ በበኩሉ ፕሬዝዳንቶች እና ጠቅላይ ሚኒስትሮች የሚያገኙት ደመወዝ ሳይኾን ጥቅማ ጥቅም በመኾኑ በሌላ መንገድ ሊታይ የሚገባው ጉዳይ እንጂ በጡረታ ሕጉ ታሳቢ ተደርጎ የሚሰላ አይደለም፤ ይህም በአዋጆች እና በመመርያዎች በግልጽ ተቀምጧል የሚል ምላሽ ሰጥቷቸዋል።

ሕጋዊ ጥቅማ ጥቅሞቼ ይከበሩል በማለት እስከ ሰበር ሰሚ ፍርድ ቤት በመሄድ ፍትህ ለማግኘት ጥረት ሲያደርጉ የነበሩት ዶክተር ነጋሶ በቀድሞ ፕሬዝዳንትነታቸው ያገኙት የነበረው የወር አበል እና የቤት ውስጥ ፍጆታ እስከ ዐሥር ሺሕ ብር ድረስ የሚደርስ በመኾኑ ጡረታቸውንም ሊሳድግላቸው ይችል እንደነበር መከራከርያ ያስቀምጣሉ።

ዶክተር  ነጋሶ በሠራተኛ እና ማኅበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ለአንድ ዓመት፣ በማስታወቂያ ሚኒስቴር ለአራት ዓመት (ከ1984 እስከ 1987)፣ በፕሬዝዳንትነት ለስድስት ዓመት (ከ1987 እስከ 1993)፣ በቀድሞ ፕሬዝዳንትነት ለአራት ዓመት (ከ1994 እስከ 1997) እና በግል  የፓርላማ አባል በመኾን ለአምስት ዓመታት (ከ1997 እስከ 2002) አገልግለዋል።

2 Responses to “ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ 1197.60 ሣንቲም የጡረታ አበል እንዲከፈላቸው ተወሰነ”

  1. በጣም የሚያሳዝን እና የሚገርም ነገር ነው! ሌላ ምንም ማለት አይቻልም::
    እርግጠኛ ነኝ አቶ ነጋሶ የተሻለ ነገ ይመጣላቸዋል:: መለስ ስልጣን ሲለቅቅ (ሲለቅቁ)ፕሮፌሰር ፧ የተባበሩት መንግስታት አማካሪ ምናምን ምናምን ይሆናል አይደለ ተረቱ :)

  2. i’m really disappointed withdr.negasos monthly penstion money.the leading party tplf andhis cadres(kangaro make with him ridiculous game).how ot could be tha one who lead ethiopian for 5years on presdent..they decide 1197.60 it is less than 50€ very embarrassing judgement….those who make this!!!
    may god keep ethiopian for those tyrant administration

ሸራተን ሆቴል ፊት ለፊት ሊደረግ የነበረው ሰላማዊ ምልጃ በመንግሥት የደኅንነት ሠራተኞች እና በፌዴራል ፖሊስ አባላት ተበተነ

እሁድ ጥቅምት 14 ቀን 2003 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከአካባቢያቸው በመፈናቀል ላይ ያሉት በሸራተን ዙርያ የሚገኙ እነዚሁ ነዋሪዎች ከሕጻን እስከ አረጋውያን በመኾን በቦታው ላይ የተገኙት መፈክሮችን ይዘው ነበር። የጠቅላይ ሚስትሩን ፎቶ እና ከሥሩ “እኛ የልማት አደናቃፊዎች ሳንኾን በልማት ላይ ያሉ የአፈጻጸም ችግሮች የፈጠሩብንን ኢ-ፍትኀዊነት ለማሳወቅ መንግሥትን አና ባለ ሀብቱን ሼሕ ሙሐመድ አላሙዲንን ለመለመን የወጣን ምስኪኖች ነን” የሚሉ መፈክሮችን ይዘዋል። እነዚሁኑ መፈክሮች የፌዴራል ፖሊሶቹ በስፍራው ላይ ደርሰው ነጥቀዋቸዋል።

(ሙሉ ገ)

ለሸራተን ሆቴል ማስፋፊያ ፕሮጀክት ከአካባቢያቸው የሚፈናቀሉ ከአምስት ሺሕ በላይ የሚኾኑ አባወራዎች ባለ ሀብቱን ሼህ ሑሴን  ሙሐመድ አላሙዲንን እና መንግሥትን በምትክ የካሳ ክፍያ ጉዳይ ላይ ኢ-ፍትኀዊ አሠራር እንዳይኖር ለመለመን ከሸራተን ሆቴል ፊት ለፊት በሚገኘው አነስተኛ ሜዳ ላይ ሊያደርጉት የነበረው ሰላማዊ ምልጃ በመንግሥት የደኅንነት ሠራተኞች እና በፌዴራል ፖሊስ አባላት አስገዳጅነት ተበተነ።

እሁድ ጥቅምት 14 ቀን 2003 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከአካባቢያቸው በመፈናቀል ላይ ያሉት በሸራተን ዙርያ የሚገኙ እነዚሁ ነዋሪዎች ከሕጻን እስከ አረጋውያን በመኾን በቦታው ላይ የተገኙት መፈክሮችን ይዘው ነበር። የጠቅላይ ሚስትሩን ፎቶ እና ከሥሩ “እኛ የልማት አደናቃፊዎች ሳንኾን በልማት ላይ ያሉ የአፈጻጸም ችግሮች የፈጠሩብንን ኢ-ፍትኀዊነት ለማሳወቅ መንግሥትን አና ባለ ሀብቱን ሼሕ ሙሐመድ አላሙዲንን ለመለመን የወጣን ምስኪኖች ነን” የሚሉ መፈክሮችን ይዘዋል። እነዚሁኑ መፈክሮች የፌዴራል ፖሊሶቹ በስፍራው ላይ ደርሰው ነጥቀዋቸዋል።

በሸራተን ሆቴል የ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ከአካባቢያቸው ከተፈናቀሉት አምስት ሺሕ በላይ አባወራዎች መካከል ስማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ አንድ አባወራ ይህን ሰላማዊ የኾነ የምልጃ ሰልፍ ለማድረግ የተነሳሱት ከዚህ ቀደም ከዚሁ ስፍራ ላይ የተነሱት አባዎራዎች የተሰጣቸውን የምትክ ቤት እና ተጨማሪ ጥቅማጥቅም ታሳቢ በማድረግ እንደኾነ ገልጸዋል። “የመጀመርያዎቹ ዙር ተፈናቃዮች ምትክ ቤት ተሠርቶላቸዋል፤ በቀበሌ ቤት ውስጥ ይኖሩ ለነበሩትም ተመጣጣኝ ቤት የተሠራላቸው ሲኾን የቤት ኪራዩም እንዲሁ ተመጣጣኝ ተደርጎላቸው ነበር። በእኛ እየተፈጸመ ያለው ግን መንግሥት ጉዳዩን እኔ አስፈጽማለኹ ብሎ መሬታችን በሊዝ ለባለ ሀብቱ በመሸጥ አውላላ ሜዳ ላይ እንደንውድቅ ማድረግ ነው። በዚሁ የመንግሥት ውሳኔ ተስፋ በመቁረጥ ከመካከላችን ያሉ አዛውንቶች ዕድሜያቸውን ሙሉ የለፉበትን ዕድርን የመሰለ የማኅበራዊ ተቋም ንብረት እስከመሸጥ ድረስ እንዲሄዱ ተደርገዋል” ይላሉ።

የአዲስ ነገር ሪፖርተር ከቦታው ኾኖ እንደታዘበው በደህንነት ሠራተኞቹ እና በፌዴራል ፖሊሶች ወከባ እና እንግልት የተበሳጩት የአካባቢው ነዋሪዎች እንደገና በሜዳው ላይ መሰባሰብ ጀምረው ነበር። ፖሊስ እንደገና ከተሰባበሰቡት መሀል ኅብረተሰቡን አነሳስተዋል ያላቸውን ዐሥራ አንድ አባወራዎች እና ሁለት እናቶችን በመኪና ጭኖ ወደ ፖሊስ ጣብያ ወስዷቸዋል። ይህን ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ታሳሪዎቹ እንዳልተፈቱ የፖሊስ ምንጮቻችንም ለአዲስ ነገር ገልጸዋል።

በሰላማዊ ምልጃው ላይ ሲሳተፉ ከነበሩት መካከል አንዱ የኾኑት አቶ መሳፍንት በቀለ (ስማቸውን ቀይረው ተናግረዋል) እንደገለጹት በቀበሌ እና በክፍለ ከተማ ያሉ ሐላፊዎች በግል ይዞታ የሚተዳደር ቤት ለነበራቸው ነዋሪዎች ከ 13 እስከ 18 ሺሕ ብር የሚገመት ገንዘብ ሰጥተዋቸዋል። “ይህ ታሳቢ ያደረገው ከከተማ ክልል ወጣ ብሎ ሚሰጠን የገበሬ ቦታ ላይ ቤት እንደንሠራ ነው። ነገር ግን ይህ ብር አይደለም ቤት ሊያሠራን ቀርቶ ለኮንደሚኒየሙ አነስተኛ ክፍል(ስቱዲዮ) የሚከፈለውን 56 ሺሕ ብር እንኳ የሚሸፍንልን አይደለም” ብለዋል።

መንግሥት ለችግሩ እውነተኛ እና ቀጥተኛ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ የልማት ተፈናቃዩን ኅብረተሰብ ባዶ ተስፋ በማስታቀፍ፣ በማታለል፣ በማጭበርብር እና በማሸማቀቅ ፖሊሲውን በግድ ተፈጻሚ እያደረገ ነው የሚሉት አቶ መሳፍንት ዛሬ ያደረግነው ሰላማዊ ሰልፍ ሳይኾን የደካሞች ምልጃ እና ልመና ስለኾነ ከአዲስ አበባ መስተዳደር ፈቃድ አልጠየቅንም። ስንጠይቅም አልተፈቀደም እንባላለን። በአንጻሩ ጥቂት የራሳቸው ሰዎችን እና ካድሬዎቻቸውን በመንግሥት ሚዲያ በማቅረብ በኹኔታው ደስተኛ የኾንን ለማስመሰል የአብዛኛውን ተፈናቃይ ምሬት እንዳልነበረና እና ምንም እንዳልተፈጠረ አድርገው ያቀርባሉ” ብለዋል።

3 Responses to “ሸራተን ሆቴል ፊት ለፊት ሊደረግ የነበረው ሰላማዊ ምልጃ በመንግሥት የደኅንነት ሠራተኞች እና በፌዴራል ፖሊስ አባላት ተበተነ”

  1. በጣም የሚያሳዝን እና የሚገርም ነገር ነው! ሌላ ምንም ማለት አይቻልም::
    እርግጠኛ ነኝ አቶ ነጋሶ የተሻለ ነገ ይመጣላቸዋል:: መለስ ስልጣን ሲለቅቅ (ሲለቅቁ)ፕሮፌሰር ፧ የተባበሩት መንግስታት አማካሪ ምናምን ምናምን ይሆናል አይደለ ተረቱ :)

  2. i’m really disappointed withdr.negasos monthly penstion money.the leading party tplf andhis cadres(kangaro make with him ridiculous game).how ot could be tha one who lead ethiopian for 5years on presdent..they decide 1197.60 it is less than 50€ very embarrassing judgement….those who make this!!!
    may god keep ethiopian for those tyrant administration

Leave a Reply

You must be to post a comment.

የአገር ቤት ጋዜጦች ምን ጻፉ?

ዶክተሩ ተተኪያቸውን አቶ ግርማ ወልደጊየርጊስን “በ92 ምርጫ በግል እንዲያሸንፉ ኦሕዴድ ነው ያመቻቸላቸው” ሲሉም አጋልጠዋል፡፡ “ኦሕዴድ የግል ተወዳዳሪዎችን ይጫናል እንዳይባል ለአንዳንድ የግል ተወዳዳሪዎች ይለቀቅላቸው ተብሎ ሪኮመንድ ስለተደረገ ለአቶ ግርማ ወልደጊዮርጊስ፣ ለአቶ በድሩ አደም ለቀቅንላቸው” ይላሉ ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ።

አቶ ምኅረት ደበበ ስለ መብራት መቋረጥ እየተናገሩ መብራት ሄደ

አርብ ዕለት ሜክሲኮ በሚገኘው የመብራት ኀይል አዳራሽ ጋዜጠኞችን ጋብዘው መግለጫ እየሰጡ ነበር፤ መልከ መልካሙ የመብራት ኀይል ሥራ አስፈጻሚ አቶ ምኅረት ደበበ፡፡ መብራት እየተቋረጠ ያለው በትራንስፎርመሮች እና በማስተላለፊያ ታወሮች አቅም ማነስ እንጂ ግድቦቻችን እስከ አፍንጫቸው ሙሉ ናቸው እያሉ ቀጠሉ አሉ አቶ ምህረት። “በዚህም የተነሳ ከፍተኛ ኀይል የሚፈልጉ ፋብሪካዎች ምሽት ከ12 እስከ አራት ሰዓት ኀይል እንዳይጠቀሙ ተነግሯቸዋል።” ያም ኾኖ “የኀይል እጥረት የለም” የሚሉት አቶ ምኅረት ኅብረተሰቡ መብራት ሲሄድ ደውሎ ይንገረን ሲሉ ተማጸኑ። ይህን እያሉ ታድያ ሦስት ጊዜ መብራት ሄደ፤ እዚያው። በመብራት ኀይል አዳራሽ።  በመብራት ኀይል ሥራ አስፈጻሚው ፊት። ሪፖርተር ነው ይህን ዜና ያስነበበው በቅዳሜው የእንግሊዝኛ ጋዜጣው።

የአስካሉካን እና የደቡብ አፍሪካ ሕልም በቅርቡ ይፈታል

አንድ ሺሕ ሁለት መቶ ከሳሾች እና አንድ ተከሳሽ የተፋጠጡበት የአስካሉካን የፍርድ ሂደት ለመጨረሻ ውሳኔ ሕዳር 10 ተቀጠረ፡፡ የአለም ዋንጫን እንድታዩ ወደ ደቡብ አፍሪካ እወስዳችኋለሁ በሚል በነፍስ ወከፍ 37 ሺሕ ብር በድምሩ 45 ሚሊዮን ብር ሰብስበው የተሰወሩት የአስካሉካን ትሬዲንግ ባለቤት እና ባለቤታቸው በተከሰሱበት የማታለል ወንጅል ላይ ጥፋተኛ ተብለው እንዲከላከሉ ተወስኖባቸው ነበር፡፡ አቶ ግርማይ እስካሁን በፖሊስ እየታደኑ ሲኾን ባለቤታቸው እና ሌሎች የድርጅቱ ተቀጣሪ ሠራተኞች በጠበቆቻቸው በኩል “ከደሙ ንፁሕ ነን” ሲሉ ተከራክረዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ “የግራ ቀኙን ሰምቻለሁ፤ ጥሩ ፍርድም እሰጥ ዘንድ ተጨማሪ ቀን እፈልጋለሁ፤ ሕዳር ዐሥር እንገናኝ” ሲል ወስኗል፡፡ ሰንደቅ ጋዜጣ እንደዘገበው፡፡

ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ ተርበዋል፣ ተጠምተዋል

ፍትሕ ጋዜጣ ሦስት ገጾቹን ለቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ ቃለ መጠይቅ አውሎታል፡፡ በዚህ ሰፊ ቃለ መጠይቅ ዶክተር ነጋሶ ያሳዝኑናል፡፡ “ኢሕአዴግ እስር ቤት ሳይከተኝ፣ በጥይት ሳይመታኝ ሊገድለኝ ነው” ይላሉ፡፡ ዶክተር ነጋሶ ቤታቸው በላያቸው ላይ እየፈረሰ እንደሆነ፣ አንድ ቀን ተንዶ ከእነ ቤተሰባቸው ሊገድላቸው እንደሚችል፤ ክረምቱን የተወጡት ጣርያውን በትልቅ ላስቲክ ሸፍነው እንደኾነ፣ ምንም ገቢ እንደሌላቸው፣ ልጃቸው በጽዳት ሥራ ተቀጥራ እንደሠራች፣ በታክሲ እንደሚሄዱ፣ ብዙዉን ጊዜ ሾፌሩ አልያም ተሳፋሪው የታክሲ እንደሚከፍልላቸው” እየነገሩን ሆዳችን ይባባል፡፡

ዶክተሩ ተተኪያቸውን አቶ ግርማ ወልደጊየርጊስን “በ92 ምርጫ በግል እንዲያሸንፉ ኦሕዴድ ነው ያመቻቸላቸው” ሲሉም አጋልጠዋል፡፡ “ኦሕዴድ የግል ተወዳዳሪዎችን ይጫናል እንዳይባል ለአንዳንድ የግል ተወዳዳሪዎች ይለቀቅላቸው ተብሎ ሪኮመንድ ስለተደረገ ለአቶ ግርማ ወልደጊዮርጊስ፣ ለአቶ በድሩ አደም ለቀቅንላቸው” ይላሉ ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ።

ጥያቄ፡- አንዳንድ ሰዎች ነጋሶ ከቤተ መንግሥት ወጡ እንጂ አሁንም የሚኖሩት ኑሮ የፕሬዝዳንት ያህል የተቀናጣ ነው ይላሉ። እውነት ነው?

ዶ/ር ነጋሶ፡- እነዚህ ሰዎች አገራቸውን አያውቁም ማለት ነው፡፡ እኔ አሁን ደሞዝ የለኝም፡፡ ጡረታም ቢኾን ገና አልተከበረልኝም፡፡ ለፕሬዝዳንቶች የሚደረገው ጥቅማ ጥቅም ቀርቶብኛል። …ፕሬዝዳንት ሳለኹ ከማገኘው ገንዘብ ላይ በአዋጁ መሠረት ጡረታ አልተቆረጠም። እናም ለዐሥር ዓመት ምግብ ለሥራ ነበር የማገለግለው…በአጠቃላይ ሲታይ ከ83 ጀምሮ እስከ 94 ድረስ ይህንን መንግሥት በነጻ ነው ያገለገልኩት ማለት ነው፡፡

ዶክተሩ አሁን በምን እንደሚተዳደሩ ሲጠየቁ “ባለቤቴ ናት የምታኖረኝ፣ በተጨማሪም ፓርላማው ሲበተን መቋቋሚያ ብለው 26ሺ ብር ሰጥተውናል፤ እሷን እየቆጠብኹ እየበላሁ ነው” ይላሉ፡፡

ጥያቄ፡- እርሶ ፕሬዝዳንት እያሉ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ሰው ላይ እንዲፈርሙ ከጠ/ሚኒስትሩ ጫና ይደረግብዎት ነበር?

ዶ/ር ነጋሶ፡- በዚህ ጉዳይ ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመጣ ነገር አልነበረም፡፡ የሚመጣ ነገር ከነበረም የአገር ሚስጥር ስለኾነ መናገር አልፈልግም፡፡

ይህን ጥያቄ ጋዜጠኛው እንዲመልሱለት ደግሞ ይጠይቃቸዋል፡፡ እንዲህ አሉት፡፡ “የለም፣ ተወው አልነገርህም፤ አንዳንድ ጉዳዮች አሉ ሥልጣን ብትለቅም ሚስጥርነታቸውን ጠብቀህ የምታቆያቸው፡፡”

ዶክተር ነጋሶ እርሳቸውንና የአሁኑን ፕሬዝዳንት ሲያነጻጽሩ እንዲህ አሉ፡- “እኔ ፕሬዝዳንት በነበርኩ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ወገንተኛ ነበርኩ፡፡ ምክንያቱም የኦሕዴድ እና የኢሕአዴግ አመራር አባል ነበርኩ፡፡ እኔ ከለቀቅኹ በኋላ ግን ፕሬዝዳንት ወገንተኛ መኾን የለበትም የሚል ሕግ ወጥቷል። …አቶ ግርማ ግን እንደምናየው ወገንተኛ ናቸው።”

የመለስን የፖለቲካ ብስለትና ስብእናን እንዲነግሩት ፍትሕ ጋዜጣ ዶክተሩን በጠየቃቸው ጊዜ “የሰው የግል ጉዳይ ላይ መግባት አልፈልግም።” ሲሉ መለሱለት፡፡ ጥያቄዉን አጥብቆ ጠየቃቸው፡፡ በመጨረሻም እንዲህ አሉ፡-“እሱን አንድ ቀን ቁጭ ብዬ በምጽፈው መጽሐፍ ላይ እገልጸዋለሁ።”

ተስፋዬ ገብረአብን በተመለከተ፡-“ሰውየው በግልጽ የመዋሸት ነገር አለበት። ሴት በመውደዱ ነው ያባረርነው ያልኩት ነገር የለም፡፡ ሴት አያያዙ ጥሩ አልነበረም ብዬም አላውቅም፡፡..አማረ አረጋዊ፣ መዝሙር ፈንቴ፣ ተስፋዬ ገብረአብ ግምገማ አድርገንባቸው የአቅም ችግር ስለነበረባቸው ነው የተነሱት ነው ያልኩት።” ሲሉ በጉዳዩ ላይ ረዘም ያለ ምላሽ ሰጥተዋል።

ዶክተር ነጋሶ በብርቱካን መፈታት ላይ በሰጡት አስተያየት፡- “ይኼ መንግሥት ልክ እንደመጥፎ አባት ነው። ልጆቹ ሳያጠፉ ከመሬት ተነስቶ እንደሚገርፋቸው። ልጆቹም ላላጠፉት ጥፋት ዱላው ሲበዛባቸው ይቅርታ አጥፍተናል ይሉታል።”

“…ሽማግሌዎቹ አቶ መለስ የሚፈልጉትን እና ደስ የሚላቸውን ነገር የሚያውቁ ነው የሚመስለኝ። የዚህን ዐይነት ደብዳቤ አዘጋጁ። እኔ እንደሚመስለኝ ደብዳቤውን ብርቱካን አልጻፈችውም፣ አቶ መለስም ጽፈው የሰጧቸው አይመስለኝም፣ ሽማግሌዎቹ ናቸው ጽፈው ያስፈረሟት፡፡ በዚህም በጣም ነው ያፈርኩት።”

ዶክተሩ ከፕሬዝዳንትነት ከወረዱ በኋላ ሕዝቡ የሚያሳያቸው ፍቅር ልባቸውን የነካው ይመስላል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ያሉትን ጠቅሰን ዶክተሩን እንሰናበት፡- “አንዳንዶቹ ያቅፉኝ እና እንወድኻለን ይሉኛል፤ አንዳንዶቹ ደግሞ እዚህች ግንባሬ ላይ መላጣዬን ይስሙኛል። በእውነት የኢትዮጵያ ሕዝብ ላሳየኝ አክብሮት እና ፍቅር አመሰግናለኹ።”

ኢሕአዴግ፤ ቻይና እና ሴኮቱሬ

በየሳምንቱ ረቡዕ የሚታተመው ሰንደቅ ጋዜጣ ከኢሕአዴግ የውጭ እና የአገር ውስጥ ግንኙነት መምሪያ ኀላፊ ከኾኑት አቶ ሴኮቱሬ ጌታቸው ጋራ ሰፊ ቃለ ምልልስ አድርጓል። ቃለ መጠይቁ ሙሉ በሙሉ በአንድ ጉዳይ ላይ ብቻ የተደረገ ነው። ኢሕአዴግ በቅርቡ ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ጋራ የመግባብያ ሰነድ በመፈረሙ ጉዳይ ዙርያ። አቶ ሴኮቱሬ እንዲህ ይላሉ፦ “ቻይና ባለፉት 30 ዓመታት ሕዝቧን ከድህነት ለማውጣት ያደረገቸው እንቅስቃሴ ብዙ ልምድ የሚወሰድበት ነው።…አገራችን የበለጸገች እና የታፈረች እንድትኾን ከቻይና የእድገት ጉዞ ብዙ የምንማረው ነገር አለ፡፡ …እነሱም ከኛ የሚማሩት ነገር አለ።”

አቶ ሴኮቱሬን በዚህ ቃለመጠይቃቸው ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ጋር መፈራረም አገራችን መድበለ ፓርቲን ትተዋለች ማለት እንዳልኾነ አብራርተዋል። “የታገልነው ለመድበለ ፓርቲ  ሥርዐት ነው፡፡ ይህ የማይቀለበስ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝቦች የተሰውለትን ዲሞክራሲ ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ጋራ በምናደርገው የልምድ ልውውጥ ላይ ለድርድር የምናቀርበው አይደለም፡፡››

አቶ ሴኮቱሬ በሰንደቅ ጋዜጠኛ ለምን መንግሥታችን በአሜሪካ አምባሳደር ለመሾም እንደዘገየ ተጠይቀው ነበር “ይህን ጥያቄ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ብታቀርበው የተሻለ ይኾናል” አሉት ጋዜጠኛውን፡፡

1147 የኦብነግ እስረኞች ተለቀቁ

መንግሥት ላለፉት 18 ዓመታት በትጥቅ ትግል ላይ ከነበረው ኦብነግ ጋራ ያደረገውን ስምምነት ተከትሎ 1147 የኦብነግ እስረኞች ምኅረት ተደርጎላቸው ከእስር ቤት ተሰናብተዋል፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት የአገር ቤት ጋዜጦች እንደዘገቡት ከኾነ ከተፈቱት እስረኞች መካከል 147ቱ ሴቶች ናቸው፡፡ ተፈቺዎቹ ከማኅበረሰቡ ጋራ ተቀላቅለው እንዲኖሩም መንግሥት ገንዘብ ይመድብላቸዋል፡፡ የተወሰኑት የዕድሜ ልክ እስራት ፍርደኞችም ከተፈቱት መካከል እንደነበሩ ተዘግቧል።

“ሰመራ ዩኒቨርሲቲ በረሃ ላይ ያለ እስር ቤት ነው።”

ሳምንታዊው ፍትህ ጋዜጣ በፊት ገፁ ስለሰመራ ዩኒቨርሲቲ አስገራሚ ዜና አስነብቧል፡፡ “ዩኒቨርሲቲው የወንዶች መጸደጃ ቤት የለውም፡፡ ወንድ ተማሪዎች ጨለማን ተገን አድርገው ሜዳ ላይ ይጸዳዳሉ፤ የሴቶች ሽንት ቤት ሙሉ በሙሉ በቆርቆሮ የተሠራ በመኾኑ ከአካባቢው 45 ዲግሪ ሙቀት ጋራ ተደማምሮ ከጉድጓድ የሚወጣውን ትነት ለማሕፀን ካንሰር ያጋልጣል” ሲል ፍትህ ጋዜጣ የተማሪዎችን እሮሮ አስነብቧል።

በዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ የውኃ ችግር በመኖሩ ለመታጠብ የግድ ከሰመራ ዐሥር ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ወደምትገኘው ሎጊያ ከተማ መጓዝ ይገደዳሉ፡፡ ከዚህም ባሻገር የዩኒቨርሲቲው መምህራን የማስተማር ፍላጎታቸው ዝቅተኛ ነው የሚለው ዘገባው ይህም የኾነው ደሞዝ በጊዜው ስለማይከፈላቸው፣ የመምህራን መጸዳጃ ቤት እና ካፌ ባለመኖሩ፣ እንዲሁም በአካባቢው ከፍተኛ ሙቀት በመኖሩ እንደኾነ ያብራራል። ዘንድሮ ሰመራ ዩኒቨርሲቲ 1500 ተማሪዎችን ተቀብሏል።

የፎቶ ስቱዲዬ በ2.5 ሚሊዮን ብር

ጌት የፎቶ ስቱዲዬ ይባላል፡፡ በአዲስ አበባ ኻያ ሁለት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ኤች ኤንድ ኤም ሕንፃ ላይ በ200 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ነው ያረፈው፡፡ ደርባን ከተማ ነዋሪ በነበረ እስክንድር ዋሴ በተባለ ወጣት ነው የተገነባው፡፡ በውስጡ በተራራ ቅርጽ የተሠራ ፋውንቴን፣ ተንቀሳቃሽ አልጋ እና ሌሎች ብዙ ገጽታዎችን ይዟል፡፡ ስቱዲዮው ለሙሽሮች፣ የሙዚቃ ክሊፕ መቅረጽ ለሚፈልጉ አርቲስቶች፣ ለፊልም ሠሪዎች አገልግሎት ይሰጣል። የቢልቦርድ ማስታወቂያ ማሠራት የሚችሉ ዘመናዊ ማሽኖችም ተገጥመውለታል። ይህን በዐይነቱ የመጀመርያ የኾነ የፎቶ ስቱዲዮ ለማስገንባት 2.5 ሚሊዮን ብር ፈጅቷል፤ አውራምባ እንደጻፈው፡፡

የአገር ቤት ምርቃት

  • “የምንዛሬ ዋጋ ጨምሯል እና የድንች ዋጋ ካልጨመርኩ የሚል ነጋዴ ሚዛናዊ ቁንጥጫ ያስፈልገዋል” አቶ መለስ ለፓርላማ፤ አውራምባ እንደዘገበው።
  • “ጉድ በሉ! በየነና መረራ ፓርላማ መግባትን ተቃወሙ” ፍትህ ጋዜጣ
  • “አንጋፋው ድምፃዊ ይርጋ ዱባለ በጠና ታመዋል” ሰንደቅ ጋዜጣ
  • “ኢሕአዴግ ይሉኝታ እና ኀፍረት ያልፈጠረበት፤ ማስመሰልን የተካነ እና ለዝንተ ዓለም የሚዋሽ ፓርቲ ነው።” አንድነት ፓርቲ
  • “በአሜሪካ ማንም ሰው ከ15-20 ዓመት እንዲገዛ አንፈልግም።” ፕሮፌሰር ሪቻርድ ሉዊ ለአውራምባ ታይምስ
  • “ልጄ አትመራኝም አለ የተባለው መሠረት የለሽ የስም ማጥፋት ነው፡፡…አሜሪካ አገር ዩኒቨርሲቲ ሳስተምር ሁለት ጊዜ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት የነበሩት ሴቶች ነበሩ።”  ዶክተር ያዕቆብ ኀ/ማርያም ለአውራምባ ታይምስ፡፡

One Response to “የአገር ቤት ጋዜጦች ምን ጻፉ?”

  1. በጣም የሚያሳዝን እና የሚገርም ነገር ነው! ሌላ ምንም ማለት አይቻልም::
    እርግጠኛ ነኝ አቶ ነጋሶ የተሻለ ነገ ይመጣላቸዋል:: መለስ ስልጣን ሲለቅቅ (ሲለቅቁ)ፕሮፌሰር ፧ የተባበሩት መንግስታት አማካሪ ምናምን ምናምን ይሆናል አይደለ ተረቱ :)

  2. i’m really disappointed withdr.negasos monthly penstion money.the leading party tplf andhis cadres(kangaro make with him ridiculous game).how ot could be tha one who lead ethiopian for 5years on presdent..they decide 1197.60 it is less than 50€ very embarrassing judgement….those who make this!!!
    may god keep ethiopian for those tyrant administration

Leave a Reply

You must be to post a comment.

ኢትዮ ፍላሜንኮ የጃዝ ኮንሰርት ትላንት ቀረበ

ስፔናውያኑ የፒያኖ ተጫዋች አይዛክ ቱሪየንዞና፣ ባለዋሽንቱ ጆርጌ ፓርዶ ተቀላቅለዋቸው ‹‹ኢትዮጵያ ሀገሬ›› እና ‹‹አምባሰል›› የተሰኙትን ተወዳጅ ኢትዮጵያዊ ሥራዎች በጃዝ ስልት አቅርበዋል፡፡ በየሙዚቃው ጣልቃ ሁሉም በየተራ የራሳቸውን ብቃት ብቻ በሚያሳዩበት አጋጣሚ ከታዳሚው የሞቀ ጭብጨባና አድናቆት የተበረከተላቸው ቢሆንም ከአምስት ዐሥርት-አመታት በላይ በሳክስፎኒስትነት የሚታወቁትን የአቶ ጌታቸው መኩሪያን ያህል አድናቆት ያገኘ አልነበረም።

የስፔን አምባሲ የባህል ክፍል ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ‹‹ኢትዮ ፍላሜንኮ›› የተሰኘ የጃዝ ኮንሰርት ትላንት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ቀርቧል፡፡ ስመጥር የኢትየጵያና የስፔን የጃዝ ሙዚቀኞች የተካፈሉበት ይህ ኮንሰርት የጀመረው የስፔኑ የባህል  አታሼ ባደረጉት ንግግር ከምሽቱ 12፡30 ላይ ነበር፡፡

የባህል አታሼው በንግግራቸው በገለፁት የፕሮግራሙ ቅደመ ተከተል መሰረት በመጀመሪያ አርማንዶ ኦረበን የተባለው ጊታሪስት ሁለት የስፔን የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን ከተጫወተ በኋላ አይዛክ ቱሪየንዞ የተባለው ፒያኒስት ለብቻው የራሱን ተወዳጅ ረቂቅ የሙዚቃ ቅንብር አቅርቧል፡፡ ጆርጌ ፓርዶ በዋሽንት አንድ ረጅም የስፔን የሀገረሰብ ሙዚቃን ካቀረበ በኋላ ዝነኞቹ የኢትዮጵያ የጃዝ ሙዚቀኞች ሳክስፎኒስት ጌታቸው መኩሪያ፣ ቤዝ ጊታሪስት ሔኖክ ተመሰገን እና ድራመር ናትናኤል ተሰማ በጋራ መድረኩ ላይ እንደወጡ አዳራሹን ሞልቶ የነበረው ከ1200 በላይ የሚኾን ተመልካች በጭብጨባ ደማቅ አቀባበል አድርጎላቸዋል፡፡

ሦስቱም በጋራ ‹‹አይ የዘመዴ›› ፣ ‹‹ብርቱካኔ›› ፣ ‹‹የማትበላ ወፍ›› እና ‹‹ሸግዬ ሸጊቱ›› የተሰኙት ተወዳጅ ሥራዎችን በሳክስፎን፣ በቤዝ ጊታርና በድራም አጀብና አስገራሚ ውህደት ሲያቀርቡ የአዳራሹን ስሜት በደንብ ለመግዛት ችለዋል፡፡

ስፔናውያኑ የፒያኖ ተጫዋች አይዛክ ቱሪየንዞና፣ ባለዋሽንቱ ጆርጌ ፓርዶ ተቀላቅለዋቸው ‹‹ኢትዮጵያ ሀገሬ›› እና ‹‹አምባሰል›› የተሰኙትን ተወዳጅ ኢትዮጵያዊ ሥራዎች በጃዝ ስልት አቅርበዋል፡፡ በየሙዚቃው ጣልቃ ሁሉም በየተራ የራሳቸውን ብቃት ብቻ በሚያሳዩበት አጋጣሚ ከታዳሚው የሞቀ ጭብጨባና አድናቆት የተበረከተላቸው ቢሆንም ከአምስት ዐሥርት-አመታት በላይ በሳክስፎኒስትነት የሚታወቁትን የአቶ ጌታቸው መኩሪያን ያህል አድናቆት ያገኘ አልነበረም።

አቶ ጌታቸው መኩሪያ ከመድረክ ከወረዱ በኋላ ስፔናዊው ጊታሪስት አርማንዶ ኦርቦን ተክቷቸዋል፡፡ አምስቱ በጋራ በመኾን ሦስት ተወዳጅ የስፔን የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን እና የቡልጋሪያዊው ፒያኔስትና የረቂቅ ሙዚቃ ቀማሪ ተወዳጅ ሥራ በጃዝ ስልት ካቀረቡ እና የተወሰኑ ሙዚቃዎች በጋራ ከተጫወቱ በኋላ ፕሮግራሙ ተጠናቋል።



One Response to “ኢትዮ ፍላሜንኮ የጃዝ ኮንሰርት ትላንት ቀረበ”

  1. በጣም የሚያሳዝን እና የሚገርም ነገር ነው! ሌላ ምንም ማለት አይቻልም::
    እርግጠኛ ነኝ አቶ ነጋሶ የተሻለ ነገ ይመጣላቸዋል:: መለስ ስልጣን ሲለቅቅ (ሲለቅቁ)ፕሮፌሰር ፧ የተባበሩት መንግስታት አማካሪ ምናምን ምናምን ይሆናል አይደለ ተረቱ :)

  2. i’m really disappointed withdr.negasos monthly penstion money.the leading party tplf andhis cadres(kangaro make with him ridiculous game).how ot could be tha one who lead ethiopian for 5years on presdent..they decide 1197.60 it is less than 50€ very embarrassing judgement….those who make this!!!
    may god keep ethiopian for those tyrant administration

Leave a Reply

You must be to post a comment.

የቢኒያም ወርቁ “ሰባተኛው ሰው” ሰኞ ይመረቃል

የፊልሙ ታሪክ ከአንድ የሚኒስቴር መሥርያ ቤት ለወርክሾፕ ወደ አሜሪካ ለሥራ ከተላኩ ሰባት ሠራተኞች ውስጥ አንደኛው ተመልሶ ወደ አገሩ በመምጣቱ የሚደርስበትን ጫና እና ትችት የሚተርክ ነው። ለሰባተኛው ሰው በዙሪያው ካሉ ወዳጆቹ፣ ቤተሰቡ እና የሥራ ባልደረቦቹ በተደጋጋሚ የሚነገረው ወርቃማ ዕድል እንዳበላሸ እና በቅብጠቱ እንደተመለሰ ነው። ፊልሙ የውጭ ዕድል በዚህ ዘመን ምን ዐይነት መልክ እየያዘ እንደመጣ በማሳየት ላይ ያተኩራል።

“ሰባተኛው ሰው” የተሰኘው የቢኒያም ወርቁ አዲስ ፊልም ሰኞ አመሻሽ 12፡00 ሰዓት ላይ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ይመረቃል፡፡

የፊልሙ ታሪክ ከአንድ የሚኒስቴር መሥርያ ቤት ለወርክሾፕ ወደ አሜሪካ ለሥራ ከተላኩ ሰባት ሠራተኞች ውስጥ አንደኛው ተመልሶ ወደ አገሩ በመምጣቱ የሚደርስበትን ጫና እና ትችት የሚተርክ ነው። ለሰባተኛው ሰው በዙሪያው ካሉ ወዳጆቹ፣ ቤተሰቡ እና የሥራ ባልደረቦቹ በተደጋጋሚ የሚነገረው ወርቃማ ዕድል እንዳበላሸ እና በቅብጠቱ እንደተመለሰ ነው። ፊልሙ የውጭ ዕድል በዚህ ዘመን ምን ዐይነት መልክ እየያዘ እንደመጣ በማሳየት ላይ ያተኩራል።

የፊልሙ ደራሲ እና ዳይሬክተር ቢኒያም ወርቁ ፊልሙን ለማጠናቀቅ ሦስት ወራት እንደሰደበት ገልጿል። በቅድመ ዝግጅት፣ በቀረጻ እና በድኅረ ዝግጅት ሦስት ወራትን የወሰደው ይኸው ፊልም ለአጠቃላይ ሥራው ሦስት መቶ ሺሕ ብር አስፈልጎት እንደነበርም ጨምሮ ገልጿል።

አዘጋጆቹ የፊልሙን መታሰቢያነት ከጥቂት ወራት በፊት ከዚህ ዓለም በሞት ለተለየው እና በበርካታ ፊልሞች ላይ በትወና ፣ በዝግጅት፣ በድርሰት እና በአማካሪነት ለሠራው አንጋፋው አርቲስት ጌታቸው አበራ አድርገዋል፡፡

በአስቴር ፊልም ፕሮዳክሽን በተዘጋጀው በዚህ ፊልም ላይ ሰለሞን ቦጋለ ፣ ኪሮስ ኀ/ሥላሴ፣ ተሻለ ወርቁ፣ ሳምሶን (ቤቢ)፣ ቢንያም ወርቁ፣ ፈቃዱ ከበደ፣ ይገረም ደጀኔ፣ ስርጉተ ማርያም እና ሌሎችም ይተውኑበታል። የፊልሙ ዘውግ ሳታየር ኮሜዲ ሲኾን አንድ ሰዓት ከኻያ ደቂቃዎችን ይወስዳል።

ተዋናይ፣ ደራሲ እና ዳይሬክተር ቢኒያም ወርቁ ከዚህ ፊልም በፊት በድርሰት፣ በትወና እና በዝግጅት በተሳተፈባቸው “አባትየው” (the father)፣ “የተወጋ ልብ”፣ “ስውሩ እስረኛ”፣ “ውበት ለፈተና”፣ “በራሪ ልቦች”፣ “አዲስ ሙሽራ”፣ “ቫኬሽን ፍሮም አሜሪካ” በሚሉ ፊልሞች እና “የአልማዝ ቀለበት” እና “ሜዳሊያ” በተሰኙት ቴአትሮች ይታወቃል።

One Response to “የቢኒያም ወርቁ “ሰባተኛው ሰው” ሰኞ ይመረቃል”

  1. በጣም የሚያሳዝን እና የሚገርም ነገር ነው! ሌላ ምንም ማለት አይቻልም::
    እርግጠኛ ነኝ አቶ ነጋሶ የተሻለ ነገ ይመጣላቸዋል:: መለስ ስልጣን ሲለቅቅ (ሲለቅቁ)ፕሮፌሰር ፧ የተባበሩት መንግስታት አማካሪ ምናምን ምናምን ይሆናል አይደለ ተረቱ :)

  2. i’m really disappointed withdr.negasos monthly penstion money.the leading party tplf andhis cadres(kangaro make with him ridiculous game).how ot could be tha one who lead ethiopian for 5years on presdent..they decide 1197.60 it is less than 50€ very embarrassing judgement….those who make this!!!
    may god keep ethiopian for those tyrant administration

Leave a Reply

You must be to post a comment.

“ውስብስብ ውሎዎች” የተሰኘ የአጫጭር ልቦለዶች መድብል ዛሬ ተመረቀ

በሥነ ሥርዐቱ ላይ የደራሲዋ ወዳጆች እና ታዳሚዎች በርካታ መጻሕፍትን በመግዛት ደራሲዋ ለምታሳድጋቸው እና ለምትንከባከባቸው የጎዳና ሕፃናት፣ ለቀይ ሽብር ሰማዕታት ቤተ መጻሕፍት እና ለኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር ቤተ መጻሕፍት በስጦታ አበርክተዋል።

ደራሲት በሁሉም አለበል “ውስብስብ ውሎዎች” በሚል ርዕስ የተጻፉ አጫጭር ልቦለዶችን እሁድ ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ 6፡00 ሰዓት በዘለቀው የምርቃት ሥነ ሥርዐት ካዛንቺስ በሚገኘው በዮፍታሄ ሲኒማ አስመረቀች። የደራሲት በሁሉም አለበል የኾነው ይኸው ሥራ በሁለት መቶ ገጾች የተጠናቀረ ሲኾን በአጠቃላይ ዐሥራ አንድ አጫጭር ልቦለዶችን አካቷል።

ደራሲዋ በምርቃት ሥነ-ሥርዐቱ ላይ ባደረገችው ንግግር የመጽሐፉን ረቂቅ ጽፋ ካጠናቀቀችበት ጊዜ ጀምሮ በኅትመት ሂደቱ እንዲሁም የመጽሐፉን ምርቃት በደመቀ ኹኔታ እስከማዘጋጀት ድረስ ከፍተኛ እገዛ ያደረጉላትን የኢትዮጵያ ሥነ-ጽሑፍ አጥኚ እና ተመራማሪ የኾኑትን ተባባሪ ፕሮፌሰር ዘሪሁን አስፋውን፣ ታዋቂውን ደራሲ፣ ሐያሲ እና የወግ ጸሐፊ መሥፍን ሀብተ ማርያምን፣ የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበርን እና ዜማ ብዕር ኢትዮጵያ የሴቶች የሥነ ጽሑፍ ማኅበርን አመስግናለች።

የምርቃት ሥነ-ሥርዐቱን የመራችው የዜማ ብዕር ኢትዮጵያ የሴቶች የሥነ ጽሑፍ ማኅበር ምክትል ፕሬዝዳንት የኾነችው እና “ቢስ ራሔል”፣ “አንጉዝ”፣ “ቋሳ”፣ እመምኔቷ” እና “የስሜት ትኩሳት” በሚሉት መጻሕፍቷ የምትታወቀው ደራሲት እና ገጣሚት ፀሐይ መላኩ ስትኾን በምርቃቱ ላይ አዝናኝ ኪነጥበባዊ ፕሮግራሞች ቀርበዋል።

በሥነ ሥርዐቱ ላይ የደራሲዋ ወዳጆች እና ታዳሚዎች በርካታ መጻሕፍትን በመግዛት ደራሲዋ ለምታሳድጋቸው እና ለምትንከባከባቸው የጎዳና ሕፃናት፣ ለቀይ ሽብር ሰማዕታት ቤተ መጻሕፍት እና ለኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር ቤተ መጻሕፍት በስጦታ አበርክተዋል።

በሞያዋ ግራፊክ ዲዛይነር የኾነችው በሁሉም አለበል ከሁለት ዓመታት በፊት “ሳምራዊ” እና “የሸንበቆ ባህር” የተሰኙ የግጥም መድብሎችን ለኅትመት አብቅታለች። “ውስብስብ ውሎዎች” ለአገር ውስጥ አንባቢያን በኻያ ብር እንዲሁም ከኢትዮጵያ ውጪ ለሚገኙ አንባቢያን ደግሞ በአምስት ዶላር ለሽያጭ እንደቀረበ ታውቋል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

የአገር ቤት ጋዜጦች ምን ጻፉ?

“ለድርድር የሚጋበዘው የታጠቀ ብቻ ነው?” በሚል አንኳር ጥያቄ በርዕሰ አንቀጹ የሚያነሳው ፍትህ ጋዜጣ ሰሞኑን መንግሥት ከኦብነግ ጋራ ያካሄደውን ድርድር እና ስምምነት “ሰላማዊ ትግል ለሚያካሄዱትም መነፈግ የለበትም” ሲል የጋዜጣውን አቋም ለማንጸባረቅ ሞክሯል፡፡ “ለድርድር ወታደራዊ አቅም፣ ታንክ እና ክላሽ መሥፈርት መኾን የለበትም” ሲል ያተተው ይኸው “ፍትህ” ጋዜጣ ዘጠኝ ቻይናውያንን እና ከስድሳ በላይ ኢትዮጵያዊያንን እንደበግ ያረዱት የኦብነግ እስረኞች ከተፈቱ በሰላም ስለተቃወሙ ብቻ እስር ቤት የታጎሩት የቅንጅት እና ሌሎች የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ለምን ይረሳሉ”

“ፍትህ ጋዜጣ” ዘወትር አርብ የሚወጣ ባለ ሽሮ መልክ ጋዜጣ ነው፡፡ ከአገር ቤት ጋዜጦች ሁሉ አነስ ያለ ገጽ እና ጠቆር ያለ መልክ አለው። ፍትህ በዚህ ሳምንት እትሙ ኮስተር ያሉ ፖለቲካዊ ትችቶችን በገዢውም በተቃዋሚውም ጎራ ባሉ ፖለቲከኞች ላይ ሰንዝሯል፡፡

“ለድርድር የሚጋበዘው የታጠቀ ብቻ ነው?” በሚል አንኳር ጥያቄ በርዕሰ አንቀጹ የሚያነሳው ፍትህ ጋዜጣ ሰሞኑን መንግሥት ከኦብነግ ጋራ ያካሄደውን ድርድር እና ስምምነት “ሰላማዊ ትግል ለሚያካሄዱትም መነፈግ የለበትም” ሲል የጋዜጣውን አቋም ለማንጸባረቅ ሞክሯል፡፡ “ለድርድር ወታደራዊ አቅም፣ ታንክ እና ክላሽ መሥፈርት መኾን የለበትም” ሲል ያተተው ይኸው “ፍትህ” ጋዜጣ ዘጠኝ ቻይናውያንን እና ከስድሳ በላይ ኢትዮጵያዊያንን እንደበግ ያረዱት የኦብነግ እስረኞች ከተፈቱ በሰላም ስለተቃወሙ ብቻ እስር ቤት የታጎሩት የቅንጅት እና ሌሎች የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ለምን ይረሳሉ ይጠይቃል በርዕሰ-አንቀጹ።

ጋዜጣው በርእሰ አንቀጹ ካቀረበው ሙግት ባሻገር በሦስት የተለያዩ የጋዜጣው አምዶች ላይ በሦስት ፖለቲከኞች ላይ ያፌዛል፣ ይሳለቃል፣ ይተቻል።

አባዱላ እና መዶሻቸው

“የአራት ኪሎ ጫዎታ” በተሰኘው ዐምዱ አዲሱን አፈ-ጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳን በአሽሙር አላስተረፋቸውም፡፡ የሰውየው ሥልጣን “ሹመት ወይስ ሹፈት” ሲል ይቀልድ እና አቶ አባዱላ ቀድሞ ጄኔራል ኾነው መቆየታቸው የአፈ-ጉባዔውን መዶሻ በምን ያህል መጠን መምታት እንዳለባቸው ለማወቅ እንዳላስቻላቸው ይተነትናል። “መዶሻውን ስብሰባው ሳያልቅ ደጋግመው እየመቱት ይስቃሉ፤ ዓመታታቸው ደግሞ ለከት የለውም፤ እኔ በአራት ኪሎ ሳልፍ እንኳ መዶሻው ግው..ግው ሲል ሰምቻለኹ” ይለናል የዚህ ፌዝ ዐምድ አዘጋጅ።

ዶክተር ያዕቆብና ውል-ውል አቋማቸው

ፍትህ ጋዜጣ ዶክተር ያዕቆብ ኀይለማርያም የአስተሳሰብ መዋዠቅ በተደጋጋሚ የሚታይባቸው ፖለቲከኛ እንደኾኑ ለማስረዳት አንድ ዐምድ ሙሉ ጽፏል፡፡ በተለይ ዶክተሩ ሰሞኑን የብርቱካንን መፈታት ተከትሎ የሰነዘሩት አስተያየት ይህንኑ የሰላ ሂስ እንዲዘንብባቸው ሳይዳርጋቸው አልቀረም። እንዲህ ነበር ያሉት፡-

“ከእንግዲህ ወደ ፖለቲካው ተመልሼ ብርቱካንን ማገልገል እፈልጋለሁ፤ እርሷ በመደበችኝ ቦታ ሁሉ ለመሥራት ዝግጁ ነኝ።” ጋዜጠኛው ጥያቄ አስከተለ፤ “ወደ ፓርቲ የአመራር ቦታ ማለትዎ ነው?” እርሳቸውም አሉ – “ብርቱካን ከመደበችኝ በየትኛውም ቦታ ከበታቿ ኾኜ ለመሥራት ዝግጁነቴን ዛሬ ላይ ከደስታ ጋር እገልጻለሁ።”

ዶክተሩ የፖለቲካ አቋማቸውን እንደከነቴራ ይቀያይራሉ ብሎ የሚሟገተው ጋዜጣው እንደማስረጃ እርሳቸው በተለያየ ጊዜ ተናገሯቸው የሚላቸውን ንግግሮች አስነብቧል። ለምሳሌ፡- “በቅንጅት ጊዜ ያጠፋው ልደቱ ብቻ አይደለም፤ ሁላችንም ላጠፋነው ጥፋት ይቅርታ ልንጠይቅ ይገባል” ብለው አወዛጋቢ መግለጫ በሪፖርተር ጋዜጣ መስጠት ጀመሩ። ቀጠሉና ብዙም ሳይቆዩ “በቃኝ ወጣቱ ደግሞ ይምራ” አሉ፡፡ አንድነት ፓርቲ ተመሥርቶ ብርቱካን በሊቀንመበርነት መመረጧ ቅሬታ ፈጥሮባቸው “እኔን ሴት አትመራኝም” ማለታቸውን ባልንጀሮቻቸው አጋለጧቸው። እርሳቸውም ለማስተባበል አልሞከሩም።”

ጋዜጣው ይቀጥልና፡- ብርቱካን ስልጣን ይዛ መምራት ስትጀምር ከአንድነት ፓርቲ ለመልቀቅ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ያወሳል፡፡ ብርቱካን ስትታሰር ደግሞ “የአስገባሁትን የእለቃለሁ ደብዳቤ አንስቻለሁ፤ ሊቀመንበራችን ታስራ አልሄድም” አሉ ይለናል፡፡ በዚህን ጊዜ አልለቅም ያሉት ትግሉ እንዲጎዳ ስላልፈለጉ ነው ተባለ፡፡

ቆየት ብለው ደግሞ “ከእንግዲህ ፖለቲካ በቃኝ ወጣቱ መተካት አለበት” ብለው ከፖለቲካው ለአፍታ ገለል አሉ። ብርቱካን ስትፈታ ደግሞ “የፈለገችው ቦታ ታሠራኝ” ማለታቸው ዶክተሩ የአቋም ውል ውል እንደሚታይባቸው ማስረጃ ነው ይለናል፡፡ “ከእንግዲህ  በቃኝ ወጣት ይተካ” ብለው የተዉትን ፖለቲካ የሚመለሱበት ሰውየው ተመልሰው ወጣት ኾኑ እንዴ? ሲል ጋዜጣው የእርሳቸውን ቆየት ያለ የወጣትነት ፎቶ ጭምር አስደግፎ በማተም ይሳለቃል፡፡

“ብርቱካን የዓላማ ጽናት እንጂ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ማለት አይደለችም፡፡ የሚታገሉት ለአንዲት ብርቱካን ሳይኾን ለአንዲት ኢትዮጵያ ነው፡፡ የፖለቲካ ትግል ብርቱካን የምትሰጥዎ እና የምትነሳዎ ጉዳይ አይደለም፡፡ የፖለቲካ ትግልዎ በብርቱካን መምጣት እና መሄድ የሚወሰን መኾን የለበትም” ሲል ጽሑፉ ጠጠር ያለ ትችቱን ያጠናቅቃል፡፡

የኢንጂነር ግዛቸው አስር ‹‹አናዳጅ›› ንግግሮች

በነገራችን ላይ ፍትህ ጋዜጣ በሌላኛው አምዱ “በፈረንሳይ ነዋሪዎች ኮራን በኢ/ር ግዛቸው አረርን” በሚል ኢንጂነሩ በተለያዩ ጊዜ የተናገሯቸውን “ቆሽት የሚያሳርሩ” ያላቸውን 10 ንግግሮችን አስነብቧል፡፡ “ለሚዲያ የሚሰጡ ቃላት እንደ እንቁላል ናቸው አንዴ ካመለጡ መመለሻ የላቸውም” ሲል የሚጀምረው ይኸው ጽሑፍ ኢ/ሩ በተለያዩ ጊዜያት ለሚዲያ የተናገሯቸውን “አናዳጅ” ያላቸውን ንግግሮች ዘርዝሯል፡፡

ኢንጂነሩ በአንድ ወቅት “ፓርቲው በብርቱካን ጉዳይ ላይ በበቂ እየሠራ አይደለም” ተብለው በተጠየቁ ጊዜ “እንዲህ የሚሉት ከእናቷ በላይ ለብርቱካን ተቆርቋሪ መኾን የሚቃጣቸው ናቸው፡፡” ብለዋል ይለናል ጋዜጣው፡፡ “ችግራችሁን ከእነፕሮፌሰር መስፍን ጋራ ለምን በውይይት አትፈቱም” ተብለው በተጠየቁ ጊዜ ደግሞ “እነርሱ ፓርቲ የማፍረስ ተልዕኮ ያላቸው ወያኔ ያደራጃቸው የመንግሥት ድጋፍ ያላቸው አካላት ናቸው” ብለዋል እንደ ጋዜጣው ገለጻ፡፡ የአንድነትን ፕሮግራም ማን አሻሻለው ተብለው በአንድ ወቅት በሪፖርተር ጋዜጣ ሲጠየቁ “እኔ እና አቶ ዐሥራት” ሲሉ መለሱ፣ ይህም ሳይበቃ በግንቦት ዐሥራ አምስቱ ምርጫ መጠናቀቅ ማግስት የሰጡትን አስተያየት በደቂቃዎች ውስጥ ኢቲቪን ጠርተው ይቅርታ አድርጉልኝ ማለታቸውም ከአናዳጅ ነጥቦች ውስጥ ተካቷል፡፡ ጋዜጣው የኢንጂነሩን ዐሥር አናዳጅ ንግግሮች ከዘረዘረ በኋላ “እባክዎን ሳያስቡ መናገር ይቅርብዎ” ሲል ኢንጂነሩን ይመክራል፡፡

ሕገ መንግሥቱ ሲጸድቅ በደስታ ሲዘሉ በቲቪ የሚታዩት ሰው ተገድለዋል

ፍትህ ጋዜጣ በዜና አምዱ ከትላንት በስተያ ለኢሕአዴግ አመራሮች ተሰራጨ ያለውን የፓርቲው ልሳን የኾነውን “አብዮታዊ ዲሞክራሲ” መጽሔትን ጠቅሶ እንደዘገበው አሁን በሥራ ላይ ያለው ሕገ-መንግሥት ሲጸድቅ የሙስሊም ቆብ እና ጋቢ ለብሰው እየዘለሉ ሲያጨበጭቡ በቴሌቭዥን የምናያቸው አዛውንት በኦነግ በዚያው ሰሞን በስምንት ጥይት ተደብድበው ተገድለዋል፡፡ ጋዜጣው በተጨማሪ የፓርቲውን ልሳን ምንጭ አድርጎ እንደጻፈው ህወሓት በ1993 የተከሰተውን ክፍፍል “የከሸፈ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ” እንደነበረ ለመጀመርያ ጊዜ አምኖ በልሳኑ ላይ መጻፉን ይነግረናል፡፡

“ኢትዮጵያዊ” መኪናዎች እየበዙ ነው

ሆላንድ ካር ልዩ የከተማ አውቶብስ መሥራቱ በዚህ ሳምንት በወጡ ጋዜጦች ተዘግቧል፡፡ በኢትዮጵያ የቤት አውቶሞቢሎችን በመገጣጠም የመጀመርያ የኾነው ሆላንድ ካር ዐባይ፣ አዋሽ እና ሸበሌ የተሰኙ መኪኖችን ከገጣጠመ በኋላ ፊቱን ወደ አውቶብሶች መልሷል፡፡ የትራንስፖርት ችግርን እንዲቀርፉ ተብለው ከሕዝብ፣ ከትራፊክ ፖሊስ፣ ከመንግሥት እና ከከተማ አውቶብስ ሐላፊዎች ጋራ በመምከር ዲዛይኑ እንደወጣ ያስታወቀው ሆላንድ ካር አውቶብሱን ለአገር ውስጥ እና ለአፍሪካ አገራት ጭምር ለገበያ እንደሚያቀርበው ተዘግቧል።

በተያያዘ ዜና የእንግሊዝኛው ሪፖርተር በሪል እስቴት እና በባንክ ይታወቅ የነበረው ፈርጀ ብዙው “አክሰስ ካፒታል አክሲዮን ማኅበር” መኪና የመገጣጠም ኢንዱስትሪ ውስጥ ሊሰማራ ነው ሲል ጽፏል፡፡ ለዚህም ከአንድ የቻይና ካምፓኒ ጋራ በመጋገር ላይ እንደኾነ ተዘግቧል፡፡ ሪፖርተር እንደጻፈው አክሰስ ወደዚህ የመኪና መገጣጠም ሥራ ከገባ ከሆላንድ፣ ከሊፋን እና ከማራቶን እንዲሁም ከበላይ አብ ቀጥሎ ስድስተኛው የመኪና መገጣጠሚያ ድርጅት ኾኖ ይመዘገባል፡፡

የሪፖርተር ርእሰ-አንቀጽ

ሪፖርተር ጋዜጣ ከተወለደ 15ኛ ዓመቱን ያዘ፡፡ ልደቱንም በዚህ ሳምንት እያከበረ ይገኛል፡፡ በረቡዕ ዕለት እትሙ የጋዜጣው ርእሰ-አንቀጽ የካቢኔ ሹመቱን ተከትሎ የብሄር ውክልና ጥያቄን ጥያቄ ውስጥ የሚከቱ ወገኖችን ሸንቆጥ ለማድረግ የታለመ አቋምን አንጸባርቋል፡፡ እንዲህ ይላል፡-

“ . . የትራንስፖርት ሚኒስትር ከኦሕዴድ ነው ማለት የኦሮሞ ሕዝብ እንዴት እንደሚጓዝ ብቻ ያስባል ማለት አይደለም፡፡…የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከደቡብ ወይም ከወላይታ ነው ማለት ወላይታ ከዓለም ጋራ ስለሚነኖራት ግንኙነት ብቻ ይጨነቃል ማለት አይደለም…፡፡›› ይል እና “የሁሉም አገልጋይነት ለመላ ኢትዮጵያ መኾኑ መዘንጋት የለበትም” ሲል ይዘልቃል፡፡ ርዕሰ-አንቀጹ የሥልጣኑን እውነተኛነት በሚጠይቁ ወገኖች ላይ ያነጣጠረ ይመስላል፡፡ እንዲህ ብሎ ያሳርጋል፡- “በአሜሪካ ታሪክ ለመጀመርያ ጊዜ ጥቁር አሜሪካዊ ፕሬዝዳንት ኾነ ብሎ ለኦባማ የጨፈረ ዲያስፖራ ለመጀመርያ ጊዜ ከደቡባዊ ኢትዮጵያ እንዴት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ኾነ ብሎ ሲናደድ እየተስተዋለ ነው፡፡”

ሪፖርተር ክብር ሚኒስትር በሚለው ዐምዱም በተመሳሳይ ኹኔታ ዳያስፖራውን ሸንቆጥ ለማድረግ ይሞክራል፡፡ “የብርቱካን መፈታት ኢሕአዴግን አስደስቷል ያላስደሰተው ተቃዋሚዎችን ነው፡፡” ይልና ለምን ለሚለው ሲመልስ “የይፈታልን አጀንዳ ስለሚያልቅባቸው” ሲል ይደመድማል፡፡

የመጀመርያዋ ሴት አብራሪ

ካፒቴን አምሳሉ ጉኣሉ ትባላለች፡፡ በታሪክ የመጀመርያዋ ሴት የመንገደኞች ካፒቴን ኾናለች፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት ኪው 400 የተባለቸውን አውሮፕላን አስነስታ መንገደኞችን አሳፍራ ባህርዳር ደርሳ ተመልሳለች፡፡ የአየር መንገዱ አዲሱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ እንዲሁም ቤተሰቦቿ ለእርሷ እና ላበረረቻት አውሮፕላን ልዩ አቀባበል አድርገውላታል፡፡

የቦሌው ጎዳና ሽር የምንልበት

አፍሪካ ጎዳና በሚል የሚታወቀው እና ከመስቀል አደባባይ እስከ ቦሌ ጫፍ የሚደርሰው መንገድ ብዙ የትራፊክ ፍሰት የሚስተናገድበት የአገራችን አውራ መንገድ ነው፡፡ ትልልቆቹ እንግዶቻችንም ፎቆቻችንን እያዩ የሚያልፉበት መኾኑ ጎዳናውን ልዩና ጠቃሚ ያደርገዋል፡፡ ይህ መንገድ ከሁለት ዓመት በፊት በዘመናዊ መልኩ ሊሠራ ውጥን ተይዞ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ከተጀመረ በኋላ እንዲቆም ተደርጎ ነበር፡፡ በዚህ ዓመት ግን ሥራው ይጀመራል ይላል ሳምንታዊው የእንግሊዝኛ ቢዝነስ ጋዜጣ የኾነው ካፒታል፡፡

የቻይናው ኤክሲም ባንክ ለዚህ መንገድ የሚኾን ብድር እሰጣለሁ ብሏል፡፡ ይህ መንገድ በዘመናዊ መልክ ሲታደስ መሀል ያለው ደሴት ጠፍቶ ሌላ መንገድ ይሆናል፡፡ “ኦሎምፒያ” ፣ “ጃፓን ጋ” እና “ወሎ ሰፈር” አካባቢ ከላይ የሚያልፉ መንገዶች ይኖሩታል፡፡ ፕሮጀክቱ ባጠቃላይ 40ሜትር ስፋት እና 4.1 ኪሎ ሜትር ርቀት ይኖረዋል፡፡ በተለይም ጃፓን ጋራ ያለው ድልድይ 300 ሜትር ርዝመት ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ይህ መንገድ እጅግ ወሳኝ በመኾኑ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ አገልግሎት ላይ መዋል ይኖርበታል፡፡ በመኾኑም የቻይናው ሲአርቢሲ ይህን ፕሮጀክት ሳይወስደው አይቀርም ይላል ጋዜጣው ግምቱን ሲያስቀምጥ፡፡

የአገር ቤት ምርቃት

“ሴት ጠቅላይ ሚኒስትር አይቼ ብሞት ደስ ይለኛል” ዶ/ር ያእቆብ በኢትዮቻናል

“የማንኛውም ፓርቲ አባል አይደለሁም” ሰራዊት ፍቅሬ ለአውራምባ ታይምስ ጋዜጣ

“ኢሕአዴግን እደግፋለሁ” ሳምሶን ማሞ ለቼንጅ ወርሃዊ የፖለቲካ መጽሔት

“የተሰጠኝ ሐላፊነት ከባድ ቢኾንም ከቅርብ አለቃዬ (ከአቶ መለስ) እና ከእግዜአብሔር ጋራ በመኾን እወጣዋለሁ፡፡” አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ለሬዲዮ ፋና (ምንጭ አውራምባ ጋዜጣ)

“ዲሞክራሲያዊ መንግሥት ቢኖር እና ሽልማቱ ወደዚህ ባይመጣ እመርጣለሁ” የሲፒጄ የዘንድሮ ተሸላሚ ዳዊት ከበደ ለፍትህ ጋዜጣ

“በነዳጅ ፍለጋ በተሰማሩት ላይ ጥቃት የፈጸመው ኦቦ የሚባለው አንዱ የግንባሩ ክንፍ ነው፡፡ እኛ ድርጊቱን አውግዘን ሀዘናችንን ገልጸናል፡፡›› ኢ/ር ሰለሀዲን አብዱረህማን የኦብነግ ሊቀመንበር ለአዲስ አድማስ

“የጁሊ ምህረቱ ሥዕል ከአንዲ ሚሊዮን ዶላር በላይ ተሸጠ” አዲስ አድማስ ጋዜጣ

One Response to “የአገር ቤት ጋዜጦች ምን ጻፉ?”

  1. በጣም የሚያሳዝን እና የሚገርም ነገር ነው! ሌላ ምንም ማለት አይቻልም::
    እርግጠኛ ነኝ አቶ ነጋሶ የተሻለ ነገ ይመጣላቸዋል:: መለስ ስልጣን ሲለቅቅ (ሲለቅቁ)ፕሮፌሰር ፧ የተባበሩት መንግስታት አማካሪ ምናምን ምናምን ይሆናል አይደለ ተረቱ :)

  2. i’m really disappointed withdr.negasos monthly penstion money.the leading party tplf andhis cadres(kangaro make with him ridiculous game).how ot could be tha one who lead ethiopian for 5years on presdent..they decide 1197.60 it is less than 50€ very embarrassing judgement….those who make this!!!
    may god keep ethiopian for those tyrant administration

Leave a Reply

You must be to post a comment.

ጓሳ – ያልተዘመረለት ተፈጥሮ

ደብረብርሃን፣ ባኬሎ፣ ጣርማ በር፣ መዘዞ፣ ማዞርያ፣ ጓሳ፣ መሀል ሜዳ፡፡ እነዚህ ወዳልተዘመረለት የጓሳ ምድር የሚያደርሱ የኢትዮጵያ ትንንሽ ከተሞች ናቸው፡፡ አዲስ አበባን መነሻ ካደረግን 260 ኪሎ ሜትር መራቅ ይኖርብናል፡፡ ይህ ድንቅ ስፍራ እንደ አክሱም ሽቅብ የተቀሰረ ሀውልት የለውም፤ እንደ ላሊበላ በፍልፍል ድንጋይ አልታነፀም፤ እንደ ኤርታሌ የሚንተከተክ ላቫ አልፈጠረበትም፡፡ እንዲያው ዝም ብሎ የተዘረጋ የፕላቶ ሸንተረር ነው፡፡ ግን ልብን ወከክ የሚያደርግ፣ ቢያዩት ቢያዩት የማይጠገብ እንዲሁም የማያልቅ፣ እንዲሁም የማይደክም ግን ደግሞ ሩቅና ሰ…ፊ!
…አቶ መለስ “መሀል ሜዳ” የመጡ ጊዜ ታድያ ሰውየው ያረፉበት ስፍራ “ሕይወት ሆቴል” በሚባል አነስተኛ የገጠር መዝናኛ መሆኑ ተነግሮኝ ይህንኑ ለማረጋገጥ ሄድኩኝ፡፡ ሆቴሏ በከተማዋ መሀል ትገኛለች፡፡ ሙሉ በሙሉ የጭቃ ቤት ስትሆን ጥግ ጥጉን የተሰሩ ወደ ጎን ያዘመሙ መኝታ ክፍሎችና አንድ ምግብ ቤት በውስጧ ይዛለች፡፡ የሆቴሉ እመቤት የሀበሻ ቀሚስ አድርገው፣ ግዙፍ መነፅራቸውን ደቅነው ለምሳ ቤታቸው የተገኘውን ሰው ለማብላት ተፍ ተፍ ሲሉ አገኘኋቸው፡፡

Guwasa 1

መሀመድ ሰልማን

ደብረብርሃን፣ ባኬሎ፣ ጣርማ በር፣ መዘዞ፣ ማዞርያ፣ ጓሳ፣ መሀል ሜዳ፡፡ እነዚህ ወዳልተዘመረለት የጓሳ ምድር የሚያደርሱ የኢትዮጵያ ትንንሽ ከተሞች ናቸው፡፡ አዲስ አበባን መነሻ ካደረግን 260 ኪሎ ሜትር መራቅ ይኖርብናል፡፡ ይህ ድንቅ ስፍራ እንደ አክሱም ሽቅብ የተቀሰረ ሀውልት የለውም፤ እንደ ላሊበላ በፍልፍል ድንጋይ አልታነፀም፤ እንደ ኤርታሌ የሚንተከተክ ላቫ አልፈጠረበትም፡፡ እንዲያው ዝም ብሎ የተዘረጋ የፕላቶ ሸንተረር ነው፡፡ ግን ልብን ወከክ የሚያደርግ፣ ቢያዩት ቢያዩት የማይጠገብ እንዲሁም የማያልቅ፣ እንዲሁም የማይደክም ግን ደግሞ ሩቅና ሰ…ፊ!

ፈጣሪ ሰማይና ምድርን ፈጠረ ሲባል መጀመርያ የተዘረጋው የተራራ ሰንሰለት ይህ ስፍራ መሆን አለበት አልኩ፤ለራሴ፡፡

ተፈጥሮን አይቶ ዝም ማለት እንጂ በንግግር አልያም በጽሑፍ ለመተንተን መሞከር ከንቱ ነው፡፡ የሕንጻን ውበት ስንት ጡብ እንደፈጀ፣ ስንት ማገር እንዳቆመ፣ ስንት ብር እንደተከሰከሰበት፣ እየተነተኑ ማዳነቅ ብዙ ጥረት አይጠይቅም፡፡ እንደ ጓሳ ያለ ዝም፣ ዥው ያለ ተፈጥሮን ግን ምን ብለው ይገልጹታል?

የአቶ መለስ እርጥብነት

የጓሳ ጎረቤት ከተማ “መሀል ሜዳ” ትባላለች፡፡ መብራት፣ ውሀ፣ ሆስፒታልና ሌሎች መሰረታዊ ነገሮችን እንደአቅሚቲ ያሟላች የገጠር ከተማ ነች፡፡ ያሳለፍነው ምርጫ ከመካሄዱ ወራት ቀደም ብሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአካል ተገኝተው ከጎበኟቸው ትንንሽ የሰሜን ሸዋ ከተሞች አንዷ ይቺው “መሀል ሜዳ” ነበረች፡፡

“ምንድነው የሚቸግራችሁ?” እያሉ አቶ መለስ ከገበሬዎች ጋር በአግዳሚ ወንበር ቁጭ ብለው መከሩ አሉ፡፡ የሰሜን ሸዋ ሕዝብ አንድ የአገር መሪ በዚህን ያህል ቅርበት ሲያናግረው የመጀመርያው በመሆኑ ጉድ አለ፡፡ መብራት ሃያ አራት ሰዓት እንዲሆን፣ ቴሌቪዥን እንዲዳረስ፣ መንገድ እንዲወጣ ወዘተ እያለ “አሉብኝ” የሚላቸውን አንገብጋቢ ችግሮች ለእርሳቸው በፊት ለፊት ተናገረ፡፡ እርሳቸውም አንዳች ሳያስቀሩ በቢክ እስክሪብቷቸው በመጻፍ ማስታወሻ ያዙ፡፡ ይህ የሆነው ታድያ በወርሃ ሚያዝያ ነበር፡፡

ይህንን ሁኔታ በወቅቱ በቅርበት የተከታተለው በኀይሉ ደምሰው የሚባል ልጅ-እግር ገበሬ ታድያ ስለእርሳቸው ታላቅነት ሲናገር ቃላት ያጥረዋል፡፡ “እርሳቸው እርጥብ መሪ ናቸው፤ ሚያዝያ እዚህ እንደመጡ ጀምሮ ዝናብ በዝናብ ሆነናል፡፡ ይኸው የእርሳቸው እርጥብነት በዓመት ሁለት ጊዜ እንድናመርት አስችሎናል፡፡ መብራቱንም ቃል በገቡት መሰረት 24 ሰዓት አደረጉልን፡፡ የተባረኩ መሪ ናቸው፡፡ ለምርጫ ግልብጥ ብለን ነው የመረጥናቸው” ሲል አድናቆቱን ገለጸልኝ፡፡ “የጃንሆይና የጃማይካ ታሪክ ጓሳ ላይ ተደገመ?” አልኩኝ በሆዴ፡፡

አቶ መለስ “መሀል ሜዳ” የመጡ ጊዜ ታድያ ሰውየው ያረፉበት ስፍራ “ሕይወት ሆቴል” በሚባል አነስተኛ የገጠር መዝናኛ መሆኑ ተነግሮኝ ይህንኑ ለማረጋገጥ ሄድኩኝ፡፡ ሆቴሏ በከተማዋ መሀል ትገኛለች፡፡ ሙሉ በሙሉ የጭቃ ቤት ስትሆን ጥግ ጥጉን የተሰሩ ወደ ጎን ያዘመሙ መኝታ ክፍሎችና አንድ ምግብ ቤት በውስጧ ይዛለች፡፡ የሆቴሉ እመቤት የሀበሻ ቀሚስ አድርገው፣ ግዙፍ መነፅራቸውን ደቅነው ለምሳ ቤታቸው የተገኘውን ሰው ለማብላት ተፍ ተፍ ሲሉ አገኘኋቸው፡፡

ስለ አቶ መለስ ሳነሳባቸው ከመቅፅበት ትኩረታቸውን ወደ እኔ አዞሩት፡፡ “እውን አቶ መለስ በዚህች ቤት አድረዋል?” ስል ጠየቅኳቸው፡፡ “ማደርስ አላደሩም..” አሉና ወይዘሮዋ ጫወታ ጀመሩ፡፡ “እርሳቸው እዚህ አላደሩም፡፡ ግን ምሳ ያዘጋጀሁላቸው እኔ ነኝ፡፡ እዚህ አንተው የተቀመጥክባት ቦታ ላይ እኔ ያዘጋጀሁላቸውን የፆም ብፌ ነው የበሉት፡፡ እጄ ጣፍጧቸው ነው የበሉልኝ፡፡”

“ስንት ብር አስከፈሏቸው?” ስል ጠየቅኳቸው፡፡ አማተቡ፡፡ “እርሳቸውን አላስከፍልም፤ ለምን ብዬ፡፡ ብሩን የከፈሉኝ የወረዳው አስተዳዳሪዎች ናቸው፡፡”

“መለስን ታድያ ምንም አላሉትም?”

“በልቶ ሲጨርስ አድናቂዎ ነኝ፡፡ (መለስን አንተም አንቱም እያሉ ነው የሚጠሩት) ይኸው የቁልፍ መያዣዬም አንተው ነህ ብዬ…(ንግግራቸውን አቋርጠው ወደ ሂሳብ መቀበያው በመሄድ መሳብያው ላይ ተሰክቶ የነበረውን ቁልፍ ይዘው መጡ) ይህችን የሱ ምስል ያለባትን ቁልፍ አሳየሁት፡፡ ሳቀና ፈረመልኝ፡፡ ፈጣሪ ይጠብቅህ ብዬ መርቄ ሸኘሁት፡፡”

በአካባቢው ካገኘኃቸው ገበሬዎች ውስጥ በአመዛኙ በአቶ መለስ ጉብኝት ከደስታቸው ያልተላቀቁ ነበሩ፡፡ የተወሰኑት ግን አንድ ቁጭት አለባቸው፡፡ “ጓሳን ቢጎበኝልን እንዴት ሸጋ ነበር” ይላሉ፡፡ ጓሳ መከበሪያቸው ናት፡፡ ጓሳ የክብር ማሳቸው ናት፡፡ ይህችን ድንቅ ስፍራ ታድያ እኚህ “እርጥብ መሪ” አላዩላቸውም፡፡ ይህ ልክ እንደ ጓሳ ሳር ዘወትር ይቆጠቁጣቸዋል፡፡፡

የጓሳ ማኅበረሰብ

በብዙኀን መገናኛ  ብዙ የተዘመረለት የአውራምባ ማኅበረሰብ ነው፡፡ የጓሳ ማኅበረሰብ ግን ብዙ ያልተዘመረለት ራሱ የቀመረው ድንቅ ባህል እንዳለው ተረድቻለሁ፡፡በተለይ የተፈጥሮ ሀብትን በመንከባከብ፡፡

በጓሳ ሰንሰለታማ ተራሮች የሚገኘውን ማንኛውምንም የተፈጥሮ ሀብት የነካ ጉድ ፈላበት፡፡ የጓሳ መንዞች በዚህ ቀልድ አያውቁም፡፡ “እረገነ !›› ብለው ይዝታሉ፡፡ ይህ የመጨረሻ ቁጣቸውን የሚገልጹበት ቃል ነው፡፡ የሚገርመው የአካባቢው ነዋሪዎቸ እንደ “አጣዬ” ካሉ ዝቅተኛ ቦታዎች ከብት ገዝተው በጓሳ ሲያልፉ እንኳ የበጎችን አፍ በቆዳ ሸብበው ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፤ ምንም አይነት ጉዳት በአካባቢው እጽዋቶች እንዳያደርሱ፡፡

መንዞች ድሮም በቃላቸው ያደሩ፣ ከዛቱ የማይመለሱ፣ በበቀል የሚንተገተጉ ህዝቦች ናቸው ይባላል፡፡ የልጆቻቸው ስሞችም ይህንን ለማመልከት የተቀመሩ ይመስላሉ፡፡ ደምሰው፣ ዳምጠው፣ በኀይሉ፣ እርገጤ፣ ደምመላሽ የሚሉት ስሞች እጅግ የሚዘወተሩ ናቸው፡፡ ከማህበረሰቡ ጋር በኢኮ ቱሪዝም ልማት ላይ የሚሰሩ ግለሰቦች እንደሚሉት ህዝቡ በተለይ በጓሳ ተራሮች ላይ ያለውን የተፈጥሮ ሀብት ነካህበት ማለት በአይኑ መጣህበት እንደማለት ነው፡፡

መንግሥታት ተቀያይረዋል፡፡ የጓሳ ማኅበረሰብ በተፈጥሮ ጥበቃ ላይ ያለው አቋም ግን አልተቀየረም፡፡ ጥናቶች እንደሚያስረዱት የጓሳ-መንዝ ሕዝብ ለተፈጥሮ ጥበቃ ማድረግ የጀመረው አሁን ሳይሆን ከ17ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ነው፡፡ በዚህ ዙርያ ተጠቃሽ የሆኑ ጥናቶች የጓሳን ማኅበረሰብ ከሰሀራ በታች ካሉ ለተፈጥሮ ጥበቃ ንቃት ካላቸው ማህበረሰቦች ቀደምቱ ሲሉ ይጠቅሱታል፡፡ የተፈጥሮ ሀብቱን ያለማንም እገዛ የሚጠብቅበት የራሱ የሆነ ስርዓት አለው፡፡ ይህም የ”ቀሮ ስርዓት” ይባላል፡፡ በ”ቀሮ ስርዓት” መሰረት ማንኛውም በጓሳ የሚገኝ የተፈጥሮ ሀብት ከሦስት እስከ አምስት ተከታታይ ዓመታት ተጠብቆ ይቆያል፡፡ ይህ ጥበቃ የጓሳ ሳርን የሚያካትት ሆኖ ማንኛውንም ግጦሽ ወይም አጨዳ በዓመት ከጥቅምትና ህዳር ወር ውጭ ማካሄድ ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡

አጥባቂ የኦርቶዶክስ አማኝ የሆነው የጓሳ ማኅበረሰብ በተለምዶ በየዓመቱ ከሐምሌ 12 ጀምሮ የሐዋርያት ፆም ሲፈታ ጓሳ ለጥበቃ ዝግ መሆኑን ያውጃል፡፡ ከዚህ ቀን በኃላ ማህበረሰቡ በመረጣቸው ሚሊሻዎች አካባቢው ይጠበቃል፡፡ ማንኛውንም በጓሳ ተራሮች ውስጥ የሚገኝን ተፈጥሮን መነካካት ፍፁም ክልክል ሆኖ ይቆያል፡፡

በነገራችሁ ላይ ጓሳ የሳር ስም ነው፡፡ በመንዝና አካባቢው ይህ የሳር አይነት ከእያንዳንዱ ነዋሪ ጋር ጥልቅ ቁርኝት አለው፡፡ በተለምዶ ከሚታወቀው የሳር አይነት ዘለግ ያለና ከርደድ ያለ ሆኖ ለልዩ ልዩ ተግባራት የሚውል የሳር አይነት ነው፤ ጓሳ፡፡ ማኅበረሰቡ ይህንን ሳር ለግጦሽ፣ ለሳር ክዳን ቤት መስሪያ፣ ለጭቃ ግድግዳ መስሪያ፣ ለአለንጋና ገመድ መስሪያ፣ ለማገዶና ምግብ ማብሰያ፣ለኮፍያ፣ ጊሳ ለሚባል የዝናብ ልብስ ፣ ሙሬ ለሚባል የቤት መጥረጊያ መስሪያ ይጠቀሙበታል፡፡ ሕዝቡ ዝተትና በርኖስን ከበግ እየሸለተ የመስራት ልምድም አለው፡፡

በጓሳ ምድር “የመስቀል ወፍና የአደይ አበባ” የሚለው ግጥም እምብዛም ትርጉም የለውም፡፡ አደይ አበባ በጓሳ እንደ አረም ዝም ብሎ መቼም የሚበቅል ነው፡፡ በተራ የግጦሽ መሬት እጅግ የሚያማምሩ በተለያዩ ቀለማት ያጌጡ የአበባ ዝርያዎች ወፍ ዘራሽ ሆነው ይበቅላሉ፡፡ ከአበቦቹ መሀል ደግሞ ጅብብራ የተሰኘው ዘምባባ መሰል ተክል ግትር ብሎ በየተወሰነ ርቀት ይታያል፡፡

የጓሳ አውቶብሶች

ይህ ማኅበረሰብ ችግር ሲገጥመው ይሰበሰባል፡፡ “እስቲ መላ ምቱ” ለማለት፡፡ ከደብረብርሃን እስከ ሞላሌ ትራንስፖርት ቢኖርም ሕዝቡ ከሞላሌ እስከ መሀል ሜዳ በሰው ጉልበትና በጋማ ከብት እቃ ማጋዝ ሰለቸው፡፡ “መላ በሉ” ተባለ፡፡ የማኅበረሰቡ ሽማግሌዎች መላ ዘየዱ፡፡ እያንዳንዱ የጓሳ አባል አንድ በግ አዋጣ ተባለ፡፡ አንድ እንደጓሳ ሳር የጠነከረ “ኤንትሬ” የጭነት መኪና ተገዛ፡፡ በጎች ተደማምረው “ኤንትሬ” ሆኑ፡፡ አካባቢው የሚታወቅበትን ዝተትና ቂቤን እንደልቡ ማጓጓዝ ቻለ፡፡ ወደ አጎራባች አገሮች፡፡ በኤንትሬው፡፡

ደግሞ በሌላ ጊዜ ወደ አካባቢው የሚመጡ አውቶብሶች ሲሻቸው ዋጋ እየጨመሩ፣ ሲላቸው አንሄድም እያሉ ተሳፋሪውን አንገላቱት፡፡ የጓሳ ሕዝብ ተቀየመ፡፡ “መላ ምታ” ተባለ፡፡ እንደተለመደው በግ አዋጣ ተባለ፡፡ በጎች ተደምረው “ካቻማሊ” ሆኑ፡፡ አራት ምን የመሳሰሉ ፈጣን ካቻማሊዎች ተገዙ፡፡ አሁን ታድያ የጓሳ መንዝ ሕዝብ ያለው እየከፈለ የሌለው እየተመዘገበ በካቻማሊው ሽር ይላል፡፡ የአካባቢው ሰዎች ተመኩ፤ በጓሳ አውቶብሶች፡፡ በማኅበረሰባቸው፡፡

የጓሳ ብርቅዬዎች

111 የወፍ ዝርያዎች በጓሳ ይገኛሉ፡፡ አልተሳሳትኩም፤ አንድ መቶ አስራ አንድ። በጠቅላላው በኢትዮጵያ ከሚገኙት 861 የወፍ ዝርያዎች ታድያ 12 ከመቶ የሚሆኑት መገኛቸው ጓሳ-መንዝ ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ብርቅዬ አእዋፋት ውስጥ 45 በመቶ ያህሉ የሚገኙት ጓሳ ነው፡፡ በቁጥር 14 የሚሆኑ በአገራችን ብቻ የሚገኙ ወፎች መኖርያቸው ጓሳ ነው፡፡ በተለይም አንኮበር ዘረበል ወፍ (Ankober Serin Serinus) እና ደረተ ነጠብጣብ ኩሊሊት (Spot breasted Plover) የተባሉት በምድራችን ላይ በመጥፋት አደጋ ላይ ናቸው ከሚባሉት ውስጥ የሚመደቡት አእዋፋት መገኛቸው ጓሳ ብቻ ነው፡፡

ከዚህም ባሻገር ከሰሜናዊ ዋልታና ከአፍሪካ በአየር ንብረትና በወቅቶች መፈራረቅ የሚሰደዱ 38 የሚሆኑ አእዋፋት መናኸሪያ ናት፤ ጓሳ፡፡

በኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች ብቻ መገኛውን ያደረገው ጭላዳ ዝንጀሮ (gelada baboon) ከሰሜን ተራራዎች ቀጥሎ ሌላ መገኛው በጓሳ-መንዝ ነው፡፡ ቁጥሩ ከ 500 እስከ 1400 ይደርሳል የሚሉ ጥናቶች አሉ፡፡ በጓሳ የሚገኙት የጭላዳ ዝንጀሮዎች “ባለደም ልብ (bleeding hearts)” የሚባሉት መሆናቸው በጎብኚዎች ተመራጭና ብርቅዬ ያደርጋቸዋል፡፡ ደረታቸው ላይ ባለው የልብ ቅርጽ ያለው ቀይ ቆዳ የተነሳ “ባለደም/የሚደማ ልብ” የሚለው ስያሜ ተሰጥቷቸዋል።

የጭላዳ ዝንጀሮዎቸ አኗኗር በራሱ መሳጭ ገፅታ አለው፡፡ እስከ አራት የሚጠጉ ወንዶችና እስከ አስር የሚጠጉ ሴቶች እንዲሁም በእነርሱ ስር ያሉ ጥገኛ የቤተሰቡ አባላት በአንድ ላይ የመኖር ልምድ አላቸው፡፡ የቡድኑ ታላላቅ አባላት የቤተሰቡን አባላት ከማንኛውም ጥቃት የመጠበቅ ኃላፊነት አለባቸው፡፡ የጓሳ ሳርን እንደ ሰው እጭድ እያደረጉ ሲቅሙት በቅርብ ማየት ልዩ ስሜትን ይፈጥራል፡፡

የጓሳ ብርድና የደብረ ብርሃን ብርድ ልብስ

የጓሳ ብርድ አይጣል ነው፡፡ በተለይ የሌሊቱን የጓሳ ቅዝቃዜ የሰሀራ በረሃ አይመልሰውም፡፡ በየዓመቱ መስከረም፣ ጥቅምትና ህዳር ጓሳ ከፍተኛ ብርዳማ ሌሊቶችን ታስተናግዳለች፡፡ ከዜሮ በታች እስከ 10 ዲግሪ ሴንትገሬድ ቅዝቃዜ ከሚመዘገብባቸው የኢትዮጵያ ጥቂት ከተሞች አንዱ ጓሳ-መንዝ ነው፡፡ የጓሳ ተራሮች ቀን ቀን በውብ ጥጥ መሰል ጭጋግ ይጋረዳሉ፡፡ ይሄኔ እጅግ አስገራሚ ዉበት ይፈጠራል፡፡ ምሽት ግን ፈረንጅን ምንጃርኛ የሚያስደንስ ብርድ ይነግሳል፡፡

የመንዝ ነዋሪዎች ይህንን የማይታመን ቅዝቃዜ ለመከላከል በሹራብ ላይ ጃኬት፣በጃኬት ላይ ኮት፣ በኮት ላይ ዝተት፣ በዝተት ላይ ካፖርት፣ በካፖርት ላይ ደብረብርሃን ብርድልብስን ደርበው ይንቀሳቀሳሉ፡፡ በአካበቢው ባለ ትምህርት ቤት መምህራኑም ተማሪዎቹም በብርድልብስ ተጀቡነው ነው የሚማማሩት፡፡ አንድ መንግስታዊ ቢሮ ቢገቡ ስራ አስኪያጁ በተሸከርካሪ ወንበር ውስጥ በብርድልብስ ራሱን ቀብሮ ያገኙታል፡፡ ለሰርግ ተጠርተው ቢሄዱ እድምተኞቹ በሚያማምሩ ባለቀለም የደብረ ብርሃን ብርድልብስ ተሸሞንሙነው ያገኟቸዋል፡፡

ጓሳ፡ የቀይ ቀበሮዎቹ ምቾት

ጓሳ ከባህር ጠለል በላይ ከ3200-3700 ከፍታ ላይ የረጋ ስፍራ ነው፡፡ ብርቅዬዎቹ ቀይ ቀበሮዎች ታድያ እንደጓሳ የሚመቻቸው ማረፍያ የላቸውም፡፡ ከዘመድ ወዳጅ ሊጠያየቁ በየምሽቱና ንጋት ላይ ከ4 እስከ 9 ቀበሮዎች ሆነው በቡድን ይንቀሳቀሳሉ፡፡ የሚያጠቃ ጦር ከመጣ በሚል ነው ሁልጊዜ በቡድን የሚንቀሳቀሱት፡፡

ጓሳ ግን ቤታቸው ናት፡፡ ቀይ ቀበሮዎች በጓሳ ብዙም ስጋት አይገባቸውም፡፡ማኅበረሰቡ እንደሚጠብቃቸው ጠንቅቀው የሚያውቁ ይመስላሉ፡፡ ለዚህም ነው መሸት ባለ ቁጥር በቀላሉ ቀይ ቀበሮን ማየት የሚቻለው፡፡

የአርሲ ከፍተኛ ተራራማ ቦታዎች፣ የሰሜን ተራራዎቸ፣ የባሌ ተራሮችና የጓሳ ፕላቶዎች ቀይ ቀበሮዎቻችን የሚገኙባቸው የአለማችን ብቸኛ ቦታዎች ናቸው፡፡ በነዚህ ስፍራዎች በጠቅላላው 500 የሚሆኑ ቀይ ቀበሮዎቸ ይኖራሉ፡፡ ከነዚህ ውስጥ ከ250 በላይ የሚገኙት በባሌ ተራሮች ነው፡፡ በጓሳ የሚገኙት የቀይ ቀበሮዎች ብዛት ግን 42-47 ቢሆን ነው፡፡

የሚገርመው ግን አንድ ቱሪስት ቀይ ቀበሮን የማየት ሰፊ እድል ያለው ከየትኛውም ቦታ ይልቅ በጓሳ-መንዝ ነው፡፡ ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ? ጓሳ ከየትኛውም የቱሪስት መዳረሻ በላይ ብርቅዬ አእዋፋትና እንሰሳትን ከሚያደናግጡ ነገሮች የተጠበቀች ናት፡፡ ማኅበረሰቡ ለዚህ ዋንኛው ተመስጋኝ ነው፡፡ በሸገር በየደቂቃው የሚደመጠው “ቅድሚያ ለእግረኛ” የሚለው አዋጅ ጓሳ ሲደርሱ እንዲህ ተቀይሮ ይገኛል፡፡ ቅድሚያ ለብርቅዬ እንሰሳት!

ቱሪስትና ጓሳ

ጓሳ-መንዝ 111 ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ስፋት አለው፡፡ ከመዲናችን ከግማሽ ቀን ባነሰ ይደረሳል፡፡ ለዚህ ድንቅ ስፍራ ብዙ የሚሉት ሶስተኛ ዲግሪያቸውን ለመስራት ከየዓለማቱ የሚመጡ ጥቂት የብዝሀ-ሕይወት ተመራማሪዎች ናቸው፡፡ አካባቢው ብዙ የተሰራበት አይደለም፡፡ በቱሪዝም አስጎብኚነት የሚሰሩ ባለሙያዎች ግን የባሌ ተራሮችንና የሰሜን ተራሮችን መተካት የሚችል ብቸኛው ስፍራ ጓሳ ነው ሲሉ በእርግጠኝነት ይናገራሉ፡፡ እኔ ይህንን ቦታ ለመጎብኘት በሄድኩባቸው ቀናት የቢቢሲ የዶክመንተሪ ቡድን በአካባቢው ለ15 ቀናት ቆይታ አድርጎ ዘጋቢ ፊልም በመስራት ላይ እንደነበረ ተመልክቻለሁ፡፡

የአገር ውስጥና የውጭ ሚዲያዎች ቦታውን በበቂ ሁኔታ ካስተዋወቁት ለኢትዮጵያ  አዲስ ላሊበላ እንደማግኘት ነው ይላሉ ቦታው ላይ ቅድመ-ጥናት ለማድረግ የተገኙ የአንድ አስጎብኚ ድርጅት ባለቤት፡፡ በተለይ ይህ አካባቢ ለቱሪስቶች ራስ ምታት ከሆኑት ተመጽዋች ሕጻናትን የመሳሰሉ ትእይንቶች የሌሉበት በመሆኑ፣ ከዋና ከተማ በቅርብ ርቀት መገኘቱና ማህበረሰብን መሰረት ባደረገ “ኢኮ-ቱሪዝም” ላይ የተመሰረተ በመሆኑ የባሌና የሰሜን ተራሮችን የቱሪስት ፍሰት የሚጋራ ስፍራ እንደሚሆን ግምታቸውን ረገጥ አድርገው ይናገራሉ፡፡ እስከ አሁንም የዘገየው ስላልተዘመረለት ብቻ ነው፡፡

በጓሳ ህልም የሚመስሉ የጎጆ ቤት ስብስቦችን ማየት ይቻላል፡፡ ወንድ ልጅ ጎጆ ሲወጣ በዚያው ግቢ ውስጥ ሌላ ጎጆ ይሠራል፡፡ የቤተሰቡ አባል ጎጆ በወጣ ቁጥር የቤቱ አጥር እየተለጠጠ ይሄዳል፡፡ ሕዝቡ የተሻለ መኖሪያ አያስፈልገውም ባይባልም ጎጆዎቹ በራሳቸው የቱሪስት መስህብ የመሆን አቅም አላቸው፡፡ የቤቶቹን አሰራሮች ተከትሎ ተመሳሳይ የቱሪስት ማረፍያ ሎጆችን መገንባት ከጓሳ ሕዝብ የሚጠበቅ ይሆናል፡፡ ለያውም በግ ሳይዋጣ፡፡

16 Responses to “ጓሳ – ያልተዘመረለት ተፈጥሮ”

  1. በጣም የሚያሳዝን እና የሚገርም ነገር ነው! ሌላ ምንም ማለት አይቻልም::
    እርግጠኛ ነኝ አቶ ነጋሶ የተሻለ ነገ ይመጣላቸዋል:: መለስ ስልጣን ሲለቅቅ (ሲለቅቁ)ፕሮፌሰር ፧ የተባበሩት መንግስታት አማካሪ ምናምን ምናምን ይሆናል አይደለ ተረቱ :)

  2. i’m really disappointed withdr.negasos monthly penstion money.the leading party tplf andhis cadres(kangaro make with him ridiculous game).how ot could be tha one who lead ethiopian for 5years on presdent..they decide 1197.60 it is less than 50€ very embarrassing judgement….those who make this!!!
    may god keep ethiopian for those tyrant administration

Leave a Reply

You must be to post a comment.

ማሃሙድ ጋ ጠብቂኝ! [ክፍል አንድ]

ስብሓት ‹‹ትኩሳት›› ብሎ በጠራው መጽሐፉ ጀርባ ላይ ምን አለ? “ወጣት ሁን” አለ፡፡ ቢመርህ ‹‹ሪቮሉሽን›› ታስነሳለህ፣ እጅግ ቢመርህ ራስህን ታጠፋለህ…፡፡ ለማንኛውም ወጣት ሁን፡፡ እኔ ግን እልኻለሁ፣ ወጣት መሆኑን ሁን፣ ነገር ግን ራስህን ከማጥፋትህ በፊት ፒያሳ ሂድ፤ ሐሳብህን ልትቀይር ትችላለህና፡፡ ለመሞትም ቢሆን የፒያሳን ያህል መልካም ሰፈር የለም፡፡ ቀባሪ አታጣም፤ በፒያሳ ሰው ባያይህ ማዘጋጃ ያይኻል፡፡ ለመሞትም ለመኖርም ስታስብ ፒያሳ ሂድ፡፡

ዝነኛው የመሐሙድ ሙዚቃ ቤት አካባቢ ምንጊዜም ሰው አያጣውም

(መሀመድ ሰልማን)

ስብሓት “ትኩሳት” ብሎ በጠራው መጽሐፉ ጀርባ ላይ ምን አለ? “ወጣት ሁን” አለ፡፡ ቢመርህ “ሪቮሉሽን” ታስነሳለህ፣ እጅግ ቢመርህ ራስህን ታጠፋለህ…፡፡ ለማንኛውም ወጣት ሁን፡፡ እኔ ግን እልኻለሁ፣ ወጣት መሆኑን ሁን፣ ነገር ግን ራስህን ከማጥፋትህ በፊት ፒያሳ ሂድ፤  ሐሳብህን ልትቀይር ትችላለህና፡፡ ለመሞትም ቢሆን የፒያሳን ያህል መልካም ሰፈር የለም፡፡ ቀባሪ አታጣም፤ በፒያሳ ሰው ባያይህ ማዘጋጃ ያይኻል፡፡ ለመሞትም ለመኖርም ስታስብ ፒያሳ ሂድ፡፡

ፒያሳን ለሞትም ቢሆን የምመርጥልህ ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ሞት ሞት የሚሸት ስም በድፍን አዲስ አበባ የምታገኘውም ፒያሳ ነው፡፡ “ዶሮ ማነቂያ” ና “እሪ በከንቱ”ን እንደናሙና ውሰድ፡፡ ‹‹ተረት ሰፈር››ም አንተን ተረት ለማድረግ በሚያስችሉ ሕይወቶች የተሞላ መንደር ነው፤ ተረት መሆን ከፈለግህ፡፡ ፒያሳ ሥጋን ብቻ ሳይሆን ነፍስን ለማጥፋት ጭምር ምርጥ ሰፈር ናት፡፡ ካላመንክ ሙትና ሞክረው፡፡ ነግቶ ሳይመሽ ማዘጋጃ ይቀብርኻል፡፡ ስራ ለማቅለል ከፈለክ ደግሞ እዚያው ማዘጋጃ በር ላይ ጠጋ ብለህ ራስህን መድፋት ትችላለህ፡፡

ፒያሳ ወደ ሕይወትም ልትመልስህ ትችላለች፡፡ “እንዴት?” በለኝ፡፡ ወጣት ነህና ስብሓት በመከረህ መሰረት ራስህን የማጥፋት መብትህን ለመጠቀም ወደ ፒያሳ መጣህ እንበል፡፡ የት ጋር መሞት እንዳለብህ ለመምረጥ በፒያሳ ዞር ዞር ስትል እመነኝ ልብ የምታጠፋ ቆንጆ ታያለህ፡፡ ፀጉሯ የሚዘናፈል፣ ዳሌዋ የሚደንስ፣ ጡቶቿ የሚስቁ… መኖር የምታስመኝ ቆንጆ ልቅም ያለች ውብ 13 ቁጥር አውቶብስ ስትጠብቅ ታያታለህ፡፡ በዚህን ጊዜ ልብህ ይሸፍትና አንተም የተፈጥሮ ሞትህን መጠበቅ እንዳለብህ ትረዳለኽ፡፡ ከዚያች ቅፅበት ጀምሮ የ13 ቁጥር አውቶብስ ቋሚ ደንበኛ ሆነህ ታርፈዋለህ፡፡ አውቶብስና ሞት በራሳቸው ሰዓት እስኪመጡ ትጠብቃለህ። ፒያሳ ወደ ሕይወት መለሰችህ ማለት አይደል?

የፒያሳ ካፌዎች

ፒያሳ አንድ ሺህ አንድ መቶ ካፌዎች ያሉባት ቅመም የሆነች ሰፈር ናት፡፡ አንድ ሺህ አንድ መቶ ቆንጆ ልጃገረዶች ደግሞ በካፌዎቿ ውስጥ ተኮልኩለው ኮካ በ‹‹ስትሮ›› ይጠጣሉ፡፡ ‹‹ስትሮ›› ምን እንደሆነ ካላወቅክ የፒያሳ ልጅ አይደለህም ማለት ነው፡፡ ‹‹ስትሮ›› በቆንጆ ልጅ ከንፈርና በቆንጆ ብርጭቆ መሀል የተሰራ የላስቲክ ድልድይ ነው፡፡

ፒያሳ በካፌ ብዛት “ከምስራቅ አፍሪካ አንደኛ ናት፡፡” የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ነው እንዲህ ያለው ይባላል፡፡ እንደ ፒያሳ በካፌ የተጥለቀለቀ ሰፈር ከየት ይገኛል?! ከአምፒር እስከ ራስ መኮንን ድልድይ ብቻ በግራና በቀኝ የተሰለፉ ከ53 በላይ ካፌዎችን ልቆጥርልህ እችላለሁ፡፡ በእርግጥ ቆንጆ ልጃገረዶችና ወርቅ ቤቶች በመሀል በመሀል እየገቡ ቆጠራዬን አስተጓጉለዉት ይሆናል፡፡ ሆኖም ቁጥራቸው ከዚህ ቢልቅ እንጂ አያንስም፡፡

የፒያሳ ካፌዎች ልዩ ገፅታ ሁልጊዜ ሙሉ መሆናቸው ነው፡፡ አንዳንድ የፒያሳ ምሁራን ይህንን ጉዳይ ከመንግሥት የትምህርት ፖሊሲ ጋር ሊያይዙት ይሞክራሉ፡፡ እኔ ግን እላለሁ፤ ይህ የፒያሳ ልዩ ከራማ እንጂ ሌላ ምንም ሊሆን አይችልም፡፡

በፒያሳ ምርጥ ቡና ጠጥተህ ቀንህን ብሩህ ለማድረግ ካሻህ እነማንኪራ፣ እነ አፍሪካ፣ እነ ቶሞካ አሉልህ…፡፡ ቆንጆ ሻይ ከቆንጆ ልጃገረዶች ጋር ተፋጠህ ፉት ለማለት ካሻህ እነ ናምሩድ፣ እነ ራዜል፣ እነ ኢቪያን፣ እነ ሳሬም፣ እነ ኦስሎ፣ እነ አፕቪው፣ እነ ዲጄስ፣ እነ ሃርድኮር፣ እነ ጉድታይምስ አሉልህ፡፡ በተለይ በቅርቡ የተከፈተው ጉድ ታይምስ እንደ ደብልፌስ ጃኬት አይነት ተፈጥሮ ነበረው፡፡ ቀን ላይ ውብ ካፌ ኾኖ ይቆይና ማታ ላይ በፍጥነት ራሱን ቀይሮ ውብ ባር የመሆን ልዩ ጥበብ ነበረው፡፡ የጨርቆስ ልጆች ያለ ሰፈራቸው መጥተው በቡዳ በሉት መሰለኝ ሰሞኑን ተቃጠለ አሉ፡፡ ነፍስ ይማር!

ፎቅ ላይ ቂብ ብለህ ፒያሳንና ዜጎቿን ቁልቁል እየገረመምካቸው ለመዝናናት ካሻህ አራዳ ላይ የተሰቀሉ  መዝናኛዎች አሉልህ፡፡ እነ አራዳ፣ እነ ሲድኒ፣ እነ ትዊንስ፣ እነ ቤስት በፒያሳ ከባህር ጠለል በላይ በምናምን ሺህ ጫማ ከፍታ የሚገኙ ካፌዎች ናቸው፡፡ አለልህ ደግሞ እንደ ዳሎል ተቀብሮ ያለ ካፌ፡፡ ቼንትሮ ይሰኛል፡፡

ልምከርህ! ፍቅረኛህ ፒዛ አማረኝ ካለችህ ፒያሳ ‹‹ፒዛ ኮርነር›› ውሰዳት፤ ከዚያ በኋላ ምን አለ በለኝ ፍቅሯ ካልጨመረ፡፡ ከዚህ ግብዣ በኋላ ካኮረፈችህ ግን ፒዛውን በልተህባታል ማለት ነው፡፡

ፒያሳ የኬክ አገር ናት፡፡ ዕድሜ ጠገቦቹን ….በዚህ አጋጣሚ ስማቸውን ማውሳት ግድ ይላል፡፡ በተለይ የ‹‹ኤንሪኮ›› ኬክ ይምጣብኝ፡፡ እስኪ በሞቴ ከዚህ ቤት ሂድና ኬክ እዘዝ፡፡ ኪኒን ኪኒን የሚያካክሉ ኬኮች ይቀርቡልኻል፡፡ የፒያሳ ልጅ ካልኾንክ ታኮርፋለህ፡፡ አንተ የለመድከው ድፎ ዳቦ የሚያካክሉ ኬኮችን ነዋ፡፡ እስኪ በሞቴ ቅመሰው፡፡ ከዚያ በአድናቆት ጭንቅላትህን ትወዘውዘዋለህ፡፡ ካልጣመህ ግን በኬክ አላደክም ማለት ነው፡፡ሂድና ሸዋ ዳቦ ተሰለፍ፡፡

ኤንሪኮ ውስጥ ዞር ዞር ብለህ ከጎንህ ያለውን ሰውዬ ገልመጥ ለማድረግ ሞክር፡፡ የሆነ ሰውዬ በትኩረት ኬክ ሲበላ ታየዋለህ፡፡ በእርግጠኝነት ስለሰውየው ብትጠይቅ ከተማዋ ውስጥ ካየኻቸው ሰማይ ጠቀስ ፎቆች የአንዱ ባለቤት ሆኖ ታገኘዋለህ፡፡ ፎቅ ባይኖረው እንኳ ፎቅ የሚሰራ ብር ያለው ለመሆኑ አትጠራጠር፡፡ ይህም ባይኖረው አንድ ቀን የማግኘት ተስፋ ያለው ነው። የኤንሪኮ የውስጥ ገፅታ አለመብለጭለጭ ተራ ቤት እንደሆነ ሊያስገምትህ ይችላል፡፡ አንድ ነገር ግን ላረጋግጥልህ፣ ይህ ቤት የሞጃዎች መናኸሪያ ነው፡፡ ስለዚህ አትንቀዥቀዥ፡፡

ከኤንሪኮ በኬክ መጋገር ጥበብ ተደንቀህ ስትወጣ ከፊት ለፊትህ የምታገኘው ‹‹እናት ህንፃ››ን ይሆናል፡፡ ይህ ህንጻ በቅርቡ ፒያሳን ከተቀላቀሉ ድንቅ ፎቆች አንዱና ዋንኛው ነው፡፡ በስነ -ህንፃ ታሪክ በምስራቅ አፍሪካ አንደኛ ከመሆኑም በላይ የሚመስለው የለም እየተባለ ነው፡፡ የፒያሳ ልጅ ካልኾንክ ይህን ህንፃ ተደግፈህ ፎቶ ብትነሳና ክፍለ ሀገር ላሉ ዘመዶችህ ብትልክላቸው ልጃችን አሜሪካ ገባ ብለው ድግስ እንደሚደግሱ አትጠራጠር፡፡ አዲስ አበባ ውብ ሕንጻ እንደሌለ የሚያስቡ ዲያስፖራዎችም ቢሆኑ እነሱ በማያውቁት አንድ የአውሮፓ ከተማ ያለ ሊመስላቸው ይችላል። (ካላመንከኝ ፎቶውን ተመልከት)

ማሃሙድ ጋ ጠብቂኝ!

አይበለውና ፒያሳ ሳለህ ድንገት ስሜትህ ቢመጣ እንደኔ የጨዋ ልጅ ከሆንክ ስልክህን በርበር አድርገህ ትደውልና እጩ ፍቅረኛህን “ማሃሙድ ጋ ጠብቂኝ” ትላታለህ፡፡ “ኢንተር ላንጋኖ” ወስደህ፣ በድብቆቹ የስሞሽ ግርዶሽ ተጠልለህ፣ ልብ የሚሰልብ የስሞሽ ስነ ስርዓት ትፈፅማለህ፡፡ ከ”ማህሙድ ሙዚቃ ቤት” እስከ “ኢንተር ላንጋኖ” ለመሄድ የሦስት ደቂቃ ትእግስት ካጣኽ ፒያሳ ውላ ትግባ እንጂ ምን ጠፍቶ! በ”አምፒር” ወደ “ዶሮ ማነቂያ” ገባ እንዳልክ “ትሬይን ሀውስ” አለልህ፡፡ ይህ ቤት መሳሳሚያ ብቻ አይደለም ያዘጋጀልህ፡፡ አይበለውና ስሜትህ ከንፈር ብቻ የማያስታግሰው ከሆነብህ ይህ ቤት እጥር ምጥን ያለ ክፍል እጥር ምጥን ላለ ሰዓት ያከራይኻል፡፡ ፒያሳ ነው ያለኸው፡፡ ብታምነኝም ባታምነኝም ፒያሳ ከ10 በላይ መሳሳሚያ ቤቶችን በጉያዋ ይዛለች፡፡ ብዙዎቹ ስም አልባ ናቸው፡፡ ልብህ ከሚቆም አንድ አምስቱን ልጠቁምህ (ሊሞት የመጣን ሰው ወደ ሕይወት ለመመለስ አምስት መሳሳሚያ መቼ አነሰው?)፤ “ኢንተር ላንጋኖ”፣ “ትሬይን ሃውስ”፣ “ቢግ ትሪ”፣ “ጊቤ”፣ “ቬሮኒካ”…

“ማህሙድ ጋ” ቀጠሮ መያዝ እጅግ የሚመከር እንደሆነ በዚህ አጋጣሚ ሳልነግርህ አላልፍም፡፡ “ለምን?” በለኝ፡፡ አንደኛ ከማህሙድ ሙዚቃ ቤት የሚለቀቁ የማህሙድ ትዝታዎች በቀጠሮ ያስደገፈችህን ልጂትና ያደረሰችብህን ብስጭት የማስታገስ ኀይል አላቸው፡፡ አንዳንዴ ደግሞ የማህሙድ ወዳጅ የነበረው ጥላሁን ‹‹ቀጠሮ ይከበር›› ሲል ያንጎራጎረውን ዜማ ሊከፍቱልህ ይችላሉ፡፡ ሁለተኛ ‹‹ማሃሙድ ጋ›› አስተውለህ ከሆነ ብዙ ቆነጃጅት ብዙ ኮበሌዎችን ቆመው የሚጠብቁበት ስፍራ ነው፡፡ ዕድለኛ ከሆንክ ፍቅረኛዋ ቀርቶባት የተበሳጨችን ልጃገረድ ይዘህ እብስ ልትል ትችላለህ፡፡

ቀጠሮ ቦታ ሴቶች ቢያንስ ሰላሳ ደቂቃ አርፍደው እንደሚገኙ ሳታስተውል አልቀረህም፡፡ ማህሙድ ጋ ግን ለምን እንደሆነ ባላውቅም አረፈዱ ቢባል 20 ደቂቃ ነው፡፡ ቢያረፍዱብህም ከፊት ለፊትህ ብዙ የሚታይና የሚያዘናጋ ነገር አታጣም፡፡ ምሳሌ ለመጥቀስ ያህል ትልቁ የሀገራችን የህዝብ ሽንት ቤት የሚገኘው “ማህሙድ ሙዚቃ ቤት” ማዶ ነው፡፡ በቀን ሦስት ሺህ ሰዎች ይሳለሙታል፡፡ ሽንታቸው እንዳያመልጣቸው የሰጉ አዛውንት ምንትሳቸውን በእጃቸው ደግፈው ወደዚህ ሽንት ቤት እየተወላገዱ ሲገቡ እያየህ መሳቅ ትችላለህ፡፡ ከፈለክ “ሰው የተፈጥሮን ጥሪ ለመመለስ እንደሚጣደፈው ለቀጠሮም ምን አለ ተመሳሳይ ጥድፊያ ቢያሳይ” እያልክ ትፈላሰፋለህ፡፡

ሽንት ያጣደፋቸውን ምእመናን ማየት ከሰለቸህ ቀና በል፡፡ አይንህ ከሕዝብ ሽንት ቤት ወደ ሕዝብ ሶኒክ ስክሪን ይወረወራል፡፡ ፒያሳ በቅርቡ ራሷን ከእህት ከተሞች ጋር ለማስተካከል ያስተከለችው ይህ ትልቅ ዲጂታል ስክሪን የማያሳይህ ነገር የለም፡፡ ከቶሚና ጄሪ አባሮሽ ጀምሮ እስከ ሕገ መንግሥቱ አንቀጾች ይተነትንልኻል፡፡ ሕገ መንግሥቱ የብሔር ብሔረሰቦችን እኩልነት እንዴት እንዳስከበረ ካልገባህ አንቀጽ በአንቀጽ ያስረዳኻል፤ ትንሽ ከቆየህም የሴቶች እኩልነት በአገራችን በአያሌው እየሰፈነ እንደሆነ ያሳይኻል፤  ይሄኔ ከሴት ጓደኛህ ጋር የያዝከው ቀጠሮህ ትዝ ይልኻል፡፡ ሶኒክ ስክሪኑ ላይ በሚታየው የሕገ መንግስቱ አንቀጽ ውስጥ እንዲህ የሚል ነገር እንዲካተትልህ ትመኛለህ፡፡ ‹‹የሴቶች እኩልነት ቀጠሮ በማክበርም ጭምር ይረጋገጥ።››

አይንህን ከሶኒክ ስክሪኑ ስትነቅል የቀጠርካት ልጅ አበባ መስላ ከተፍ ትላለች፡፡ ጉንጮችህን ሳም ሳም፣ እቅፍ እቅፍ ስታደርግህ ንዴትህ ድራሹኑ ይጠፋል፡፡ ጭራሽ ቀጠሮ ማርፈዷ ተዘንግቶህ አንተው ራስህ “አረፈድኩብሽ አይደል” ልትል ይቃጣኻል፡፡ ፒያሳ! (ክፍል ሁለት ይቀጥላል)

9 Responses to “ማሃሙድ ጋ ጠብቂኝ! [ክፍል አንድ]”

  1. በጣም የሚያሳዝን እና የሚገርም ነገር ነው! ሌላ ምንም ማለት አይቻልም::
    እርግጠኛ ነኝ አቶ ነጋሶ የተሻለ ነገ ይመጣላቸዋል:: መለስ ስልጣን ሲለቅቅ (ሲለቅቁ)ፕሮፌሰር ፧ የተባበሩት መንግስታት አማካሪ ምናምን ምናምን ይሆናል አይደለ ተረቱ :)

  2. i’m really disappointed withdr.negasos monthly penstion money.the leading party tplf andhis cadres(kangaro make with him ridiculous game).how ot could be tha one who lead ethiopian for 5years on presdent..they decide 1197.60 it is less than 50€ very embarrassing judgement….those who make this!!!
    may god keep ethiopian for those tyrant administration

Leave a Reply

You must be to post a comment.

መጽሐፍ አሳታሚዎች እና ደራስያን ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ገብተዋል

በአገሪቱ እውቀት እንዲስፋፋ ከተፈለገ በኅትመት ኢንዱስትሪ ላይ የሚታዩት የዋጋ ጭማሪዎች ላይ ትኩረት ማድረግ ይኖርበታል የሚል አቋም አለው። በትምህርት ላይ ለውጥ ለማምጣት ከተፈለገ የመንግሥት ርምጃም አፋጣኝ ሊኾን ይገባዋል ብሎም ያስባል። መንግሥት በእንዲህ ዐይነቱ ዐይን ያወጣ ትርፍ የማጋበስ ሥራ ላይ ዝምታን የሚመርጥ ከኾነ በሌላ ቋንቋ የንባብ ባህል እንዳይዳብር እና እውቀት እንዳይስፋፋ የሚያስችል ፖሊስ ቀርጾ በሥራ ላይ እያዋለ ነው ሊያስብለው ይችላል

(ይርጋ ተሻለ)

ከሳምንታት በፊት በኢትዮጵያ በተከሰተው የውጭ ምንዛሪ ንረት ምክንያት ወረቀት አስመጪዎች እና ማተሚያ ቤቶች ከምንዛሪው ጭማሪ በፊት ከነበረው ዋጋ ከ40 ከመቶ በላይ ጨምረዋል።

ይህ የዋጋ ጭማሪ ያስደነገጣቸው በርካታ የመጻሕፍት አሳታሚዎች መጻሕፍትን ከማሳተም እየታቀቡ እንደኾነ ለአዲስ ነገር ገልጸዋል። እንዲያውም አንዳንድ ማተሚያ ቤቶች ለኅትመት ያስከፍሉ ከነበረው ዋጋ እስከ 80 በመቶ ጭማሪ በማድረግ ላይ ናቸው። አዲስ ነገር ያነጋገራቸው የመጻሕፍት አሳታሚዎች ባለፉት የክረምት ወራት ውስጥ አዳዲስ ወጥ ልብ ወለዶች፣ የትርጉም ሥራዎች፣ የሥነ- ልቡና እና የትምህርት አጋዥ መጻሕፍትን ለኅትመት ሲያበቁ ምንም ዐይነት የወረቀት ዋጋ መዋዠቅ እንዳልነበር እና እንደ አሁኑ እንዳላስደነገጣቸው ገልጸዋል። ይኹንና ከውጭ ምንዛሪው ንረት በኋላ ማተሚያ ቤቶች የኅትመት ዋጋውን በመስቀላቸው አሳታሚዎቹ አዳዲስ መጻሕፍትን ማሳተሙን “ዋጋ እስኪረጋጋ” በሚል ምክንያት ለጊዜው ገትተውታል።

ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ አሳታሚ ይህን የውጭ ምንዛሬ ንረት ተንተርሰው የኅትመት ዋጋው በተለያየ መንገድ እና የዋጋ ስሌት እንዲጨምር ያደረጉት የማተሚያ ቤቶች ብቻቸውን ሊፈረድባቸው እንደማይገባ ይናገራሉ። እንደ እርሳቸው አስተያየት ከኾነ የችግሩ ዋነኛ ምንጮች የወረቀት አስመጭዎቹ ናቸው። የወረቀት አስመጭዎቹ የውጭ ምንዛሬው ከጨመረው የ20 በመቶ ጭማሪ በእጥፍ መጨመራቸው ምክንያት አንባቢው ወደ መጻሕፍት ራሱን እንዳይመልስ ለማድረግ እየተዘጋጁ ነው ሲሉ ይገልጻሉ። መንግሥትም በዚህ ንግድ ዙርያ ያለውን ዐይን ያወጣ ትርፍ የማጋበስ አካሄድ በያዙት ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እና ክትትል አለማድረጉ እንዳስገረማቸው ነው የሚናገሩት።

ባለፉት ጊዜያት አምስት የትምህርት እና የቋንቋ አጋዥ መጻሕፍትን ለኅትመት ያበቃው የ43 ዓመቱ ሌላኛው ስሙ እንዳይጠቀስ የሚሻ የመርጃ መጻሕፍት አዘጋጅ በቅርቡ በኅትመት ላይ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ ግን ማመን ከሚችለውም በላይ አስደንግጦታል። ይህን መገረሙን የሚገልጸው ያለፈውን ልምዱን ከአሁኑ ጋራ እያነጻጸረ እና በምሳሌ እያስረዳ ነው። “ብዛቱ 3 ሺሕ ለኾነ፤ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችን ለዘለቄታው የሚያግዝ ባለ 380 ገጽ መጽሐፍ ለማሳተም 87 ሺሕ ብር እንድከፍል ተጠየቅኹ። አንዱን መጽሐፍ በ29 ብር ሂሳብ ማለት ነው። ነገር ግን ከዚሁ መጽሐፍ ጋራ ተቀራራቢ የኾነ ሌላ መጽሐፍ ከዚህ በፊት ያሳተምኹት በ16 ብር ነበር።” ይላል። ለዚሁ የመርጃ መጽሐፍ አዘጋጅ በመጀመርያ ደረጃ ተወቃሹ መንግሥት ነው። በአገሪቱ እውቀት እንዲስፋፋ ከተፈለገ በኅትመት ኢንዱስትሪ ላይ የሚታዩት የዋጋ ጭማሪዎች ላይ ትኩረት ማድረግ ይኖርበታል የሚል አቋም አለው። በትምህርት ላይ ለውጥ ለማምጣት ከተፈለገ የመንግሥት ርምጃም አፋጣኝ ሊኾን ይገባዋል ብሎም ያስባል። መንግሥት በእንዲህ ዐይነቱ ዐይን ያወጣ ትርፍ የማጋበስ ሥራ ላይ ዝምታን የሚመርጥ ከኾነ በሌላ ቋንቋ የንባብ ባህል እንዳይዳብር እና እውቀት እንዳይስፋፋ የሚያስችል ፖሊስ ቀርጾ በሥራ ላይ እያዋለ ነው ሊያስብለው ይችላል ሲል ይገልጻል።

አሳታሚዎቹ እና ደራስያኑ በየጊዜው ከ3 ሺሕ እስከ 5 ሺሕ አንዳንድ ጊዜም እስከ 10 ሺሕ የሚደርስ ብዛት ያላቸው መጻሕፍትን ለማሳተም ጥያቄ ባቀረቡ ቁጥር በተደጋጋሚ ማተሚያ ቤቶቹ የወረቀት እጥረት እንዳለባቸው እንደሚነግሯቸው ያወሳሉ። አሁን ግን ነገሩ ከወረቀት እጥረት ወደ ዋጋ ንረት ተለውጧል። በትንሹ በ9 ብር ይታተም የነበረ ባለ 220 ገጽ መጽሐፍ 16 ብር እና ከዚያ በላይ ብር እንዲከፍል እየተጠየቀበት ነው። ይህ አካሄድ በኣሳታሚዎችም ኾነ በደራስያኑ ላይ ምሬትን እያሳደረ ነው። በአገሪቱ ያሉት አምስት ያህል ወረቀት አስመጭዎች ወረቀት እየቆጠቡ ማስወደድን እንደ ዋነኛ ግብ አድርገው እየተንቀሳቀሱ ነው የሚል አስተያየት የሚሰጡት አሳታሚዎቹ ተወቃሾቹ እነርሱ እና መንግሥት ናቸው ሲሉ ለአዲስ ነገር ገልጸዋል። አንድ አሳታሚ እንደ “አልሳም” እና “ጥቁር ዐባይ” ያሉ ወረቀት አስመጭዎች ሌሎቹን ሦስት አስመጭዎች ጨምሮ “ወረቀት በመጋዘን ደብቀው የዋጋ ንረት ጫዎታ እየተጫወቱ ነው” ሲሉ ይከሷቸዋል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

የአገር ቤት ጋዜጦች ምን ጻፉ?

የዚህ ሳምንት የአገር ቤት ጋዜጦች እና መጽሔቶች “ብርቱካናማ” ኾነው ሰንብተዋል። ደብዝዞ የነበረው የጋዜጦች ገበያም ድንገተኛ የኾነ መነቃቃት ዐሳይቷል። ዕድሜ ለብርቱካን! ለምሳሌ አውራምባ ታይምስ ቀድሞ ያሳትመው ከነበረው የጋዜጣ ቁጥር የሦስት ሺሕ ኮፒ ጭማሪ አድርጓል። የወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ከእስር መፈታት እና በመንግሥት ሚዲያ የሰጠችው ቃል በእስሯ ዋዜማ ላይ ከጻፈችው “ቃሌ” ጽሑፍ ጋራ እየተመዘነ፣ እየተመነዘረ፣ ተተንትኗል፣ ተበትኗል። የአገር [...]

የዚህ ሳምንት የአገር ቤት ጋዜጦች እና መጽሔቶች “ብርቱካናማ” ኾነው ሰንብተዋል። ደብዝዞ የነበረው የጋዜጦች ገበያም ድንገተኛ የኾነ መነቃቃት ዐሳይቷል። ዕድሜ ለብርቱካን! ለምሳሌ አውራምባ ታይምስ ቀድሞ ያሳትመው ከነበረው የጋዜጣ ቁጥር የሦስት ሺሕ ኮፒ ጭማሪ አድርጓል።

የወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ከእስር መፈታት እና በመንግሥት ሚዲያ የሰጠችው ቃል በእስሯ ዋዜማ ላይ ከጻፈችው “ቃሌ” ጽሑፍ ጋራ እየተመዘነ፣ እየተመነዘረ፣ ተተንትኗል፣ ተበትኗል። የአገር ቤት ጋዜጦች የብርቱካንን ጉዳይ መነካካት የጀመሩት ከመፈታቷ ከቀናት በፊት ነበር። ከትንታኔያቸው መረዳት የሚቻለው መረጃውን ቀድመው እንዳገኙት ነው።

ዘወትር ማክሰኞ የሚታተመው አዲስ ፕሬስ ጋዜጣ በብርቱካን ጉዳይ ላይ በሚጽፏቸው ጠንካራ ትንተናዎች የሚታወቁትን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲውን ዶክተር ዳኛቸውን በሰፊ ቃለ ምልልስ እንግዳው አድርጓቸው ነበር። ይህ የኾነው ብርቱካን ከመፈታቷ አንድ ቀደም ብሎ ነው። ዶክተሩ የገዥው ፓርቲ ዓላማ ሲተነትኑ “ብርቱካንን እንደ ግለሰብ (ማደብዘዝ) ሳይኾን ብርቱካናዊውን መንፈስ መጨፍለቅ ነው” በማለት ነበር ትንታኔያቸውን የጀመሩት።

ዶክተሩ በቃለ ምልልሳቸው የሚሰጧቸው ማስረጃዎች እና ምሳሌዎች ዘና ያደርጋሉ። ብርቱካንን ሲገልጹ በኢራቁ ወረራ ጊዜ የቡሽን የወረራ ዕቅድ አሻፈረኝ ካሉት የፈረንሳዩን ዣክ ሺራክ ጋራ እያነጻጸሩ ነበር። ዣክ ሺራክ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ የአገራቸው አቀንቃኞች “the man who said No” የሚል ዜማን እንዳቀነቀኑላቸው አስታውሰው፣ ብሩቴ ደግሞ ለእኔ ይላሉ ዶክተሩ “the woman who said No” ናት ሲሉ ያሞካሿታል።  ዶክተሩ ብርቱካን መታሰሯ ፖለቲካውን ጎድቶታል በሚለው ነጥብ ላይ ሲሞግቱ ሐሳባቸውን በምሳሌ እንዲህ ያብራራሉ።

“ኬኔያ ኀይሌን እና ቀነኒሳን ለውድድር ልከህ እንደነገ ሊሮጡ፤ ከሰዓት በኋላ መብራት ጥሰዋል ብሎ የኬኒያ ፖሊስ እስር ቤት ያስገባቸዋል። …እኔ ምን ተጠቀምኩ እነርሱን በማሰሬ መብራት ስለጣሱ ነው ይባላል እንዴ? ነገ ጠዋት ውድድር እያለ!?…ቡርቱካንን በማሰራቸው ምን ተጠቀምን ይላሉ። …እንዴ እንክት አድርገው ነው የተጠቀሙት።”

ስለ ብርቱካን የእስር ቤት አያያዝን ዶክተሩ የገዥውን ፓርቲ ዘዴ ከቀድሞ ነገሥታት ጋራ ያመሳስሉታል። ነገሥታቱ ተቀናቃኝ ናቸው ብለው ያሰቧቸውን ልዑላንን፣ መሳፍንቶችን እና የጦር አበጋዞችን የተገለለ ዐምባ ውስጥ እንደሚያስሯቸው ሁሉ ብርቱካንንም በትልቅ እስር ቤት ውስጥ ትንሽ አምባ ፈጥረው (አኖሯት)።  ዓላማቸው ደግሞ የአይበገሬነት መንፈሷን ሰብረው ብርቱካናዊ መንፈስን ከኅብረተሰቡ መፋቅ ነው” ሲሉ ነጥባቸውን ያሳርጋሉ።

ኢትዮጵያ በትምህርት ጥራት ከሶማልያ ጋራ ተስተካከለች

አዲስ ፕሬስ ጋዜጣ “ግሎባል ካምፔይን ፎር ኤጁኬሽን” ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ የጻፈው አስደንጋጭም አስገራሚም ዜና ነው። በዚህ ድርጅት መረጃ መሠረት ላይ የተንተራሰው ይኸው ጋዜጣ ኢትዮጵያ ከሶማልያ እኩል ደረጃ ላይ ተቀምጣለች ሲል ዘግቧል፤ በትምህርት ጥራት። ጋዜጣው በዚሁ ዜና ላይ “በትምህርት ጥራት ቀውስ ውስጥ ከመደባቸው የመጨረሻዎቹ አገራት ውስጥ አራቱ በአፍሪካ የሚገኙ ሲኾን ሦስቱ ደግሞ በምሥራቅ አፍሪካ ውስጥ ይገኛሉ። በደረጃው መጨረሻ የተካተቱት ሦስቱን አገራት በመዘርዘር ጋዜጣው መርዶውን ያጠቃልላል። “ኤርትራ፣ ሶማልያ እና ኢትዮጵያ።”

ዐሥራ ሦስት ኢትዮጵያውያን በኤደን ባህረ ሰላጤ ሕይወታቸው አለፈ

ሰማንያ አምስት ሰዎችን አሳፍሮ የኤደን ባህረ ሰላጤን በማቋረጥ ላይ የነበረው ጀልባ ሰጠመ። ተሳፋሪዎቹ 85 ነበሩ። የሚገርመው 75ቱ ኢትዮጵያውን ሲኾኑ ቀሪዎቹ ሶማልያውያን ናቸው። እንደ ጋዜጣው ዘገባ የብዙዎቹን ሕይወት ከሕልፈት የታደጉት እና ያዳኑት በአቅራቢያው የነበሩ የአሜሪካ የባሕር ኀይል አባላት ናቸው።

ፀረ ብርቱካን ዘገባዎች “በዳጉ ኢትዮጵያ”

የመንግሥትን አቋም ጫን አድርገው የነጻ ሚዲያ ባንዲራን እያውለበለቡ ከሚዘግቡ ጋዜጦች አንዱ “ዳጉ ኢትዮጵያ” እንደኾነ ይወራል፤ ይነገራል። ዳጉ በቅዳሜ ዕትሙ ከአዲስ ዘመን የኮረጃቸው የሚመስሉ ዘገባዎችን ይዞ ወጥቷል። ለምሳሌ በፊት ገጹ በጻፈው አንድ ዜና ላይ እንዲህ ሲል ይጀምራል። “አንዳንድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ሕግም ተከበረ፤ ብርቱካንም ተፈታች” ሲሉ ገለጹ።”

ይኸው ጋዜጣ “የወይዘሪት ብርቱካን ሁለት ዓመት ዘግይቶ የተጻፈ ደብዳቤ” በሚል ርእስ የብርቱካንን “ዘግይቶ ሕዝብን እና መንግሥትን ይቅርታ መጠየቅ” በተመለከተ ሰፊ ጽሑፍ አስተናግዷል። የዚህን ጽሑፍ ጭብጥ ራሱኑ በካርቱን ሥዕል በውስጥ ገጹ ደግሞታል። በ“ሴትዮዋ” መፈታት እና “ይቅርታ” እጅጉን ለመሳለቅ ሞክሯል።  “ስዊድን ገንዘብ ለማሰባሰብ ነበር የሄደችው፤ በሞቅታ ዳይስፖራው መስማት የሚፈልገውን ነጠላ ዜማ ለቀቀች…።” እያለ በስላቅ የተሞላ ትንታኔን ይሰጣል። ሲቀጥልም “ገና ከስዊድን መጥታ የኢትዮጵያን አፈር እንደረገጠች ከቦሌ ወደ ቃሊቲ በቀለበት መንገድ አድርጎ መውሰድ ይችል የነበረው መንግሥታችን ለስላሳውን መንገድ እንደመረጠ ተከታትለን የነበረው ነው።” ሲል የመንግሥትን ብስለት ለማጉላት ይታትራል። ጽሑፉን ምንግሥትን ለማስደሰት ኾነ ብሎ የተጻፈ ለመኾኑ ምንም ዐይነት ማረጋገጫ መጥቀስ አያስፈልግም። አጠቃላይ ይዘቱ በኢቲቪ የወጣውን ዜና እና መግለጫ መድገም ነው። አንባቢ የዚህን ጽሑፍ ደራሲ ወደደም ጠላ መጎብኘቱ አይቀርም። ምክንያቱም ስለሚያጓጓ፤  ጸሐፊው በረደድ ፈለቀ (ከፈረንሳይ ለጋሲዮን) ነው። የፈረንሳይዋን ልጅ በፈረንሳይ ቋንቋ መኾኑ ነው?

“ለመመረጥ አልፈለኩም. . . እምቢ ማለት ስለማልችል ተቀብያለኹ” አቶ አየለ ጨሚሶ

ባለፈው እሁድ አዲሱ የእነ አየለ ጫሚሶ ቅንጅት ጠቅላላ ጉባዔ በማካሄድ ዘጠኝ አባላትን መርጧል። ፓርቲውን በፕሬዝዳንትነት እንዲመሩት ታድያ የፓርቲው ወላጅ አባት አቶ አየለ ጫሚሶን በድጋሚ መርጧቸዋል። ሰውየው ለኢትዮ-ቻናል እንዲህ ሲሉ ነገሩት። “ለመመረጥ አልፈለኩም ነበር፤ ለማረፍ ብፈልግም እምቢ ማለት ስለማይቻል የተሰጠኝን ኀላፊነት ተቀብያለኹ።” ልብ በሉ። እርሳቸው ግን የፓርቲዬ ወታደር ነኝ አላሉም።

“ከኢሕአዴግ የሚለየኝ ሞት ነው” አቶ መለስ ዜናዊ

ዘመን መጽሔትን ምንጭ አድርጎ ነጋድራስ ጋዜጣ በዓርብ ዕትሙ የአቶ መለስ ዜናዊን አጭር ቃለ ምልልስ ጨልፎ አስነብቧል።

ጥያቄ- እንግዳ ሲቀበሉም ኾነ ውጭ ሲሄዱ ለምንድነው ከባለቤትዎ ጋራ የማይሄዱት?

መለስ፡- …ባለቤቴ በግል የራሷ የኾነ ሥራ አላት። የራሷን ሥራ መሥራት ትፈልጋለች። የድርጅት አባል እና ታጋይ ነች። የቤት እመቤትነትን እንደ ብቸኛ ሥራ ለመቀበል ዝግጁ አይደለችም። ስለዚህ እርሷም የራሷን ሥራ ትሠራለች፤ እኔም የመንግሥት ሥራ እሠራለኹ። እኔም የመንግሥትን ሥራ እርሷም የግል ሥራ ጨርሳ ስንገኛኝ ደግሞ የቤተሰብ ሥራችንን በጋራ እንሥራለን።…

ጥያቄ፦- ለወደፊቱ ጡረታ ሲወጡ ምን ሊሠሩ ያስባሉ?

መለስ፦ ከመንግሥት ሥራ በጡረታም በሌላም መልኩ መገለል እንዳለ እና መኖርም እንዳለበት አምናለኹ። ከኢሕአዴግ ጡረታ መውጣት የሚባል ነገር ግን ለእኔ ግልጽ አይደለም። ከኢሕአዴግ የሚለየኝ ሞት ነው የሚል አቋም ነው ያለኝ።…

“ትክክለኛ ፓርላማ የተመሠረተው አሁን ነው” የቀድሞው የቴዲ አፍሮ ጠበቃ አቶ ሚልዮን

በየሳምንቱ አርብ የሚታተመው ጎግል ጋዜጣ በዚህ ሳምንት ዕትሙ የዘንድሮ ፓርላማ አባላት ምን ይላሉ በሚል አጫጭር አስተያየቶችን አስነብቧል። ታድያ ጋዜጣው ካነጋገራቸው የተከበሩ የፓርላማ አዳዲስ አባላት መካከል የቀድሞው የቴዲ አፍሮ ጠበቃ አቶ ሚሊዮን አሰፋ ይገኙበታል። እርሳቸውም እንዲህ አሉ፡- “ፓርላማ ሥራው ሕግን ማውጣት እና ሕግ አስፈጻሚውን መቆጣጠር ነው። ተቃዋሚዎች በፓርላማው ቢኖሩም የመደመጥ እንጂ ሕግ የማውጣት ሥልጣን የላቸውም። ሕግ የማውጣት ሥልጣን የአሸናፊው ፓርቲ ነው፤ ኢሕአዴግ ጊዜውን በሌላ ነገር ሳያጠፋ ያወጣውን ሕግ ለማስፈጸም ይጠቀምበታል። ኢሕአዴግ ሁልጊዜም የሚለው አንድ ነገር አለ። የአፈጻጸም ችግር አለብን እናስተካክል ነው። እንዲያውም ትክክለኛ ፓርላማ የተመሠረተው አሁን ነው”

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

ዳዊት ከበደ እና ዮሴፍ ሙሉጌታ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን አሸነፉ

“አንደኛ ሕይወትን ከጋዜጠኝነት ውጭ መኖር ለእኔ የማይቻል ነው፤ ሁለተኛ የሞት ሽረት ጥያቄ ካልገጠመኝ በቀር በፍጹም ኢትዮጵያን ትቼ መኖር አልችልም፤ ሦስተኛ ተቃዋሚ አይደለሁም፤ እንደ ጋዜጠኛ በአስተዳደር ላይ ያለው አገዛዝ ማንም ይሁን ምን ለአገር የተሻለ ዕድገት እና ለውጥ እንዲመጣ ከመጻፍ እና ከመተቸት በፍጹም ወደ ኋላ አልልም።” ብሏል።

yoseph mulugeta

(ገዛኸን ይርጋ)

ሁለት ኢትዮጵያውያን ታላቅ እና የተከበረ ዓለም አቀፍ ሽልማት አገኙ። ባለፈው ሳምንት እነዚህን ሽልማቶች ያሸነፉት የአውራምባ ታይምሱ ማኔጂንግ ኤዲተር ዳዊት ከበደ እና የቀድሞው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ዋና ጸሐፊ የነበሩት አቶ ዮሴፍ ሙሉጌታ ናቸው።

ኮሚቴ ቱ ፕሮቴክት ጆርናሊስት (ሲፒጄ) በመባል የሚታወቀው ዓለም አቀፍዊው የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት የአውራምባ ታይምስ ማኔጂንግ ኤዲተሩን ዳዊት ከበደን ተመራጭ አድርጎ ሸልሞታል። የ30 ዓመቱን ዳዊትን ሲፒጄ የመረጠው በ2005 ዓ.ም ምርጫ ወቅት ገለልተኛ በኾነ አቋም ይጽፋቸው በነበሩት ጽሑፎቹ አማካኝነት ለሁለት ዓመታት ከቅንጅት አመራሮች እና ከሌሎች ጋዜጠኞች ጋራ እስር ቤት በመቆየቱ፤ ከተፈታ በኋላም ባለው ክፍተት በመጠቀም እና ጫናውን በመቋቋም ለመሥራት ወስኖ እስከ አሁንም በሥራ ላይ ያለ ጋዜጠኛ በመኾኑ እና በአገሪቱ ካሉት የአማርኛ ጋዜጦች መካከል መንግሥትን ፊት ለፊት ለመተቸት የሚደፍር በመኾኑ የሚሉት ዝርዝሮች ይገኙበታል።

ዳዊት ለዚህ ሽልማት እንደበቃ ያወቀው ግን በዚህ ሳምንት አልነበረም። በሐምሌ ወር መጀመርያ ላይ ለሥራ ወደ ናዝሬት በሄደበት አጋጣሚ በኢሜይሉ የተላከለት መልእክት ነበር ተሸላሚነትን ያበሠረው። በመልእክቱ መጨረሻ ግን ይህን የምሥራች የላከለት ሲፒጄ በመስከረም ወር መጨረሻ በአደባባይ ይፋ እስኪያደርገው ድረስ ዳዊት ምንም ነገር ትንፍሽ ማለት እንደሌለበት ማስጠንቀቂያ አስቀምጦለታል። የዛሬ የአውራምባ ታይምስ እትም በሰፊው እንደተነተነው ዳዊት ለዚህ ሽልማት የሚያበቃ ሥራ ሠርቻለሁ ብሎ የሚያስብበት ደረጃ ላይ ሳይደርስ ነው ድንገተኛው መልእክት በሩን አንኳኩቶ የመጣው። ዳዊት ከሽልማቱ ጋራ አያይዞ ስለ ራሱ ሰው ማወቅ ያለበት ያለውን ሦስት ነገር ለሲፒጄ እንዲህ ሲል ተናገረ።

“አንደኛ ሕይወትን ከጋዜጠኝነት ውጭ መኖር ለእኔ የማይቻል ነው፤ ሁለተኛ የሞት ሽረት ጥያቄ ካልገጠመኝ በቀር በፍጹም ኢትዮጵያን ትቼ መኖር አልችልም፤ ሦስተኛ ተቃዋሚ አይደለሁም፤ እንደ ጋዜጠኛ በአስተዳደር ላይ ያለው አገዛዝ ማንም ይሁን ምን ለአገር የተሻለ ዕድገት እና ለውጥ እንዲመጣ ከመጻፍ እና ከመተቸት በፍጹም ወደ ኋላ አልልም።” ብሏል።

ከዳዊት ጋራም በዚሁ የሽልማት ሥነ ሥርዐት ላይ ሌሎች ሦስት ጋዜጠኞች ተሸላሚ ይኾናሉ። ተሸላሚ ኾነው የሚገኙት  ነዲራ ኢሳያቫ ከራሺያ፣ ላዉሪኖ ማርኪዩዝ ከቬኒዙዌላ እና ሞሐመድ ዳቫሪ ከኢራን ናቸው። እነዚህ አራት ተሸላሚዎች የመጻፍ ነጻነት በሌለበት ኹኔታ ውስጥ ያዩትን በጀግነት እና በድፍረት መዘገብ የቻሉ የሚል አድናቆት ተችሯቸዋል። የዘንድሮ ተሸላሚዎች ጭቆና፣ አፈና፣ ማስፈራርያ እና እስር እየገጠማቸውም እንኳን እውነትን ከመዘገብ ያላፈገፈጉ ጀግኖች ናቸው ሲል ድርጅቱ በድረ ገጹ አሞግሷቸዋል። ዳዊት ከበደ ይህን ሽልማት እ.ኤ.አ ሕዳር 14 ቀን 2010 በኒውዮርክ በሚደረገው ሥነ ሥርዐት ላይ ይቀበላል።

ሁለተኛው የዚህ ሳምንት የሽልማት አሸናፊ የቀድሞው የኢሰመጉ ዋና ጸሐፊ የነበሩት አቶ ዮሴፍ ሙሉጌታ ናቸው። አቶ ዮሴፍ የ2010 ሂዩማን ራይትስ ዎች ታላቁን የዶክተር አሊሰን ሽልማት ለመሸለም በቅተዋል። ይህ ሽልማት በዓለም ላይ ለሰው ልጆች ክብር እና ሰብአዊ መብት ለታገሉ ግለሰቦች በየዓመቱ የሚሰጥ ነው። እርሳቸውን ጨምሮ ይህንኑ ሽልማት የሚያገኙ ስድስት የዘንድሮ ተሸላሚዎች ሽልማታቸውን ወስደዋል። ሆሳም ባጋት ከግብፅ፣ ኤለን ሚላሺና ከራሺያ፣ ስቲቭ ኔማንድ ከካሜሮን፣ ሱዛን ታህማሴቢ ከኢራን አንዲሁም ዮሴፍ ሙሉጌታ ከኢትዮጵያ ናቸው።

ለእነዚህ ጀግኖች ትልቅ ክብር አለን ያሉት የድርጅቱ ዳይሬክተር ኬኔት ሮስ በአስቸጋሪ ኹኔታዎች ሁሉ ሕይወታቸው አደጋ ላይ ኾኖ እንኳ ለሰብአዊ መብት መከበር ደፋ ቀና ያሉ ድንቅ የሰብአዊ መብት ጀግኖች ናቸው ሲሉ የዘንድሮ ተሸላሚዎቹን አድንቀዋል። አቶ ዮሴፍ ሙሉጌታ በአሁኑ ሰዓት በጥገኝነት አሜሪካ የሚገኙ ሲኾን አሁንም ድረስ በሰብአዊ መብቶች ጉዳይ ላይ ጠንክረው እየሠሩ እንደሚገኙ መግለጫው ያትታል። ሂዩማን ራይትስ ዎች የተባለው የሰብአዊ መብት ተሟጋች በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት በተደጋጋሚ በጥናት እያስደገፈ በማውጣት ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋራ ከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ የሚገባ ዓለም አቀፍዊ ተቋም ነው።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

[አንድ ለቅዳሜ!] ከብርቱካን እስር ወደ ብርቱካን ጥያቄዎች

ክርክሩ “ለምን ይቅርታ ጠየቀች” ሳይሆን በዋናነት ይቅርታ ለመጠየቅ ተጠቀመችበት የተባለው አገላለጽ ነው። በእውነትም አገላለጹ እርሷን ለማዋረድ፣ ደጋፊዎቿን ለማሳፈር ሆን ተብሎ የተቀመረ እንደሆነ የሚያከራክር አይደለም። በዚህ ጉዳይ ላይ የብርቱካንን ምስክርነት ሳንሰማ “ይህኛውን ቃል፣ ያኛው አረፍተ ነገር” ብሎ መከራከር ትርጉም ካለው መደምደሚያ ላይ ማድረስ አይችልም። ብርቱካን ይቅርታ በጠየቀችበት ደብዳቤ ውስጥ በጣም ያስገረመኝን አንድ አረፍተ ነገር ልጥቀስ። “…ወደዚህ ስህተት ልገባ የቻልኩት መንግሥት የውጭ ኀይሎችን ተጽእኖ በመፍራት ሊያስረኝ አይችልም፤ ካሰረኝም ተገዶ በአጭር ጊዜ ይፈታኛል በሚል የተሳሳተ ግንዛቤ ነው።” ቃላት ለአንድ ቀን እግር አውጥተው ወደየመጣችሁበት ተመለሱ ቢባሉ እነዚህ ቃላት የነብርቱካንን ሰፈር (ፈረንሳይ ለጋሲዮን) ዳገት ችለው ይወጡታል? ብርቱካን ይቅርታው ስለጠየቀችበት ከባቢያዊ፣ አካላዊ እና ስነ ልቦናዊ ሁኔታ የራሷን ቃል ሳንሰማ “ቢሆንም…ምንም ቢሆን…” ማለት ብዙዎችን ከወዲሁ የሚያሳጣ አመለካከት ይመስለኛል። ጊዜ ሰጥቶን ዝርዝሩን እንሰማለን።

ሁለተኛው የአመለካከት ዘርፍ “ዋናው መፈታቷ” ብሎ የሚቆመው ነው። ይህ ምልከታ ለብርቱካን ሰብአዊነት የበለጠ ቦታ ይሰጣል፤ ለከፈለችው ዋጋ ከፍተኛ ዋጋ በመስጠትም “እርሷ የበኩሏን አድርጋለች” ብሎ ሊያምንም ይችላል። ከዚያም ባለፈ ስል ልጇ እና እናቷ ወዘተ በማሰብ መፈታቷን የራሱ ግብ አድርጎ ያስቀምጠቃል። እርግጥ በመጀመሪያው ክፍል ያሉትም ሰዎች ቢሆኑ ይህንን አይቃወሙም፤ ይደግፋሉ እንጂ። የዚህ ምልከታ ውሱንነት የብርቱካን ከእስር መፈታትም ሆነ አፈታቷ በፖለቲካችን ውስጥ የሚኖረውን ትርጉም እንዳናሰላስለው ያሳንፋል።

ብርቱካን በአካል ተፈታች። በዚህ በራሱ ብቻ አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ እፎይታን እንዳገኘ እገምታለሁ፤ የኢሕአዴግን ካድሬዎች ጭምር። ባለፈው ሳምንት “ይቅርታ ለብርቱካን ወይስ ይቅርታ ከብርቱካን? ይቅር ባዩ ማነው?” በሚል ርእስ በዚሁ ብሎግ ላይ ያነሳኋቸው ጥያቄዎች ተገቢ እንደነበሩ የበለጠ የተገነዘብኩት ብርቱካን ለመፈታት አቀረበችው በተባለው የይቅርታ ደብዳቤ የተንጸባረቀውን ሐሳብ ስመለከት ነው። የብርቱካን መታሰር ብቻ ሳይሆን መፈታቷም በፖለቲካችን ውስጥ እየተካሄደ ስላለው ለውጥ መሠረታዊ ጥያቄ እንድናነሳ የሚጋብዘን መሆኑንም አንስቼ ነበር።

ጉዳዩ ብዙ የሚያነጋግሩ ሐሳቦች የታጨቁበት ስለሆነ ለዛሬው ብርቱካን በተፈታችበት ሁኔታ ዙሪያ በሚነሳው ጥያቄ ላይ ብቻ ላተኩር። በአጠቃልይ የብርቱካንን መታሰር ሲቃወም፣ መፈታቷን ሲወተውት በነበረው ጎራ ሁለት ስሜቶች ጎልተው ወጥተዋል። አንደኛው ብርቱካንን “ጽድቋን አፈረሰቸ” ብሎ ለመውቀስ የሚግደረደር ነው፤ ፊት ለፊት ባይለውም። “ይቅርታ መጠየቋ ካልቀረ መጀመሪያውኑ ለምን ታሰረች?” በሚል ወቀሳ ያዘለ ጥያቄ መልክ ይቀርባል። በተለይም ለኢቲቪ የሰጠችው ቃለ መጠይቅ እና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቀረበችው የተባለው ማመልከቻ ይዘት “አዋራጅ” መሆኑ ለዚህ ጥያቄ ባለቤቶች ለመዋጥ የሚያስቸግር መራራ እውነት የሆነ ይመስላል። በሁለተኛው ወገን ገዝፎ የሚሰማው ስሜት ደግሞ “መፈታቷን በራሱ” እንደግብ በማየት ፖለቲካዊና ማኅበረሰባዊ ፋይዳውን አቃሎ የሚመለከት ነው።

ሦስተኛ መጨመር ካስፈለገ ከኢሕአዴግ ደጋፊዎች የተወሰኑት የሚያንጸባርቁት የአሸናፊነት ቀረርቶ ነው። ቀረርቶው በአብዛኛው የብርቱካንን ደጋፊዎች ለማብሸቅ እና ለመጎንተል፣ ግፋ ቢል ደግሞ “ጉልበተኞቹ እኛ ስለሆንን እንደፈለግን እንደምናደረግ አሳየናችሁ” የሚል ቃና ያለው ማስፈራሪያ ነው።

የአንደኛው ጥያቄ ባለቤቶች በተለይ የብርቱካን ቃለ መጠይቅ በቴሌቪዥን እንደተላለፈ ብስጭት እና ኀዘናቸው ከፍተኛ ነበር።   ይህ ስሜት ወዲያው ለአደባባይ ባይበቃም በግለሰቦች ደረጃ ተንጸባርቋል። እየቆየም ለተለያየ ዓለማ የበለጠ የሚያራምዱት ሰዎች እንደሚኖሩ ግልጽ ነው። “ለዚህ ለዚህ መጀመሪያውኑ ለምን ታሰረች? ይቅርታስ መጠየቅ ካለባት እንዴት እንዲህ ባለ አዋራጅ እና ራሷን መልሶ ሊመታ በሚችል አገላለጽ ትጠቀማለች? ድሮስ ከኢሕአዴግ ምን ጠብቃ ነበር? በዚህ ሁኔታ ወጥታ ቀጣይ የፖለቲካ እጣዋ ምን ሊሆን ይችላል?” የሚሉት ጥያቄዎች የክርክሩ ጭብጦች ናቸው።

የዚህ ጭብጥ ባለቤቶች ቢያንስ ለተወሰነ ጊዜ የማይመልሷቸው ከባድ ጥያቄዎች አሉባቸው። የመጀመሪያው ፈተናቸው ብርቱካን በምንም ሁኔታ ትፈታ፣ ምንም ቃል ትጠቀም እስከአሁን ለከፈለችው መስዋእትነት ዋጋ ያለመስጠት አጣብቂኝ ውስጥ ይከታቸዋል። ሰፋ አድርገን ስንመለከተው ደግሞ ዜጎች (በተለይም የፖለቲካ መሪዎች) የሚችሉትን እና የሚፈልጉትን ያህል ሳይሆን ሌሎች የሚያስቡትን/የሚፈልጉትን ዓይነት ለውጥ የሚያመጣ መስዋእትነት ካልከፈሉ ለአስተዋጽኦዋቸው ዋጋ ልንሰጠው አይገባም/አይቻልም የሚል መደምደሚያ ላይ ሊያደርሰን ይችላል። ይህ ደግሞ በቂ መስዋእትነት/ዋጋ ምን ዓይነት ነው? አንድ የፖለቲካ መሪ “መክፈል ያለበት ዋጋ ምን ያህል ነው?” የሚል ሰፊ ጥያቄ የሚጋብዝ ነው። በውጤቱም ዜጎችን ከፖለቲካ ተሳትፎ የሚያርቅ፤ ፖለቲካ ውስጥ መግባትን ጦር ሜዳ ከመግባት ጋር የሚያስተካክል ይሆናል። “ፖለቲካ ውስጥ ስትገባ በሕይወትህ ቆርጠህ መሆን አለበት” እንደማለት ነው። “ትግሉ የሚጠይቀውን” ዋጋ መጠን እና እያንዳንዱ ሰው ሊከፍል የሚገባውን የሚወስነው ማነው? እርግጥ ይህን የሞራል ጥያቄ ብርቱካን ላይ ለማንሳት “የሞራል ስልጣኑ አለኝ” የሚል ሰው አላጋጠመኝም። ይህን ጥያቄ ለማንሳት የግድ የእርሷን  ያህል ዋጋ መክፈል ያስፈልጋል ማለት ግን አይደለም።

ይህን ሐሳብ ለመቀበል ሌላው መመለስ የሚገባው ጥያቄ ብርቱካን ስለተፈታችበት ሁኔታ ዝርዝር እውነታውን መረዳት ነው። ክርክሩ “ለምን ይቅርታ ጠየቀች” ሳይሆን በዋናነት ይቅርታ ለመጠየቅ ተጠቀመችበት የተባለው አገላለጽ ነው። በእውነትም አገላለጹ እርሷን ለማዋረድ፣ ደጋፊዎቿን ለማሳፈር ሆን ተብሎ የተቀመረ እንደሆነ የሚያከራክር አይደለም። በዚህ ጉዳይ ላይ የብርቱካንን ምስክርነት ሳንሰማ “ይህኛውን ቃል፣ ያኛው አረፍተ ነገር” ብሎ መከራከር ትርጉም ካለው መደምደሚያ ላይ ማድረስ አይችልም። ብርቱካን ይቅርታ በጠየቀችበት ደብዳቤ ውስጥ በጣም ያስገረመኝን አንድ አረፍተ ነገር ልጥቀስ። “…ወደዚህ ስህተት ልገባ የቻልኩት መንግሥት የውጭ ኀይሎችን ተጽእኖ በመፍራት ሊያስረኝ አይችልም፤ ካሰረኝም ተገዶ በአጭር ጊዜ ይፈታኛል በሚል የተሳሳተ ግንዛቤ ነው።” ቃላት ለአንድ ቀን እግር አውጥተው ወደየመጣችሁበት ተመለሱ ቢባሉ እነዚህ ቃላት የነብርቱካንን ሰፈር (ፈረንሳይ ለጋሲዮን) ዳገት ችለው ይወጡታል? ብርቱካን ይቅርታው ስለጠየቀችበት ከባቢያዊ፣ አካላዊ እና ስነ ልቦናዊ ሁኔታ የራሷን ቃል ሳንሰማ “ቢሆንም…ምንም ቢሆን…” ማለት ብዙዎችን ከወዲሁ የሚያሳጣ አመለካከት ይመስለኛል። ጊዜ ሰጥቶን ዝርዝሩን እንሰማለን።

ሁለተኛው የአመለካከት ዘርፍ “ዋናው መፈታቷ” ብሎ የሚቆመው ነው። ይህ ምልከታ ለብርቱካን ሰብአዊነት የበለጠ ቦታ ይሰጣል፤ ለከፈለችው ዋጋ ከፍተኛ ዋጋ በመስጠትም “እርሷ የበኩሏን አድርጋለች” ብሎ ሊያምንም ይችላል። ከዚያም ባለፈ ስል ልጇ እና እናቷ ወዘተ በማሰብ መፈታቷን የራሱ ግብ አድርጎ ያስቀምጠቃል። እርግጥ በመጀመሪያው ክፍል ያሉትም ሰዎች ቢሆኑ ይህንን አይቃወሙም፤ ይደግፋሉ እንጂ። የዚህ ምልከታ ውሱንነት የብርቱካን ከእስር መፈታትም ሆነ አፈታቷ በፖለቲካችን ውስጥ የሚኖረውን ትርጉም እንዳናሰላስለው ያሳንፋል። ይህን ስል ብርቱካን ስለተፈታች ብቻ መሠረታዊ ለውጥ ይፈጠራል አለዚያም ተፈጠሯል ከሚል ድምዳሜ በመነሳት አይደለም። ጉዳዩ “ታሰረች፣ ተፈታች፤ እንኳንም ተፈታች” ተብሎ ሊታገት እንደማይችል ሁለት ማሳያዎች ልጥቀስ።

የብርቱካን መፈታት በራሱ ለፓርቲዋ እና አገር ውስጥ ላለው የፖለቲካ ውድድር ትልቅ ትርጉም እንደሚኖረው አያጠራጥርም። በፖለቲካ ባትቀጥል እንኳን ይህ በራሱ ሰፊ ትርጉም የሚሰጥ መሆኑ አይቀርም። የብርቱካን መፈታት እና ከዚያ በኋላ የሚኖራት ተሳትፎ በተቃዋሚ ፓርቲዎች ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች፣ ተቃዋሚዎችን በግልጽም ይሁን በድብቅ ለሚደግፉ ሰዎች ወዘተ የሚያስተላልፈው ችላ ሊባል የማይችል መልእክት አለው።

አሁን ደግሞ ኢሕአዴግ ብርቱካን እንድትፈታ የመረጠበት መንገድ ሌላ መዘዝ እንደሚጋብዝ መገመት ይቻላል። ማረጋገጫውን ከብርቱካን መስማት የሚፈልጉ ሰዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ እገምታለሁ። ወዲህ ይቅርታ መጠየቅ እና ይቅርታ መስጠት ፖለቲካችን ውስጥ አዲስ ትርጉም ለማግኘታቸው ብርቱካን አዲሷ ተጠቃሽ ማሳያ ተደርጋ ልትቀርብ ትችላለች። ተጠቃሽነቷ ለየትኛው ወገን እንደሚሆን ወደፊት የሚታይ ነው። በሌላ በኩል ብርቱካን “ይቅር የተባለችበት” ሁኔታ ብቻውን በተቃውሞው ጎራ ለሚገኙ የሚያስተላልፈውን መልእክት “ተስፋ ቁረጡ” እንደማለት አድርጎ ለመውሰድ የቀለለ ይመስላል።  ከብርቱካን ተነስተን “ይቅርታ መጠየቅ፣ ይቅርታ መስጠት ፖለቲካችን ውስጥ ያላቸው ትርጉም ምንድን ነው?” ብለን እንጠይቃለን። ማሰላሰሉ ይቀጥላል፣ በግልም በጋራም።

በመጨረሻ ከኢሕአዴግ ደጋፊዎች የተወሰኑት የሚያሰሙትን ፉከራ ላንሳ። “የተወሰኑ” ያልኩት ሆን ብዬ ነው። በሌሎች የፖሊሲ ወይም የአመለካከት ጉዳዮች በአንዱ ጉዳይ ተስማምተን በሌላው ብንለያይ እንኳን፣ በዚህ መሰሉ የ“ይቅር ባይ” ቀረርቶ መሳተፍ የማይፈልጉ ወዳጆቼ ስላሉ ጭምር ነው። መቼም ይቅር ባይ “ይቅርታ አደርኩ” ብሎ ከፎከረ የይቅርታውን ነፍስ እንደሚገድለው በባህላችን የታመነ ነው። ይቅርታ በሌላ መንገድ (በሕግ፣ በጉልበት ወዘተ) የማይገኝን እርቅ ማውረጃ ነው። ይቅር ባይ ነኝ የሚል ሰው/አካል በይቅርታ ጠያቂው ላይ አይዘብትም። ከዘበተም እጅግ ግብዝና ጨካኝ ሰው ነው። “እነአሞራው በሞት ፊት እንኳን ፊታቸውን አልመለሱም እንኳን በሞቀ እስር ቤት…” አይነቱ ንግግር (የአይጋ ፎረም ኤዲቶሪያል አስተያየት) መልእክቱ የእርቅን መንፈስ ፈጽሞ የሚገድል ነው፤ “የፉከራው ዓላማ ምን ሆነና” ካልተባልኩ በቀር። “እናንተም እንደእኛ ካልሞታችሁ…” የሚል ፉከራ ምን ይጠቅማል? ምንም። ለዚያውም እኮ ሞቱ የሚባሉት ጀግኖች መርጠው ለእነርሱ (ለአሁኖቹ ፎካሪዎች) የሞቱላቸው ይመስል፤ እኛ የጎረቤት/የጠላት አገር ዜጎች የሆንን ያህል።

ለማንኛውም ብርቱካን እስሯ ብቻ ሳይሆን መፈታቷም ብዙ ነገሮችን እንድንጠይቅ ግድ ይለናል።

2 Responses to “[አንድ ለቅዳሜ!] ከብርቱካን እስር ወደ ብርቱካን ጥያቄዎች”

  1. በጣም የሚያሳዝን እና የሚገርም ነገር ነው! ሌላ ምንም ማለት አይቻልም::
    እርግጠኛ ነኝ አቶ ነጋሶ የተሻለ ነገ ይመጣላቸዋል:: መለስ ስልጣን ሲለቅቅ (ሲለቅቁ)ፕሮፌሰር ፧ የተባበሩት መንግስታት አማካሪ ምናምን ምናምን ይሆናል አይደለ ተረቱ :)

  2. i’m really disappointed withdr.negasos monthly penstion money.the leading party tplf andhis cadres(kangaro make with him ridiculous game).how ot could be tha one who lead ethiopian for 5years on presdent..they decide 1197.60 it is less than 50€ very embarrassing judgement….those who make this!!!
    may god keep ethiopian for those tyrant administration

Leave a Reply

You must be to post a comment.

ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ “ከእስር ሊለቀቁ ነው”

ላለፈው አንድ ዓመት ከዘጠኝ ወራት በእስር ላይ የቆዩት የአንድነት ለዲሞክራሲ እና ለፍትሕ ሊቀመንበር ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ዛሬ ማታ ወይም በነገው ዕለት እንደሚፈቱ የአዲስ ነገር ምንጮች ገለጹ። ሆኖም በምን ዐይነት ቅድመ ኹኔታ እንደሚፈቱ እንደማያውቁ ምንጮች ተናግረዋል።
እንደምንጮቹ ገለጻ ከሆነ ብርቱካንን የማስፈታት ሂደት የተጀመረው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በአዲስ ዓመት የመጀመርያ ሳምንት ላይ የሀገር ሽማግሌዎችን “መጥታችሁ እንድፈታት ጠይቁ እና ትፈታ” የሚል መልእክት መላካቸውን ተከትሎ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ስለ ብርቱካን መፈታት በሚጠየቁበት ጊዜ በተደጋጋሚ የሚሰጡት መላሽ “የሕግ ጉዳይ ነው” የሚል ቢሆንም በቅርቡ በኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ በተገኙበት ወቅት ሊቀመንበሯ ይቅርታ ከጠየቁ መንግስት ምህረት ሊያደርግ እንደሚችል ጠቁመው ነበር።

ላለፈው አንድ ዓመት ከዘጠኝ ወራት በእስር ላይ የቆዩት የአንድነት ለዲሞክራሲ እና ለፍትሕ ሊቀመንበር ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ዛሬ ማታ ወይም በነገው ዕለት እንደሚፈቱ የአዲስ ነገር ምንጮች ገለጹ። ሆኖም በምን ዐይነት ቅድመ ኹኔታ እንደሚፈቱ እንደማያውቁ ምንጮች ተናግረዋል።
እንደምንጮቹ ገለጻ ከሆነ ብርቱካንን የማስፈታት ሂደት የተጀመረው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በአዲስ ዓመት የመጀመርያ ሳምንት ላይ የሀገር ሽማግሌዎችን “መጥታችሁ እንድፈታት ጠይቁ እና ትፈታ” የሚል መልእክት መላካቸውን ተከትሎ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ስለ ብርቱካን መፈታት በሚጠየቁበት ጊዜ በተደጋጋሚ የሚሰጡት መላሽ “የሕግ ጉዳይ ነው” የሚል ቢሆንም በቅርቡ በኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ በተገኙበት ወቅት ሊቀመንበሯ ይቅርታ ከጠየቁ መንግስት ምህረት ሊያደርግ እንደሚችል ጠቁመው ነበር።
ከዚህ ቀደም የቅንጅቶችን የሽምግልና ሂደት ሲከታተሉ የነበሩት ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅ እና ሌሎች ሁለት የሀገር ሽማግሌዎች ባለፈው ሳምንት በቃሊቲ እስርቤት መታየታቸውን የሚናገሩት ምንጮች ወይዘሪት ብርቱካን በመስቀል በዐል ዋዜማ ይፈታሉ ተብሎ ይጠበቅ እንደነበር ያስታውሳሉ። ስለጉዳዩ የተጠየቁት የወይዘሪት ብርቱካን ጠበቃ አቶ ተስፋዬ ደረሰ የሊቀመንበሯን ከእስር መለቀቅ በተመለከተ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ለአዲስ ነገር ገልጸዋል። ሆኖም ዛሬ ማታ ወይም ነገ ጠዋት እንደሚፈቱ ወሬ መስማታቸውን ይናገራሉ። “መፈታቷን ግን በተስፋ እና በጉጉት እየተጠባበቅን ነው” ይላሉ።
“ስለመፈታቷ እኔም እንደማንኛውም የአዲስ አበባ ነዋሪ እየሰማሁ ነው። እርሷን የማየትም ኾነ የመጎብኘት ፈቃድ ስላልተሰጠኝ በምን ዐይነት የሕግ አግባብ እንደምትፈታ አላውቅም” ይላሉ አቶ ተስፋዬ። ከእስር የመፈታትን ጉዳይ በሁለት መንገድ አማራጭ እንዳለው የሚናገሩት አቶ ተስፋዬ አንዱ በቀጥታ ለፍትህ ሚኒስትር በሚቀርብ የይቅርታ መጠየቂያ ሲኾን ሌላኛው ደግሞ ከዚህ በፊት የቅንጅት አመራሮች በሽምግልና በተፈቱበት አካሄድ እንደኾነ ተናግረዋል።
ብርቱካን ዛሬ ማታ ወይም ነገ ጠዋት እንደምትለቀቅ የሚጠቁሙ መረጃዎች ከመንግሥት ከፍተኛ ባለ ሥልጣናት ጭምር እየተሰሙ እንደኾነ ምንጮቻችን ለአዲስ ነገር ገልጸዋል። ይኹንና ባለ ሥልጣናቱ የምትፈታበትን ቅድመ ኹኔታ ከመናገር ተቆጥበዋል። አቶ መለስ በየአቅጣጫው የብርቱካን መታሠር ጉዳይ ዓለምአቀፍ ጫና እያሳደረ ስለመጣባቸው ወደ መፍታቱ እንደመጡ ውስጥ አዋቂዎች ለአዲስ ነገር ገልጸዋል።

One Response to “ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ “ከእስር ሊለቀቁ ነው””

  1. በጣም የሚያሳዝን እና የሚገርም ነገር ነው! ሌላ ምንም ማለት አይቻልም::
    እርግጠኛ ነኝ አቶ ነጋሶ የተሻለ ነገ ይመጣላቸዋል:: መለስ ስልጣን ሲለቅቅ (ሲለቅቁ)ፕሮፌሰር ፧ የተባበሩት መንግስታት አማካሪ ምናምን ምናምን ይሆናል አይደለ ተረቱ :)

  2. i’m really disappointed withdr.negasos monthly penstion money.the leading party tplf andhis cadres(kangaro make with him ridiculous game).how ot could be tha one who lead ethiopian for 5years on presdent..they decide 1197.60 it is less than 50€ very embarrassing judgement….those who make this!!!
    may god keep ethiopian for those tyrant administration

Leave a Reply

You must be to post a comment.

ተስፈኝነት የማይጨልምበት ስደተኝነት

የሰው እጅ ጥበቃ የሰለቻቸው ብልኀትን ፈጥረዋል። አንዳንዶቹ ብልኀቶች ዛሬ ነፍስን ከማዳን ነገን ደግሞ ተስፋ ከማድረግ ብቻ የመነጩ ናቸው። ብዙ የታሰበባቸው የሚመስሉ አይደሉም። ሴቶቹ የምሽት ዳንስ ቤቶችን በመጎብኘት የሚመጣውን የማታ ሲሳይ ይጠብቃሉ። ጥቂት የማይባሉ ወንዶች ደግሞ በፌስ ቡክ እና መሰል የማኅበራዊ ሚዲያዎች አማካይነት አውሮፓ የሚገኙ እና ለትዳር እና ለውሲብ የሚጓጉ በዕድሜ ገፋ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሴቶች ጋራ ግንኙነት በመመሥረት ተስፋ ላይ ራሳቸውን ይጥላሉ። የዕለት ወጭያቸውን ከመሸፈን ባሻገር የአውሮፓ ጉዞ ተስፋቸውን ብሩህ ለማድረግ ያታትራሉ።

(ታሪኩ አዳፍሬ ከኬንያ)

ክፍሏን ለመግለጽ ጠባብ የሚለው ቃል ብቻውን የልብ አያደርስም። በአጭሩ የበሬ ግንባር የሚሏት ዐይነት ናት። ጥበቷ እና የታቀፈቻቸው ሰዎች ብዛት ግን ለተመጣጥኖሽ እንኳ የሚከብድ ነው። በሦስት ማእዘናት የተዘረጉ ፍራሾች፣ ከአንድ ጥግ መደገፍ እንጂ በወጉ መቀመጥ ያልቻለ ቴሌቭዥን፣ ተደራርበው የተቀመጡ ሻንጣዎች፣ ከሻንጣው በላይ የተደረቡ ቀለም ዐልባ ድሪቶዎች . . . መሀል ላይ በትሪ ላይ የተደረደሩ የቡና ስኒዎች፣ ዕጣን ማጤሻ፣ የከሰል ምድጃ . . .

ምሽቱ ለብርሃን ተራውን ከለቀቀ አስር ሰዓታት ተቆጥረዋል። በኬንያ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች አቆጣጠር ግን “ከማለዳው” ሁለት ሰዓት ሊኾን ነው። በዚሁ ፀሐይ እያዘቀዘቀች በመጣችበት ሰዓት ገና እየነጋ የሚመስለው እና የጠዋቱ አራት ሰዓት የሚታሰበው ስደተኛ ካለ በታታሪዎቹ የኬንያ ስደተኞች አቆጣጠር “ማልዶ” ከቀኑ ስድስት ሰዓት ላይ ተነስቷል ማለት ነው። ይህ ቀትር ላይ ከእንቅልፍ የመንቃት ልምድ የራሱ የኾኑ መላምቶች አሉት።

ከአገር ያፋታው እና ቀን ከሌት ሕልም ኾኖ የሚያባዝነው የምዕራብ አውሮፓ እና የሰሜን አሜሪካ ጉዞ ስኬታማ እስኪኾን ድረስ “ጊዜ መግደያ ነው” የሚለው የመጀመርያው መላምት ነው። በዚህኛው መላምት አብዛኞቹ ስደተኞች ይስማማሉ። ሁሉም በሚባል ደረጃ ውጭ በሚኖር የወዳጅ ዘመድ ድጎማ የሚኖሩ እንጂ የተለየ የገቢ ምንጭ የሌላቸው ናቸው። ስለዚህ ማልዶ ለመነሳት ምክንያት የላቸውም። ሁለተኛው መላምት ባለሙሉ ተስፈኞች የሚያቀነቅኑት ዐይነት ነው። ወደፊት ምርታማ አሜሪካዊ ዜጋ የመኾን ራዕይን ያዘለ መላምት። በኬንያ ከቀኑ ዐሥር ሰዓት ሲኾን አብዛኛው የአሜሪካ ግዛት ንጋትን የሚያይበት ነው። ቀኑ ሳያመልጠው ራሱን የሩጫው አካል ለማድረግ የሚራወጥበት እና ለመኳተን የሚዘጋጅበት ሰዓት ነው።

በኬንያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ስደተኞችም በአሜሪካ ኑሮ ማልዶ የመንቃት ጥቅም የገባቸው ይመስል እኩል ሰዓት ላይ ይባንናሉ። እናም በተመሳሳዩ ሰዓት አርፍደው (ተግተው) በመነሳት ልምምዳቸውን በኬንያ ምድር ከወዲሁ ተያይዘውታል። በርካታ ሐበሻ በሚኖርባቸው እንደ ኢስሊ ባሉ አካባቢዎች ያሉ የሐበሻ ሱቆች በማለዳ የማይከፈቱትም በእነዚህ እና በእነዚህ መሰል ምክንያቶች ጭምር ነው። “አውሮፓ እና አሜሪካ የሚኖር ዘመድን ለማግኘት አመቺው ሰዓት ከዐሥር ሰዓት በኋላ ነው” የሚለው የተለመደ ንግግር በሦስተኛ ደረጃ የሚገኝ ሌላኛው መላምት ነው።

አብዛኞቹ ኬንያ ውስጥ ያሉ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በአዲስ አበባ ወንደላጤዎች እና ዘመናዊ ቆጣቢዎች ዘንድ “ቁ-ምሳ” (በምዕራባውያን ዘንድ “ብራንች” ተብሎ ይታወቃል) የሚል ማእረግ የተሰጠው ቁርስንም ምሳንም ከረፋዱ አምስት ሰዓት ላይ የመመገብ ልማድን ቢኮርጁም የሚጠቀሙበት በራሳቸው የሰዓት አቆጣጠር ነው። የሐበሻዋ “መክሰስ” “የቁምሳን” ቦታ ወስዳለች። እራት ደግሞ በውድቅት ሌሊት ተተክቷል። ድንገት ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ላይ አንድ ስደትን የሚጋራ የአገር ሰው በራችሁን አንኳኩቶ “በዚህ ሳልፍ ሰላም ሳልላችኹ አላልፍም ብዬ ነው” ቢላችኹ ሊገርማችኹ አይገባም። የእራት ሰዓት ላይ መገናኘታችኹ እንጂ። ከረፋዱ አምስት ሰዓት ላይ ተመልሶ ቢመጣ ግን ለጠብ ፈልጎዎታል ወይም እነደ አገር ቤት ይትበኻል “መርዶ ነጋሪ” ነው ማለት ነው። ደግነቱ እርሱም “በውድቅት ማለዳ”አይሞክረውም።

ስደት እና ቅፈላ . . .

በዚህ ሰዓት እንግዲህ ማለዳ ለእንቅልፍ ያገለገሉ ፍራሾች አሁንም ብቻቸውን አይኾኑም፤ አይደሉምም። ዘወትር የሚጎበኟቸው እንግዶች ቢያንስ ቀጣዮቹን ስምንት ሰዓታት እንዳሻቸው ያሹዋቸዋል። እረፍት የለሾቹን ፍራሾች። በዚያች “የበሬ ግንባር” በምታህል ክፍል ስምንት ወጣቶች ጥግ ጥጋቸውን ይዘዋል፤ የመንታ ያህል በሚያመሳስላቸው አቀማመጥ። ቡና የምታፈላው ወጣት ከጊዜያዊ ረኸቦቷ ጋራ ለማዕከላዊነት የቀረበውን ሥፍራ ይዛላች። በእያንዳንዱ ተቀማጭ ጭን ሥር በጥቁር ላስቲክ የተቋጠረ ጫት ይገኛል። ሚራ ይሉታል ኬንያውያን እና የምሥራቅ አፍሪካ አገራት ሰዎች። አዲስ አበቤዎች ከሚያወቁት የተለየ ጫት ነው። ከካርቶን የሚወፍር ቅጠል፣ ማንጠልጠያ እንጨት እንኳ የሌለው። በሁለት ጣቶች እየተቆነጠረ የሚሰፈር። ከሰላሳ የኬንያ ሽልንግ (አምስት የኢትዮጵያ ብር) ጀምሮ ይገኛል። ለአብዛኛው ስደተኛ ያለ ጫት የምታልፍ ቀን እንደባከነች ትቆጠራለች። ጫት እና ሕይወት ያላቸው ትሥሥር እንደ ሳንቲም ገጽታ ያለ ነው። የሌለው ቢቻል ቀፍሎ (ለምኖ) አልያም ዱቤ የማያውቁትን የኬንያ ጫት ሻጮች አሳምኖ ዕለታዊ ምሱን ያደርሳል።

ደምስ ከፕሮፌሽናል ቀፋዮች (PK) የአንደኛነትን ደረጃ ከሚይዙት መካከል የሚመደብ ነው። ወደጆቹ “ሲቀፍል ጉርሻም ቢኾን አይቀረው” ሲሉ መረር አርገው ይቀልዳሉ። ዛሬም ቡድኑን ለመቀላቀል የዘገየ ቢኾንም በ100 ሽልንግ ለሌሊቱ የሚበቃውን ያህል ጫት አግኝቷል። የደምስ ኑሮ ላለፉት አምስት ይችኑ መደጋገም ብቻ ነው። ቀፍሎ የቤት ኪራይ ይከፍላል፤ ቀፍሎ ይመገባል፤ ቀፍሎ ይጠጣል፤ ቀፍሎ የመረጣትን ኬንያዊ ሴት ይዞ ያነጋል፤ ቀፍሎ ይቅማል . . .  በቃ ቅፈላ እስካለ ሕይወት ለደምስ ጎድላለች የምትባል አይደለችም።

የኬንያ ምድርን ከረገጠበት ከ1992 ዓ.ም ጀምሮ ለስድስት ዓመታት የቤተዘመዶቹን ድጎማ አልተነፈገም ነበር። በየወሩ እስከ ሦስት መቶ ዶላር ያህል እየተደጎመ ስደተኛ ሳይኾን አምባሳደር መስሎ አሳልፏል። በዓመታቱ ርዝመት ወደ አውሮፓ የመሄዱ ሕልም የከሰመ የመሰላቸው ለጋሾቹ እጃቸው እያጠረ መጣ። ከሦስት . . .ወደ ሁለት . . .  አንድ  እያለ ወደ ኪሱ ሲገባ የነበረው ዶላር ወደ ዐልቦነት ተሻገረ። በወቅቱ ወደ አገር ቤት የመመለሱም ፍላጎት ተኖ ጠፍቶ ነበርና ኬንያን ከቅፈላ ጋራ እንደ አዲስ ይለማመዳት ጀመር። ሲነቃ ስለ ጫቱ አብዝቶ ያስባል፣ ይጨነቃል፣ ሲለው ይተጋል፤ ሲመረቅን ለአንገት ማስገቢያ የሚላትን ኻያ ሽልንግ ለመጠጡ በመፈለግ ይባትላል። ሲሰክር ደግሞ ቤቱ እንዳይቀዘቅዘው በጭኗ የምታሞቀው ሴት ከንጋቱ 11 ሰዓት ያስሳል። “ሳይደግስ አይጣላም” የሚለው አባባል ለደምስ የተሠራ እስኪመስል ጠይም የሐበሻ መልኩ አግዞት አንዷን ሳያስከትል ገብቶ አያውቅም። ይህ የኑሮ ዑደቱ ለአንድም ቀን እንኳ አልተዛነፈበትም። የሚዛነፍበትም አይመስለውም።

ደምስን መሰል አንዳች ደጋፊ የሌላቸው ስደተኞች ዕለታዊ ዕድላቸውን ተጠልለው በናይሮቢ  በሽ በሽ ኾነዋል። ሐበሻ በአብዛኛው በሚኖርባቸው እንደ ኢስሊ፣ ፓንጋኒ እና ሐርሊንግሃም አካባቢዎች አይጠፉም። ብዙዎች ከዐሥር ዓመታት በላይ የቆዩ በመኾናቸው ዘመድ አዝማድ እጁን ማስረዘም ሰልችቶት የተዋቸው ናቸው። ወደ አገር ቤትም የመመለስ ሐሳብ ለብዙዎቹ እንደ መርግ ከብዷቸዋል። አንዳንዶቹ ነገን ተስፋ በማድረግ ቀሪዎቹ ደግሞ “ምን ይዤ ልመለስ” በሚለው ሐሳብ ራሳቸውን እየሞገቱ ጭንቅላታቸው ውስጥ የ”መመለስን” አራት ነጥብ አትመዋል። በፖሊቲካ ጉዳይ የተሰደዱት ደግሞ በአማራጭ ዕጦት ውሳኔያቸው አየር ላይ ነው።

የዐዩ መንገድ . . .

ይህ ሁሉ ሕይወት እና ሐሳብ በሚናጥበት የስደተኞች ምድር ወደ አገር ቤት ለመመለስ “የዐዩን ድፍረት ይስጥህ” የምትል ቀልድ ትደመጣለች። ዐዩ ከሁለት ዓመታት በፊት ወደ አሜሪካ ለመጓዝ 15 ሺሕ ዩሮ ከቤተሰቡ ይዞ የመጣ ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ነው። 15 ሺሕ ዩሮው በአጠቃላይ ለአሜሪካ ጉዞው (ፕሮሰሱ) ማስፈጸሚያ የተመደበለት ሲኾን ለዕለታዊው ወጪው ደግሞ እስከ አራት መቶ ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በየወሩ ይላክለት ነበር። ካልበቃው ደግሞ እጅግ የሚሳሱለት ዘመዶቹ ፈጥነው ይጸድቁበታል።

ከቁጠባ ይልቅ አለማባከንን የሚያስተምረው ዐጣ። ለወትሮው የስደተኞችን አርፍዶ መነሳትን የለመደ ቢኾንም ከብክነት አልታደገውም። አራት መቶ ዶላር ለወር አልበቃ እያለው ተቸገረ። ቀዳዳ ለመሸፈኛ ተብለው የሚላኩ ዩሮዎች ሊበግሩት አልተቻላቸውም። ወጪው ባስ ሲልበት ለአሜሪካ “ፕሮሰስ” የተባለችውን 15 ሺሕ ዩሮ ይዳብሳታል፤ ገንዘብ ይላካል- እርሱ ያጠፋል። ከተቀማጭ ዩሮ ላይ ይመዛል። በቀን ሦስት ጊዜ እየተመላለሰ ያስጨነቀው አስቀማጭ ባንክ ተቀማጭ ገንዘቡን እንዲወስድ ዐዩን እሰከ መገሰጥ የደረሰበት ጊዜም ነበር።

ለዐዩ ገንዘብ የልውውጥ ሳይኾን የነውጥ መሣርያ ኾነ። በሄደበት መሸታ ቤት ዶላር ይተኩሳል፤ ዮሮ ይወረውራል። የሚላከውን ጨምሮ ተቀማጩን ዩሮ ለማሟጠጥ ግን ስድስት ወራት በቂ ነበሩ። ይኼን የሰሙ ቤተሰቦች አንድ ዶለርም አንልክ ወደሚል ውሳኔ ተዛወሩ። ለወር ያህል የገዛቸውን የቤት ቁሳቁሶች በመሸጥ ኑሮን ታገላት፤ አልቻለም። አንድ ማለዳ ቆረጠ። የናይሮቢ ቆይታው ዓመት እንኳ ሳይኾነው ወደ እናት ምድሩ ተመለሰ።

ለብዙዎች ዐዩ የተጓዘው መንገድ ቀላል እና እኛም ልንከተለው እንችላለን የሚሉት ዐይነት አይደለም። ፖለቲካው ያስፈራቸዋል፤ ባዶ እጅ መመለሱ አንገት ያስደፋቸዋል። የያዟት ተስፋ ታጓጓቸዋለች፡፡ ያን ተስፋ መጠበቅ ደግሞ የረጂ ወገንን እጅ ማየትን ያስከትላል። ዶላርን በተስፋ መጠበቅ ለብዙዎች ፈተና ነው። በተለይ ዘመድ አዝማድ ለሌላቸው ከሚታሰበውም በላይ ከባድ ነው። በስደት ላይ ያለ ሌላ ስደት፤ ሁለተኛ ደረጃ ስደተኝነት የኾነባቸው ብዙ ናቸው።

የቢቸግር መፍትሄዎች . . .

የሰው እጅ ጥበቃ የሰለቻቸው ብልኀትን ፈጥረዋል። አንዳንዶቹ ብልኀቶች ዛሬ ነፍስን ከማዳን ነገን ደግሞ ተስፋ ከማድረግ ብቻ የመነጩ ናቸው። ብዙ የታሰበባቸው የሚመስሉ አይደሉም። ሴቶቹ የምሽት ዳንስ ቤቶችን በመጎብኘት የሚመጣውን የማታ ሲሳይ ይጠብቃሉ። ጥቂት የማይባሉ ወንዶች ደግሞ በፌስ ቡክ እና መሰል የማኅበራዊ ሚዲያዎች አማካይነት አውሮፓ የሚገኙ እና ለትዳር እና ለውሲብ የሚጓጉ በዕድሜ ገፋ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሴቶች ጋራ ግንኙነት በመመሥረት ተስፋ ላይ ራሳቸውን ይጥላሉ። የዕለት ወጭያቸውን ከመሸፈን ባሻገር የአውሮፓ ጉዞ ተስፋቸውን ብሩህ ለማድረግ ያታትራሉ።

በአብዛኛውን ጊዜ ጥንድ መኾን በብዙዎች የተመረጠ ነው። ጥንዶቹ ፍቅረኛ ወይም የትዳር አጋር ከኬንያ ውጭ ሊኖራቸው ይችላል። ይህ ግን አብሮ ከመኖር አያግዳቸውም። ካልተስማሙ በሳምንት ውስጥ በመለያየት ከቅርብ ጓደኛ ጋራ ሌላ ግንኙነት ቢመሠረት የሚገርም አይደለም። ዋናው ኑሮን ማሸነፍ ነው።

ለስድስት ዓመታት በናይሮቢ የቆየችው እና ወደ ካናዳ ለመብረር በዝግጅት ላይ ያለችው ሐረግ ይኼን መፍትሄ ከተጠቀሙት መካከል አንዷ ናት። በአንድ ወር ውስጥ ከሁለት ወንዶች ጋራ “ትዳርን” ሞክራው ታውቃለች። “ሁሉም በር ሲዘጋብህ ሰብረህ ከመውጣት ውጭ የተሻለ አማራጭ የለህም” ትላለች። ማንም ረዳት ያልነበራት ሐረግ ከለላ ለኾናት ኹሉ ጊዜያዊ ሚስት በመኾን ስድስቱን ዓመታት አሳልፋለች። “የእኔ አይግረምህ፣ ሕጋዊ ባሎቸው እንኳን አሜሪካ የሚኖሩ ጓደኞቼ እኔ ባለፍኩበት አልፈዋል።”

ይህ ዐይነቱ ፈጣን “የትዳር” ዝውውር ግን ኹሌ እንደታሰበው ኑሮን በመደጎም ብቻ አይጠናቀቅም። በተለይ የትዳር አጋሮቻቸው አሜሪካ ወይም ሌላ አገር የሚገኙ ስደተኞች ሌላ ያልተጠበቀ ውጤት በመፍጠር ተስፋቸውን ይሠብራል።  ወዳጆቻቸው ናይሮቢ የሚያደርጉትን በመስማት ቃል የገቡትን የአውሮፓ ጉዞ ይሰርዛሉ። ቀለበት ያወልቃሉ፤ ትዳርቸውንም ያፈርሳሉ። ብዙዎች በጊዜያዊው መፍትሄ ክፍተት ዕድሎቻቸውን አበላሽተዋል። ይህ ሁሉ ግን በአብዛኛው የሚኾነው የተገባው የቤተዘመድ የዶላር ድጎማ ሲጓደል ወይም ጭርሱኑ ሲቋረጥ ነው። . . .

ምርቃና ደጉ

አሁን ይህን ሁሉ ባለ ታሪክ ያቀፈቸው የበሬ ግንባሯ ክፍል መጋል ጀምራለች። ብዙኀኑም በቡናው ታጅቦ ወደ ምርቃናው ጥግ እየሄደ ነው። ይኼን ጊዜ ብዙኀኑ  ሞባይሉን ይጎረጉራል። ፌስቡኩን ይከፍታል። የሚጽፋቸውን ቃላቶች ይመርጣል። ጥያቄዎች ከወዲያ ወዲህ ይወናጨፋሉ። “ለዚያች አሮጊት ምን ብዬ ልጻፍላት”፣ “አቦ አሁን ምን ኬዝ ፈጥሬ ገንዘብ ልቀበላት?”  . . . ምርቃና ደጉ ሁሉን ደፋር ያደረጋል። ሙሉ ተስፋም ያስታጥቃል። አሁን ስለብዙ ጉዳዮች የሚታለምበት፤ ተስፋ የሚደረግበት ነው። ብርሃናማ ነገሮች ብቻ ወለል ብለው የሚታዩበት ክፍለ ጊዜ ነው። ጎላ ያለ ድምፅ አይሰማም። ሁሉም በራሱ ሐሳብ ተውጧል። ቅድምን የሚያስታውስ የለም። ነገን ግን በሙሉ ኀይላቸው እየሳሉ ነው፡፡ ዶላር . . . አሜሪካ . . .  ካናዳ . . . አውስትራሊያ . . . ። ኢትዮጵያ? No! No! No!

-

One Response to “ተስፈኝነት የማይጨልምበት ስደተኝነት”

  1. በጣም የሚያሳዝን እና የሚገርም ነገር ነው! ሌላ ምንም ማለት አይቻልም::
    እርግጠኛ ነኝ አቶ ነጋሶ የተሻለ ነገ ይመጣላቸዋል:: መለስ ስልጣን ሲለቅቅ (ሲለቅቁ)ፕሮፌሰር ፧ የተባበሩት መንግስታት አማካሪ ምናምን ምናምን ይሆናል አይደለ ተረቱ :)

  2. i’m really disappointed withdr.negasos monthly penstion money.the leading party tplf andhis cadres(kangaro make with him ridiculous game).how ot could be tha one who lead ethiopian for 5years on presdent..they decide 1197.60 it is less than 50€ very embarrassing judgement….those who make this!!!
    may god keep ethiopian for those tyrant administration

Leave a Reply

You must be to post a comment.

የአገር ቤት ጋዜጦች ምን ጻፉ

ዘወትር ማክሰኞ የሚታተመው አዲስ ፕሬስ ጋዜጣ የኅትመቱን ሲሶ ለዶክተር አሸብር አውሎታል። አወዛጋቢው ዶክተር አሸብር ከዚሁ ጋዜጣ ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ ሰጥተዋል። ከሰጧቸው መልሶች መካከል አወዛጋቢ የነበሩትን እነኾ። የንግድ ሥራ የጀመሩት ታጃኪስታን እንደነበረ በመግለጽ የሚጀምሩት ዶክተሩ “በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ሦስት ዋንጫ ያመጣኹ ብቸኛው ፕሬዝዳንት ነኝ” ሲሉ ራሳቸውን ያሞካሻሉ። የጋዜጣው ሪፖርተር በአልረታም ባይነት እንደሚታወቁ ጠቅሶ በፌዴሬሽን ውስጥ [...]

ዘወትር ማክሰኞ የሚታተመው አዲስ ፕሬስ ጋዜጣ የኅትመቱን ሲሶ ለዶክተር አሸብር አውሎታል። አወዛጋቢው ዶክተር አሸብር ከዚሁ ጋዜጣ ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ ሰጥተዋል። ከሰጧቸው መልሶች መካከል አወዛጋቢ የነበሩትን እነኾ።

የንግድ ሥራ የጀመሩት ታጃኪስታን እንደነበረ በመግለጽ የሚጀምሩት ዶክተሩ “በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ሦስት ዋንጫ ያመጣኹ ብቸኛው ፕሬዝዳንት ነኝ” ሲሉ ራሳቸውን ያሞካሻሉ። የጋዜጣው ሪፖርተር በአልረታም ባይነት እንደሚታወቁ ጠቅሶ በፌዴሬሽን ውስጥ በነበረው ውዝግብ እንዴት ተስፋ ሳይቆርጡ መቀጠል እንደቻሉ ሲጠይቃቸው፤ “እንደ ግለሰብ ተስፋ ልቆርጥ እችል ነበር፣ ተስፋ ያላስቆረጠኝ ለእውነት የሚፈርድ ሃቀኛ መንግሥት መኖሩ ነው፤ እውነትን ይዘህ ከተከራከርኽ ፍትሕን የማያጎድል መንግሥት መኖሩ በራሱ ጥንካሬ ይሰጣል” ሲሉ መንግሥትን የፍትሕ ጠባቂ አድርገው ለማሳየት ሞክረዋል።

መንግሥት ቀጣዩ ፕሬዝዳንት እርስዎ እንዲኾኑ በማሰብ በምርጫው እንዲያሸንፉ ድጋፍ አድርጎልዎታል ይባላል በሚል በጋዜጣው ሪፖርተር የተጠየቁት ዶክተር አሸብር ስለዚህ ጉዳይ ምንም የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ነው የገለፁት። ቀጥለውም “ለእኔ መንግሥት ድጋፍ አላደረገልኝም፤ መንግሥት ድጋፍ ያደረገው ለተቃዋሚዎች እና ለገዢው ፓርቲ ብቻ ነው” ብለዋል። ቀጣዩ ፕሬዝዳንት እንደሚኾኑ የተጠየቁት ዶክተር አሸብር እንዲህ አሉ- “ኢትዮጵያ የብዙ ብሔረሰቦች አገር ናት። ወንበሩ ደግሞ አንድ ነው። መንግሥት ያው መስጠት ላለበት ሰው ይሰጣል…።”

በዚሁ ሳምንት የወጣው አውራምባ ታይምስ የፖለቲካ ሽሙጥ በሚጽፍበት አምዱ ዶክተሩን እንዲህ ሲል ሸንቆጥ አድርጓቸዋል። “… ለጥርስ እንጂ ለእግር ኳስ ዶክተር አያስፈልግም! ከሚል ሰላማዊ ሰልፍ ጋራ ከፌዴሬሽን የተባረሩት ዶክተር አሸብር ቢያንስ ፕሬዝዳንት ኾነው ስለሚያውቁ የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ቢኾኑ ተቃውሞ የለኝም።… የፕሬዝዳንትነት የሥራ ልምድ ስላላቸው።”

አወዛጋቢው ዶክተር በዚህ ሰፊ ቃለ ምልልሳቸው “ኢሕአዴግ መጪውን ፓርላማ የፍጭት እና የክርክር ቦታ የሚያደርገው ይመስለኛል” ሲሉም ተናግረዋል። ቀጠሉ እና ደግሞ እንዲህ አሉ፦ “ኢሕአዴግ ከ97 በኋላ ብዙ ሠርቷል።…ተቃዋሚዎች አሜሪካን አገር የትም የትም ሲሉ ኢሕአዴግ ከሕዝቡ ጋራ ቁጭ ብሎ የሚለውን ሲሰማ ነበር።”

“አንድነቶች ተኩስ አቁመው ብርቱካንን ቢቀበሉስ”

ብርቱካን ልትፈታ እንደምትችል ጭምጭምታ እንዳለ የሚጠቋቁሙ ጽሑፎች በዚህ ሳምንት በወጡ ጋዜጦች ላይ ተነበዋል። ከእነዚህ ውስጥ አውራምባ ታይምስ በቅዳሜ እትሙ ያስነበበው ፊቸር አንዱ ነው። “አንድነት ብርቱካን ደፋ ቀና ብላ የሠራችው ቤት ነው። ስትመለስ ፈርሶ ካገኘቸው የሚደርስባት የመንፈስ ሥብራት ከሁለት ዓመቱ እስር እና በእስሩ ወቅትም ከደረሰባት የከበደ ይኾናል።” በመኾኑም አስቸኳይ የተኩስ አቁም አድርገው ብርትኳንን በአንድነት ስሜት ቢቀበሏት ይበጃል” ይላል የጽሑፉ መንፈስ። ይህን ማድረግ አለመቻል ግን ከራስ በላይ አለማሰብ ይኾናል” ሲል ፊቸሩ ሐሳቡን ያጠቃልላል። የእንግሊዝኛው ሪፖርተርም የብርቱካንን ጉዳይ ጉዳዬ ብሎ አንድ ጽሑፍ አስነበቧል። የብርቱካን የመፈታት ወሬ በጋዜጦችም በሕዝቡም ዘንድ እየተጠናከረ ይመስላል።

“ሻለቃ ዋሚ ቢራቱ 99 ዓመት ሞላቸው”

አውራምባ ታይምስ በስፖርት ገጹ የመጀመርያውን የማራቶን ሯጭ ሻለቃ ዋሚ ቢራቱን አነጋግሯል። ቃለ መጠይቁ አዝናኝ ነበር። እጅግ አስገራሚ ታሪኮችንም ያስነብባል። ዋሚ ቢራቱ በአትላንታ ኦሎምፒክ ድል ያደረጉትን እነ ኀይሌን፣ ፋጡማን እና ጌጤን ለመቀበል በዘበኝነት ይሠሩበት ከነበረበት ሲ.ኤም.ሲ አካባቢ እየሮጡ ቦሌ ደረሱ። የሚያውቃቸው ስለሌለ መግባት አልቻሉም። “መሠረት የጣልኩ እኔ ነኝ አስገቡኝ፤ ቢሉ ማን ይስማቸው። ከሕዝብ ጋራ መኪና አጅበው እየሮጡ እስከ አራት ኪሎ ጨፈሩ። በኋላ የስፖርት ቤተሰቡ አወቃቸው እና ባንዲራ አልብሶ ከእርሳቸው ጋራ መጨፈር ጀመረ። “ዋሚ አይረሳም ቅርሳችን ነው” እያለ። የአትሌቶቹ ደጋፊዎች፣ አድናቂዎች እና ዋሚ እየጨፈሩ ፒያሳ ደረሱ። ፒያሳ ግን ነገር ተበላሸ። ሰው ሲከተላቸው ያየ ፖሊስ ዱላ አወረደባቸው። “እኔን አይደለም የመታኸው ታሪክን ነው” አሉ ሻለቃ ዋሚ ቢራቱ።

በቃለ መጠይቁ መሀል ሰውየው ይቆጣሉ፣ “መንግሥት እንዴት አንድ መኪና አይሸልመኝም ሲሉ!” የሻለቃ ዋሚ ቢራቱ መተዳደርያ በአሁኑ ሰዓት 129 ብር የጡረታ ገንዘብ ብቻ እንደኾነም ይኸው ጋዜጣ አስነብቧል።

የሚያወፍሩት እና የሚያከሱት ኢትዮጵያዊው ዶክተር

ዶክተሩ ብርሃኔ ረዳዒ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የቀዶ ሕክምና ሐኪም ናቸው። መወፈር እና መክሳት ለሚፈልጉ የማወፈር እና የማስከሳት ሕክምናን ጀምረዋል። “ሐበሻ ያልወፈረ ማን ይወፍራል?” ሲሉ ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ ጋራ ባደረጉት ቃለ መጠይቅ ይጠይቃሉ? ሐበሻን የሚያወፍረው ደግሞ እንደርሳቸው አባባል እንጀራ ነው። ዶክተር ብርሃኔ ረኀብ ሌላኛው የውፍረት ምንጭ እንደኾነ አስረግጠው ይናገራሉ።  ዶክተሩ መወፈር ወይም መክሳት ለሚፈልጉ የራሳቸውን ሜኑ ሠርተው ያቀርባሉ። ለዚህ አገልግሎት የሚጠይቁት ክፍያ ከ2000 እስከ 2500 ብር ብቻ ነው። ደንበኞቻቸው የእርሳቸውን ሕክምና ተከታትለው ካልከሱ ብር ይመልሳሉ፤ የተባረኩ ዶክተር።

ታላቁ ሩጫ እየመጣ ነው

ዘንድሮ ለ10ኛ ጊዜ ነው የሚካሄደው፡፡ 35 ሺህ ህዝብ ይሳተፍበታል፡፡ ሰኞ ምዝገባ ይጀመራል፡፡ አዲስ አድማስ እንዳስነበበው የዘንድሮው ታላቁ ሩጫ በቤተመንግስት አያልፍም፡፡ አቅጣጫ ተቀይሯል፡፡ ሆኖም መነሻና መድረሻው ዘንድሮም መስቀል አደባባይ ነው፡፡ ታላቁ ሩጫ በአፍሪካ በታላቅነቱ አንደኛ ሲሆን የአለም አቀፍ ሚዲያዎችን ትኩረት በእጅጉ የሚስብ ነው፡፡

የሼህ አላሙዲን ሳውዲ ስታር ጋምቤላን እየጠቀለለ ነው

ሪፖርት በእንግሊዝኛ ሳውዲ ስታር ተጨማሪ 129 ሄክታር መሬት ለሩዝ ምርት እንደተሰጠው ዘግቧል፡፡ ከዚህ በፊት 10 ሺህ ሄክታር ተሰጥት ነበር፡፡ ይህ ድርጅት በአጠቃላይ የጠየቀው መሬት 300 ሺህ ሄክታር ነው፡፡ የወደፊት እቅዱ ደግሞ 500ሺህ ሄክታር ይደርሳል፡፡ የህንዱ ካራቱሪ ካምፓኒ የአዲስ አበባን ግማሽ የሚያህል መሬት በጋምቤላ መረከቡ መዘገቡ ይታወሳል፡፡

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

“Yoomi Laataa” የተሰኘው መጽሐፍ ትላንት ተመረቀ

“መጽሐፉ በኦሮሞ ሕዝብ ትግል ውስጥ ከፍተኛ ሚና የነበራቸውን የእነ ታደሰ ብሩ፣ ባሮ ቱምሳ፣ ዋቆ ጉቱ እና ሌሎችም በትግሉ ወቅት ደማቅ ታሪክ የነበራቸውን ግለሰቦች እንዲሁም የኦሮሞ ሕዝብን ከጭቆና ለማውጣት እና ነጻነትን ለማጎናጸፍ ሲንቀሳቀሱ የነበሩትን እንደ ሜጫ እና ቱለማ፣ ኦነግ እንዲሁም ዐበይት ድርጅቶችን ጨምሮ አሁን በፖለቲካ መድረኩ ላይ ከፍተኛውን ሚና በመጫወት ላይ እስከሚገኘው ኦ.ሕ.ዴ.ድ ድረስ ያሉ ድርጅቶችን ታሪክ፤ ሥነ ጽሑፋዊ በኾነ መልኩ በውብ ቋንቋ በጥልቀት እና በሥፋት ዳስሰው በማቅረባቸው በኦሮምኛ እንደተጻፈ ቋሚ የታሪክ ሰነድ ሊወሰድ ይችላል”

የኦሮምኛ የረጅም ልቦለድ ድርሰት የኾነው እና በኢሳያስ ኦርዶፋ የተጻፈው “Yoomi Laataa” የተሰኘው መጽሐፍ ትላንት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ሲኾን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ተመረቀ። የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር ከአርቲስቲክ ማተሚያ ቤት ጋራ በመተባበር ለኅትመት ያበቃው ይሕ መጽሐፍ በ279 ገጾች የተጠናቀረ ነው።

የመጽሐፉ ደራሲ አቶ ኢሳያስ ኦርዶፋ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የኦሮምኛ ክፍል ውስጥ ለረጅም ጊዜያት በጋዜጠኝነት ያገለገሉ ሲኾን ከዚህ መጽሐፍ በፊት ሦስት የኦሮምኛ ልቦለድ መጻሕፍትን ለኅትመት አብቅቷል። ይኼኛው አራተኛ መጽሐፋቸው የደራሲውን እውነተኛ የሕይወት ታሪክ መሠረት ያደረገ ሲኾን የመጽሐፉ ጥንስስ የጀመረው ከዐሥራ አንድ ዓመት በፊት እንደኾነ የደራሲው የቅርብ ጓደኛ እና የምርቃት ፕሮግራሙ ዋና አስተባባሪ አቶ ዘውዱ ረጋሳ ገልጸዋል።

አቶ ዘውዱ አያይዘው “መጽሐፉ በኦሮሞ ሕዝብ ትግል ውስጥ ከፍተኛ ሚና የነበራቸውን የእነ ታደሰ ብሩ፣ ባሮ ቱምሳ፣ ዋቆ ጉቱ እና ሌሎችም በትግሉ ወቅት ደማቅ ታሪክ የነበራቸውን ግለሰቦች እንዲሁም የኦሮሞ ሕዝብን ከጭቆና ለማውጣት እና ነጻነትን ለማጎናጸፍ ሲንቀሳቀሱ የነበሩትን እንደ ሜጫ እና ቱለማ፣ ኦነግ እንዲሁም ዐበይት ድርጅቶችን ጨምሮ አሁን በፖለቲካ መድረኩ ላይ ከፍተኛውን ሚና በመጫወት ላይ እስከሚገኘው ኦ.ሕ.ዴ.ድ ድረስ ያሉ ድርጅቶችን ታሪክ፤ ሥነ ጽሑፋዊ በኾነ መልኩ በውብ ቋንቋ በጥልቀት እና በሥፋት ዳስሰው በማቅረባቸው በኦሮምኛ እንደተጻፈ ቋሚ የታሪክ ሰነድ ሊወሰድ ይችላል” ብለዋል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

“ትዝታህ” ፊልም ባለፈው አርብ ተመረቀ

ይኸው “ትዝታህ” የተሰኘው ፊልም ዘውጉ የፍቅር ድራማ ሲኾን በፊልሙ ላይ ግሩም ኤርሚያስ፣ ሜላት አሰፋ፣ አንተነህ አስረስ፣ ታዬ ወንድሙ፣ አስቴር መኮንን፣ በ “ገመና” ሳምንታዊ የቴሌቪዥን ድራማ ላይ ዝናን እያገኘ የመጣው መሐመድ ሚፍታህ፣ ቢንያም በቀለ፣ ኤፍሬም ልሳኑ፣ መድሃኒት ጌታቸው እና ሌሎችም ይተውኑበታል።

በሔደን ፊልም ፕሮዳክሽን የተሠራው “ትዝታህ” የተሰኘው የአንድ ሰዓት ከ35 ደቂቃ ፊልም አርብ መስከረም 20 ቀን 2002 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ቴአትር እና ባህል አዳራሽ ተመረቀ። ፊልሙን ዳይሬክት ያደረገው ሀብታሙ ኅብረ ወርቅ ሲኾን ፕሮዲውሰሩ ደግሞ ስንሻው ዓለሙ ነው። ዳይሬክተሩ ሀብታሙ ኅብረ ወርቅ የፊልሙን ኦርጂናል ድርሰት በአባቱ እውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ ቢጽፈውም “ኮሞሮስ” የተሰኘው ፊልም ስክሪፕት ፀሐፊ መቅደስ፣ የፊልም ተዋናይ ግሩም ኤርሚያስ እና አንተነህ አስረስ በጋራ ለፊልም በሚበቃ መልኩ እንዳዳበሩት የፊልሙ ዳይሬክተሩ ገልጿል።

ዳይሬክተሩ ለአዲስ ነገር እንደገለጸው የፊልሙ አጠቃላይ ሥራ አንድ ዓመት ከሰባት ወር ያህል ፈጅቷል። ይህንኑ ፊልም ለመሥራትም 400,000.00 (አራት መቶ ሺሕ ብር) አስፈላጊ ኾኖ መገኘቱን ጨምሮ ገልጿል። ይኸው “ትዝታህ” የተሰኘው ፊልም ዘውጉ የፍቅር ድራማ ሲኾን በፊልሙ ላይ ግሩም ኤርሚያስ፣ ሜላት አሰፋ፣ አንተነህ አስረስ፣ ታዬ ወንድሙ፣ አስቴር መኮንን፣ በ “ገመና” ሳምንታዊ የቴሌቪዥን ድራማ ላይ ዝናን እያገኘ የመጣው መሐመድ ሚፍታህ፣ ቢንያም በቀለ፣ ኤፍሬም ልሳኑ፣ መድሃኒት ጌታቸው እና ሌሎችም ይተውኑበታል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

[አንድ ለቅዳሜ!] ይቅርታ ለብርቱካን ወይስ ይቅርታ ከብርቱካን? ይቅር ባዩ ማነው?

አቶ መለስ በኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲው ንግግራቸው ወቅት ስለብርቱካን ዳግም መለቀቅ ያቀረቡትን “የመፍትሔ አቅጣጫ” ነው። በአጭሩ አቶ መለስ ብርቱካን “ድጋሚ ይቅርታ ትጠይቅና እንለቃታለን” እያሉን ነው። መለስ “ካለፈው ታሪኳ አንጻር ድጋሚ ይቅርታ ብትጠይቅ አይገርመኝም፤ መንግሥትም ከልምዱ አኳያ ይቅርታ ቢያደርግላት አይደኝቀንም” ብለዋል። ትርጉም ግልጽ መሰለኝ።እንዲያውም አይጋ ፎረም ላይ እንዳነበብኩት ከሆነ እርሷ ብቻ ሳትሆን ቤተሰብም፣ ጠበቃም…ስለእርሷ ተገብቶ ይቅርታ ሊጠይቅላት እንደሚችል አንቀጽ ተጠቅሶ “አቅጣጫው” ተብራርቷል። በአጭሩ ጥሪው “እርሷ እምቢ ማለቷ ስለማይቀር እባካችሁ አንዳችሁ ይቅርታ ጠይቁላትና እንገላገል” ይመስላል። በቀዳሚው የቅንጅት አመራሮች እስር ወቅት ፕሮፌሰር መንስፍ ወልደ ማርያም “ለኢሕአዴግ የማርያም መንገድ እንስጠው” በማለት ታሳሪዎቹ እንዲፈርሙ ሐሳብ አቅርበው ነበር ይባላል። ይህም ሌላ “የማርያም መንገድ” ጥያቄ ይሆን?

ሞራል በፖለቲካ ውስጥ ያለውን ቦታ ባስታወስኩ ቁጥር የዛሬዎቹ ይቅርታ ጠያቂ እና ሰጪዎች ልዩነት አብሮ ይመጣብኛል። ብርቱካ እና መለስ የሁለት ትውልድ ብቻ ሳይሆን የሁለት ዓለምም ሰዎች ናቸው (“መለስ” ስል አቶ መለስን ብቻ ማለቴ አይደለም፤ “ብርቱካን” ስል የእርሷን ሐሳብ የሚጋሩ በተለይም የትውልድ አቻዎቿን ማለቴ እንደሆነ ሁሉ)። በዚህ ጉዳይ ላይ በሌላ ጽሑፍ እመለስበት ይሆናል፤ መለስ፣ ብርቱካንን እና ቴዲን ሊረዷቸው ያልቻሉበትን ምክንያት ፍለጋ። ለመሆኑ አሁን ይቅርታ ጠያቂው ማነው? ይቅርታ ሰጪውስ? ብርቱካን የእነአቶ መለስን ይቅርታ ትፈልጋለች ወይስ እነአቶ መለስ የእርሷ ይቅርታ ይገባቸዋል? ዓለም ይህን አትፈቅድ ይሆናል እንጂ ለነገሩስ በአደባባይ ብርቱካንንም ሆነ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ መጠየቅ የነበረባቸው አሳሪዎቿ ነበሩ።

imgres

ብርቱካን ለዳግም እስራት ከተዳረገች ጀምሮ የኢትዮጵያ ፖለቲካ አንዳች ዓይነት ለውጥ ውስጥ ሊገባ እንደሚችል የገመቱ ጥቂቶች ሳይሆኑ አይቀሩም። ለውጡ እጅግ ለስላሳና ገር የሚመስል ነገር ግን ብዙ ዜጎች የሞራል እና የፖለቲካ ጥያቄዎችን መላልሰው እንዲያስቡ የሚያደርግ ለስላሳ አብዮት መሆኑን እየቆየም ቢሆን መረዳት አዳጋች አልሆነም። አንድ ነገር ግን እርግጥ ነው፤ ለራሷ ለብርቱካን ጭምር መታሰሯ የሚፈጥረው ውጤት ይህ ይሆናል ብሎ መረዳት እጅግ አስቸጋሪ ነበር፤ የቀደመ ተሞክሮ ቀርቶ የበሰለ ንግግር እንኳን ያልተደረገበት የትግል ስልት በመሆኑ።

አለመታደል ሆኖ አቶ መለስ እና ብዙዎቹ ተከታዮቻቸው አንድ የማይወዱት የአብዮት አይነትና ቀለም አለ፤ ብርቱካናማ አብዮት። ለክፋቱ ደግሞ ልጅቷ (እንዲህ እንድጠራት ይፈቀድልኝ) ስሟ ብርቱካን ሆኖ ተገኘ። በሌላ ኢሕአዴግ ፈጽሞ ባልገመተው ምክንያትም ልጅቷ የአንድ ዝምተኛ አብዮት ተምሳሌት ለመሆን በቃች። የሞራል ልዕልና፣ የሰብአዊ ማንነት ክብር ፖለቲካ ውስጥ ዋጋ ያለው የአመለካከት መሠረት፣ እንዲሁም የፖለቲካ ትግል መሣሪያ ሊሆን እንደሚቸል በተግባር ለማሳየት የሞከረ ፖለቲከኛ ሲያጋጥመን ቢያንስ ለእኔ ትውልድ የመጀመሪያችን ነው። ይህን የምታደርገው አንዲት ወጣት እና የተማረች ሴት መሆኗ ደግሞ ነገሩን የበለጠ ያጎላዋል። ከዚያም በፊት በሞራልና በሰብአዊ ክብር መነሻነት መንግሥትን የተቹ፣ ሹመኞችን የሞገቱ ሰዎች ቢኖሩም እነዚህ ሰዎች በአብዛኛው የፖለቲካ ስልጣንን የሚፈልጉ አልነበሩም። ፖለቲከኞቹ ደግሞ የብርቱካንን እጣ ለመጋፈጥ አልፈቀዱ ይሆናል።

ብርቱካን ዳግም የታሰረችበት ሁኔታ ለብዙ ኢትዮጵያውያን አሳዛኝ ብቻ ሳይሆን አሳፋሪም ጭምር እንደሚሆን አምናለሁ። ሐዘኑም ሆነ እፍረቱ ድርጊቱ በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ ባህላዊ እና ወቅታዊ ዳራ ውስጥ ከሚኖረው ትርጉም የሚመነጭ ነው። ብርቱካንን ማሰር ለኢህአዴግ የሚያስገኝለት ፖለቲካዊ ጥቅም ከደረሰበት ፖለቲካዊ ኪሳራ ጋራ ሲነጻጸር እጅግ ያነሰ ነው። በግሌ ብርቱካን ባትታሰር ኖሮ በ2002 ምርጫ ላይ ሊኖር ይችል የነበረው ለውጥ ኢሕአዴግን ሊያርበተብተው ከሚችልበት ደረጃ ስለመድረሱ  እጠራጠራለሁ። በአንጻሩ ግን ብርቱካንን በማሰሩ ኢሕአዴግ ከራሱ አባላት ጭምር ተቃውሞ እንደሚነሳበት ያልሰሙት ብርቱካንን ለወራት ለብቻዋ እንድትታሰር፣ ሰው እንዳይጠይቃት የወሰኑት “ፍጥረታት” ብቻ ናቸው።

ከአገራችን ባህል አንጻርም ቢታይ ብርቱካንን ማሰር የፈሪ እና የጨካኝ ሰው ተግባር ነው። በቀድሞው እስራት የተለየቻትን ሕጻን ልጇን እና የምትረዳቸውን እናቷን እንኳን የሚያስብ ማንኛውም ሰው ፍትሕ የመስጠት ሸክሙን የሚጥለው በኢሕአዴግ/መለስ ላይ እንጂ በብርቱካን ላይ አይደለም። አንድ ሰሞን ብርቱካን መታሰሯ ሕጋዊ እና ተገቢ መሆኑን ለማስረዳት በየመስሪያ ቤቱ ጭምር ሰበካ ተጀምሮ ነበር። ሕዝብ ጉም ጉም ስላበዛ ዝም ለማሰኘት ነበር። የሕዝቡ ጥያቄ የተነሳው የአንቀጹን ቁጥር ባለማወቁ ይመስል ውይይቱ የጥናት ክበብ መስሎ ነበር።

ብርቱካን የታሰረችበት ወቅትም ቢሆን ክርክሩን ሁሉ ያለጥርጥር ለእርሷ የሚያጋድል ያደርገዋል። ሲጀመር ብርቱካን አልዋሸችም፤ ስለዚህ የምታስተባብለው ነገር የለም። ንግግሩ ውሸት ነበር ከተባለም “የዋሸችው” ብርቱካን ብቻ አልነበረችም። በወቅቱ የአገሪቱ ፖለቲካ ከምርጫ 97 ሕመሙ ገና ማገገም እንኳን አልጀመረም። ለዚህ ሒደት በጎ አስተዋጽኦ ለማድረግ ከሚችሉት አንዷን ለዚያውም ብቸኛዋን ሴት ነጥሎ ማሰር ስሙ ምን ይባለል? አመክንዮ ኢሕአድግኛ። መቼም ብርቱካንን ከታሰረች በኋላ እንዳትጎበኝ፣ ጠበቃዋን እንዳታናግር ወዘተ ስላደረገው  ሕግ እና የሕግ የበላይነት መነጋገሩ ድካም ነው። ኢሕአዴግን እንደጎዳው ግን እውነት ነው።

የብርቱካንን መታሰር የሚቃወሙ ሰዎች ሌላው ቀርቶ በበሽተኛው የኢትዮጵያ የኢንተርኔት መረብ እንኳን ድምጻቸውን እያሰሙ ነው። የኢትዮጵያውያንን የፌስቡክን ገጾች የብርቱካን ፎቶዎች ሞልተውታል። በስሟ የተከፈቱ ድረ ገጾች እና ደጋፊዎች እየበዙ ነው…

ከዚህ ሁሉ ነገር በኋላ ብርቱካን በመታሰሯ ኢትዮጵያ እና ፖለቲካችን ምን እንደሚያተርፉ፣ ኢህአዴግ ምን እንደሚጠቀም የሚያውቁት አንድዬ ናቸው፤ ለልማዱ “አቡዬ ናቸው ወይም ሥላሴዎች ናቸው” ነበር የሚባለው። “እኛም አለን ሙዚቃ፣ ስሜት የሚያነቃ” መሆኑ ነው።

በመጨረሻ የማነሳው አቶ መለስ በኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲው ንግግራቸው ወቅት ስለብርቱካን ዳግም መለቀቅ ያቀረቡትን “የመፍትሔ አቅጣጫ” ነው። በአጭሩ አቶ መለስ ብርቱካን “ድጋሚ ይቅርታ ትጠይቅና እንለቃታለን” እያሉን ነው። መለስ “ካለፈው ታሪኳ አንጻር ድጋሚ ይቅርታ ብትጠይቅ አይገርመኝም፤ መንግሥትም ከልምዱ አኳያ ይቅርታ ቢያደርግላት አይደኝቀንም” ብለዋል። ትርጉም ግልጽ መሰለኝ።እንዲያውም አይጋ ፎረም ላይ እንዳነበብኩት ከሆነ እርሷ ብቻ ሳትሆን ቤተሰብም፣ ጠበቃም…ስለእርሷ ተገብቶ ይቅርታ ሊጠይቅላት እንደሚችል አንቀጽ ተጠቅሶ “አቅጣጫው” ተብራርቷል። በአጭሩ ጥሪው “እርሷ እምቢ ማለቷ ስለማይቀር እባካችሁ አንዳችሁ ይቅርታ ጠይቁላትና እንገላገል” ይመስላል። በቀዳሚው የቅንጅት አመራሮች እስር ወቅት ፕሮፌሰር መንስፍ ወልደ ማርያም “ለኢሕአዴግ የማርያም መንገድ እንስጠው” በማለት ታሳሪዎቹ እንዲፈርሙ  ሐሳብ አቅርበው ነበር ይባላል። ይህም ሌላ “የማርያም መንገድ” ጥያቄ ይሆን?

ሞራል በፖለቲካ ውስጥ ያለውን ቦታ ባስታወስኩ ቁጥር የዛሬዎቹ ይቅርታ ጠያቂ እና ሰጪዎች ልዩነት አብሮ ይመጣብኛል። ብርቱካ እና መለስ የሁለት ትውልድ ብቻ ሳይሆን የሁለት ዓለምም ሰዎች ናቸው (“መለስ” ስል አቶ መለስን ብቻ ማለቴ አይደለም፤ “ብርቱካን” ስል የእርሷን ሐሳብ የሚጋሩ በተለይም የትውልድ አቻዎቿን ማለቴ እንደሆነ ሁሉ)። በዚህ ጉዳይ ላይ በሌላ ጽሑፍ እመለስበት ይሆናል፤ መለስ፣ ብርቱካንን እና ቴዲን ሊረዷቸው ያልቻሉበትን ምክንያት ፍለጋ። ለመሆኑ አሁን ይቅርታ ጠያቂው ማነው? ይቅርታ ሰጪውስ? ብርቱካን የእነአቶ መለስን ይቅርታ ትፈልጋለች ወይስ እነአቶ መለስ የእርሷ ይቅርታ ይገባቸዋል? ዓለም ይህን አትፈቅድ ይሆናል እንጂ ለነገሩስ በአደባባይ ብርቱካንንም ሆነ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ መጠየቅ የነበረባቸው አሳሪዎቿ ነበሩ። “ለፕሮቶኮል” ሲባል ይህ ቢቀር እንኳን በአደባባይ ወጥቶ “ይቅርታ ትጠይቀን” እያሉ አለመመጻደቅ እንዴት ጨዋነት ነበር?

እንደ ብዙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ሁሉ ብርቱካን ተፈታ ማየትን እናፈቃለሁ። የምትፈታበትን ሒደት ከአቶ መለስም ሆነ ከደጋፊዎቿ በበለጠ ሁኔታ የምትወስነው እርሷው ራሷ ብቻ እንደሆነች እረዳለሁ። በማንኛውም እርሷ በምትፈቅደው ምክንያትና መንገድ ብትፈታ እወዳለሁ። የምትፈታበት መንገድ እርሷ በወከለችው ዝምተኛ አብዮት ላይ የሚኖረው ተጽእኖ ምን ሊሆን እንደሚቸልም ለማየት እጓጓለሁ።

ከዚህ በተረፈ ግን ይቅርታ መጠይቅም ሆነ ይቅርታ መስጠት በሁሉም የአገራችን ባህሎች የተከበረ አስተሳሰብ እና የአኗኗር ዘይቤ በመሆኑ መሠረታዊ ባህርይው የፖለቲከኞች መቀለጃ እንዳይሆን መከላከል ያለብን ይመስለኛል። ይቅርታ በሕግም ሆነ በፍልስፍና ዘርፍ ትልቅ ግምት የሚሰጠው ረቂቅ እሴት ነው። በሕግ፣ በትምህርት፣ በቅጣት፣ በሽልማት ወዘተ ታግዞ እንኳን ቢሆን ፍጽም መሆን የማይችለውን የሰው ግላዊና ማኅበራዊ ሕይወት ከፍጹም ክስረት፣ ከማያባራ መፈራረስ የሚታደገው አንዱ መሣሪያ ይቅርታ ነው። አሁን እንደሚባለው ግን ይቅርታ ተራ የጠላት ማዋረጃ መሣሪያ መሆኑ አዲስ የፖለቲካ ባህላችን እየሆነ ይመስላል። ይቅርታ ጠያቂም እየዋሸ፣ ይቅርታ ሰጪም እየዋሸ፣ ሁለቱም መዋሸታቸውን እየተዋወቁ የሚደረግ ይቅርታ በአረም ያስመልሳል፤ ሁለቱም በይቅርታው አይማሩና። አልተማሩምና።

በነገራችን ላይ

(“በነገራችን ላይ’ ራሷ ሌላ በነገራችን ላይ ሳይስፈልጋት አልቀረም። አንዳንድ አንባቢዎች “በነገራችን ላይ” የዋናው ጽሑፍ አካል እየመሰላቸው ሁለቱ ክፍሎች የተዘበራረቁ ሐሳቦች የቀረቡባቸው እንደመሰላቸው መረዳት ችያለሁ። “በነገራችን ላይ” ተብሎ የሚቀጠለው ጉዳይ ከፍ ሲል ከተወሳው ጉዳይ የተለየ መሆኑን በድጋሚ ላስታውስ። ፈረንጆቹ  “ባይ ዘ ዌይ” አለዚያም “ፖስት ስክሪፕት” እንደሚሉት መሆኑ ነው፤ በኋላ የተጨመረ፤ ከቀዳሚው ጋራ የግድ ተፈጥሯዊ ግንኙነት የሌለው፤ ነገር ግን ሊጠቀስ የሚገባው።)

በአዲሱ ዓመት የመንግሥት ሹመኞች ሀብትና ንብረታቸውን ማስመዝገብ እንደሚጀምሩ ከወዲሁ ቃል እየተገባ ነው። የጸረ ሙስና ኮሚሽን በየቀኑ በኢቲቪ “አደራ ተባበሩኝ” እያለ ተማጽኖውን ከወዲሁ ጀምሯል። እኔን የናፈቀኝ ግን ሁለት ነገር ነው። አንደኛ፤ ምዝገባው የሚጀምረው ከየት ነው፤ ከላይ ነው ከታች? መቼም ድሮ ድሮ ሁሏም ነገር በስራ አስፈጻሚና በማእከላዊ ኮሚቴ ተወስና ነበር “ወደ ታች” የሚትወርደው። አሁንስ? ከታች ይጀመር ከተባለ ተራው እላይ እስኪደርስ የአመራር ለውጡ እንዲዘገይ በሰላማዊ ሰልፍ እንጠይቃለን። ሁለተኛ፤ በቡድን ደረጃ ሀብታም አመራሮች ያሉት የኢህአዴግ ፓርቲ የትኛው ይሆን? ህወሓት ወይስ ኦሕዴድ? ታዳጊውስ? ወደ ኋላ የቀረውስ? በውጤት ተኮር ተሸላሚው ባለስልጣን ማን ይሆን? ከአጋር ፓርቲዎችስ ማን ይመራል? ስም የማዛወር ስራው ተጧጡፏል የሚባለው እውነት ነው እንዴ?

የሕጉን ቅጂ ስላላገኘሁት ዝርዝሩን አላነበብኩትም። ነገር ግን የንብረት ምዝገባው ተቃዋሚዎችንም ቢያንስ ከፍተኛ አመራሮቹን ማካተት ይኖርበታል። የንብረት ምዝገባ ጽንሰ ሐሳቡ የመንግሥት ገንዘብ እንዳይመዘበር ቢሆንም በተቃዋሚ ፓርቲዎችም ውስጥ የሚዘረፈው ገንዘብ የሕዝብ ነው። ምናልባት እነርሱ በኦዲት ሪፖርት ምርጫ ቦርድ ይቆጣጠራቸዋል ይባል ይሆናል፤ ግር እርሱ መንገድ አይሰራም። ስንት ገንዘብ ተበላ? ተዋዋሚ ፓርቲዎችን ከቡችላ ተስፈኛ መዝባሪዎች ለማጽዳት ንብረት ቢያስመዘግቡ ምንኛ ድንቅ ነበር። እስቲ ለማንኛውም ከመንግሥት ተሿሚዎች እንደጀምርና በሒደት እንደርስበታለን። የምዝገባው ውጤት መቼ ይፋ እንሚደረግ ይታወቃል?

3 Responses to “[አንድ ለቅዳሜ!] ይቅርታ ለብርቱካን ወይስ ይቅርታ ከብርቱካን? ይቅር ባዩ ማነው?”

  1. በጣም የሚያሳዝን እና የሚገርም ነገር ነው! ሌላ ምንም ማለት አይቻልም::
    እርግጠኛ ነኝ አቶ ነጋሶ የተሻለ ነገ ይመጣላቸዋል:: መለስ ስልጣን ሲለቅቅ (ሲለቅቁ)ፕሮፌሰር ፧ የተባበሩት መንግስታት አማካሪ ምናምን ምናምን ይሆናል አይደለ ተረቱ :)

  2. i’m really disappointed withdr.negasos monthly penstion money.the leading party tplf andhis cadres(kangaro make with him ridiculous game).how ot could be tha one who lead ethiopian for 5years on presdent..they decide 1197.60 it is less than 50€ very embarrassing judgement….those who make this!!!
    may god keep ethiopian for those tyrant administration

Leave a Reply

You must be to post a comment.

Bad Behavior has blocked 2073 access attempts in the last 7 days.