ማሃሙድ ጋ ጠብቂኝ! [ክፍል አንድ]
ስብሓት ‹‹ትኩሳት›› ብሎ በጠራው መጽሐፉ ጀርባ ላይ ምን አለ? “ወጣት ሁን” አለ፡፡ ቢመርህ ‹‹ሪቮሉሽን›› ታስነሳለህ፣ እጅግ ቢመርህ ራስህን ታጠፋለህ…፡፡ ለማንኛውም ወጣት ሁን፡፡ እኔ ግን እልኻለሁ፣ ወጣት መሆኑን ሁን፣ ነገር ግን ራስህን ከማጥፋትህ በፊት ፒያሳ ሂድ፤ ሐሳብህን ልትቀይር ትችላለህና፡፡ ለመሞትም ቢሆን የፒያሳን ያህል መልካም ሰፈር የለም፡፡ ቀባሪ አታጣም፤ በፒያሳ ሰው ባያይህ ማዘጋጃ ያይኻል፡፡ ለመሞትም ለመኖርም ስታስብ ፒያሳ ሂድ፡፡
This post is available in: Amharic
(መሀመድ ሰልማን)
ስብሓት “ትኩሳት” ብሎ በጠራው መጽሐፉ ጀርባ ላይ ምን አለ? “ወጣት ሁን” አለ፡፡ ቢመርህ “ሪቮሉሽን” ታስነሳለህ፣ እጅግ ቢመርህ ራስህን ታጠፋለህ…፡፡ ለማንኛውም ወጣት ሁን፡፡ እኔ ግን እልኻለሁ፣ ወጣት መሆኑን ሁን፣ ነገር ግን ራስህን ከማጥፋትህ በፊት ፒያሳ ሂድ፤ ሐሳብህን ልትቀይር ትችላለህና፡፡ ለመሞትም ቢሆን የፒያሳን ያህል መልካም ሰፈር የለም፡፡ ቀባሪ አታጣም፤ በፒያሳ ሰው ባያይህ ማዘጋጃ ያይኻል፡፡ ለመሞትም ለመኖርም ስታስብ ፒያሳ ሂድ፡፡
ፒያሳን ለሞትም ቢሆን የምመርጥልህ ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ሞት ሞት የሚሸት ስም በድፍን አዲስ አበባ የምታገኘውም ፒያሳ ነው፡፡ “ዶሮ ማነቂያ” ና “እሪ በከንቱ”ን እንደናሙና ውሰድ፡፡ ‹‹ተረት ሰፈር››ም አንተን ተረት ለማድረግ በሚያስችሉ ሕይወቶች የተሞላ መንደር ነው፤ ተረት መሆን ከፈለግህ፡፡ ፒያሳ ሥጋን ብቻ ሳይሆን ነፍስን ለማጥፋት ጭምር ምርጥ ሰፈር ናት፡፡ ካላመንክ ሙትና ሞክረው፡፡ ነግቶ ሳይመሽ ማዘጋጃ ይቀብርኻል፡፡ ስራ ለማቅለል ከፈለክ ደግሞ እዚያው ማዘጋጃ በር ላይ ጠጋ ብለህ ራስህን መድፋት ትችላለህ፡፡
ፒያሳ ወደ ሕይወትም ልትመልስህ ትችላለች፡፡ “እንዴት?” በለኝ፡፡ ወጣት ነህና ስብሓት በመከረህ መሰረት ራስህን የማጥፋት መብትህን ለመጠቀም ወደ ፒያሳ መጣህ እንበል፡፡ የት ጋር መሞት እንዳለብህ ለመምረጥ በፒያሳ ዞር ዞር ስትል እመነኝ ልብ የምታጠፋ ቆንጆ ታያለህ፡፡ ፀጉሯ የሚዘናፈል፣ ዳሌዋ የሚደንስ፣ ጡቶቿ የሚስቁ… መኖር የምታስመኝ ቆንጆ ልቅም ያለች ውብ 13 ቁጥር አውቶብስ ስትጠብቅ ታያታለህ፡፡ በዚህን ጊዜ ልብህ ይሸፍትና አንተም የተፈጥሮ ሞትህን መጠበቅ እንዳለብህ ትረዳለኽ፡፡ ከዚያች ቅፅበት ጀምሮ የ13 ቁጥር አውቶብስ ቋሚ ደንበኛ ሆነህ ታርፈዋለህ፡፡ አውቶብስና ሞት በራሳቸው ሰዓት እስኪመጡ ትጠብቃለህ። ፒያሳ ወደ ሕይወት መለሰችህ ማለት አይደል?
የፒያሳ ካፌዎች
ፒያሳ አንድ ሺህ አንድ መቶ ካፌዎች ያሉባት ቅመም የሆነች ሰፈር ናት፡፡ አንድ ሺህ አንድ መቶ ቆንጆ ልጃገረዶች ደግሞ በካፌዎቿ ውስጥ ተኮልኩለው ኮካ በ‹‹ስትሮ›› ይጠጣሉ፡፡ ‹‹ስትሮ›› ምን እንደሆነ ካላወቅክ የፒያሳ ልጅ አይደለህም ማለት ነው፡፡ ‹‹ስትሮ›› በቆንጆ ልጅ ከንፈርና በቆንጆ ብርጭቆ መሀል የተሰራ የላስቲክ ድልድይ ነው፡፡
ፒያሳ በካፌ ብዛት “ከምስራቅ አፍሪካ አንደኛ ናት፡፡” የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ነው እንዲህ ያለው ይባላል፡፡ እንደ ፒያሳ በካፌ የተጥለቀለቀ ሰፈር ከየት ይገኛል?! ከአምፒር እስከ ራስ መኮንን ድልድይ ብቻ በግራና በቀኝ የተሰለፉ ከ53 በላይ ካፌዎችን ልቆጥርልህ እችላለሁ፡፡ በእርግጥ ቆንጆ ልጃገረዶችና ወርቅ ቤቶች በመሀል በመሀል እየገቡ ቆጠራዬን አስተጓጉለዉት ይሆናል፡፡ ሆኖም ቁጥራቸው ከዚህ ቢልቅ እንጂ አያንስም፡፡
የፒያሳ ካፌዎች ልዩ ገፅታ ሁልጊዜ ሙሉ መሆናቸው ነው፡፡ አንዳንድ የፒያሳ ምሁራን ይህንን ጉዳይ ከመንግሥት የትምህርት ፖሊሲ ጋር ሊያይዙት ይሞክራሉ፡፡ እኔ ግን እላለሁ፤ ይህ የፒያሳ ልዩ ከራማ እንጂ ሌላ ምንም ሊሆን አይችልም፡፡
በፒያሳ ምርጥ ቡና ጠጥተህ ቀንህን ብሩህ ለማድረግ ካሻህ እነማንኪራ፣ እነ አፍሪካ፣ እነ ቶሞካ አሉልህ…፡፡ ቆንጆ ሻይ ከቆንጆ ልጃገረዶች ጋር ተፋጠህ ፉት ለማለት ካሻህ እነ ናምሩድ፣ እነ ራዜል፣ እነ ኢቪያን፣ እነ ሳሬም፣ እነ ኦስሎ፣ እነ አፕቪው፣ እነ ዲጄስ፣ እነ ሃርድኮር፣ እነ ጉድታይምስ አሉልህ፡፡ በተለይ በቅርቡ የተከፈተው ጉድ ታይምስ እንደ ደብልፌስ ጃኬት አይነት ተፈጥሮ ነበረው፡፡ ቀን ላይ ውብ ካፌ ኾኖ ይቆይና ማታ ላይ በፍጥነት ራሱን ቀይሮ ውብ ባር የመሆን ልዩ ጥበብ ነበረው፡፡ የጨርቆስ ልጆች ያለ ሰፈራቸው መጥተው በቡዳ በሉት መሰለኝ ሰሞኑን ተቃጠለ አሉ፡፡ ነፍስ ይማር!
ፎቅ ላይ ቂብ ብለህ ፒያሳንና ዜጎቿን ቁልቁል እየገረመምካቸው ለመዝናናት ካሻህ አራዳ ላይ የተሰቀሉ መዝናኛዎች አሉልህ፡፡ እነ አራዳ፣ እነ ሲድኒ፣ እነ ትዊንስ፣ እነ ቤስት በፒያሳ ከባህር ጠለል በላይ በምናምን ሺህ ጫማ ከፍታ የሚገኙ ካፌዎች ናቸው፡፡ አለልህ ደግሞ እንደ ዳሎል ተቀብሮ ያለ ካፌ፡፡ ቼንትሮ ይሰኛል፡፡
ልምከርህ! ፍቅረኛህ ፒዛ አማረኝ ካለችህ ፒያሳ ‹‹ፒዛ ኮርነር›› ውሰዳት፤ ከዚያ በኋላ ምን አለ በለኝ ፍቅሯ ካልጨመረ፡፡ ከዚህ ግብዣ በኋላ ካኮረፈችህ ግን ፒዛውን በልተህባታል ማለት ነው፡፡
ፒያሳ የኬክ አገር ናት፡፡ ዕድሜ ጠገቦቹን ….በዚህ አጋጣሚ ስማቸውን ማውሳት ግድ ይላል፡፡ በተለይ የ‹‹ኤንሪኮ›› ኬክ ይምጣብኝ፡፡ እስኪ በሞቴ ከዚህ ቤት ሂድና ኬክ እዘዝ፡፡ ኪኒን ኪኒን የሚያካክሉ ኬኮች ይቀርቡልኻል፡፡ የፒያሳ ልጅ ካልኾንክ ታኮርፋለህ፡፡ አንተ የለመድከው ድፎ ዳቦ የሚያካክሉ ኬኮችን ነዋ፡፡ እስኪ በሞቴ ቅመሰው፡፡ ከዚያ በአድናቆት ጭንቅላትህን ትወዘውዘዋለህ፡፡ ካልጣመህ ግን በኬክ አላደክም ማለት ነው፡፡ሂድና ሸዋ ዳቦ ተሰለፍ፡፡
ኤንሪኮ ውስጥ ዞር ዞር ብለህ ከጎንህ ያለውን ሰውዬ ገልመጥ ለማድረግ ሞክር፡፡ የሆነ ሰውዬ በትኩረት ኬክ ሲበላ ታየዋለህ፡፡ በእርግጠኝነት ስለሰውየው ብትጠይቅ ከተማዋ ውስጥ ካየኻቸው ሰማይ ጠቀስ ፎቆች የአንዱ ባለቤት ሆኖ ታገኘዋለህ፡፡ ፎቅ ባይኖረው እንኳ ፎቅ የሚሰራ ብር ያለው ለመሆኑ አትጠራጠር፡፡ ይህም ባይኖረው አንድ ቀን የማግኘት ተስፋ ያለው ነው። የኤንሪኮ የውስጥ ገፅታ አለመብለጭለጭ ተራ ቤት እንደሆነ ሊያስገምትህ ይችላል፡፡ አንድ ነገር ግን ላረጋግጥልህ፣ ይህ ቤት የሞጃዎች መናኸሪያ ነው፡፡ ስለዚህ አትንቀዥቀዥ፡፡

ከኤንሪኮ በኬክ መጋገር ጥበብ ተደንቀህ ስትወጣ ከፊት ለፊትህ የምታገኘው ‹‹እናት ህንፃ››ን ይሆናል፡፡ ይህ ህንጻ በቅርቡ ፒያሳን ከተቀላቀሉ ድንቅ ፎቆች አንዱና ዋንኛው ነው፡፡ በስነ -ህንፃ ታሪክ በምስራቅ አፍሪካ አንደኛ ከመሆኑም በላይ የሚመስለው የለም እየተባለ ነው፡፡ የፒያሳ ልጅ ካልኾንክ ይህን ህንፃ ተደግፈህ ፎቶ ብትነሳና ክፍለ ሀገር ላሉ ዘመዶችህ ብትልክላቸው ልጃችን አሜሪካ ገባ ብለው ድግስ እንደሚደግሱ አትጠራጠር፡፡ አዲስ አበባ ውብ ሕንጻ እንደሌለ የሚያስቡ ዲያስፖራዎችም ቢሆኑ እነሱ በማያውቁት አንድ የአውሮፓ ከተማ ያለ ሊመስላቸው ይችላል። (ካላመንከኝ ፎቶውን ተመልከት)
“ማሃሙድ ጋ ጠብቂኝ!”
አይበለውና ፒያሳ ሳለህ ድንገት ስሜትህ ቢመጣ እንደኔ የጨዋ ልጅ ከሆንክ ስልክህን በርበር አድርገህ ትደውልና እጩ ፍቅረኛህን ”ማሃሙድ ጋ ጠብቂኝ” ትላታለህ፡፡ “ኢንተር ላንጋኖ” ወስደህ፣ በድብቆቹ የስሞሽ ግርዶሽ ተጠልለህ፣ ልብ የሚሰልብ የስሞሽ ስነ ስርዓት ትፈፅማለህ፡፡ ከ”ማህሙድ ሙዚቃ ቤት” እስከ “ኢንተር ላንጋኖ” ለመሄድ የሦስት ደቂቃ ትእግስት ካጣኽ ፒያሳ ውላ ትግባ እንጂ ምን ጠፍቶ! በ”አምፒር” ወደ “ዶሮ ማነቂያ” ገባ እንዳልክ “ትሬይን ሀውስ” አለልህ፡፡ ይህ ቤት መሳሳሚያ ብቻ አይደለም ያዘጋጀልህ፡፡ አይበለውና ስሜትህ ከንፈር ብቻ የማያስታግሰው ከሆነብህ ይህ ቤት እጥር ምጥን ያለ ክፍል እጥር ምጥን ላለ ሰዓት ያከራይኻል፡፡ ፒያሳ ነው ያለኸው፡፡ ብታምነኝም ባታምነኝም ፒያሳ ከ10 በላይ መሳሳሚያ ቤቶችን በጉያዋ ይዛለች፡፡ ብዙዎቹ ስም አልባ ናቸው፡፡ ልብህ ከሚቆም አንድ አምስቱን ልጠቁምህ (ሊሞት የመጣን ሰው ወደ ሕይወት ለመመለስ አምስት መሳሳሚያ መቼ አነሰው?)፤ “ኢንተር ላንጋኖ”፣ “ትሬይን ሃውስ”፣ “ቢግ ትሪ”፣ “ጊቤ”፣ “ቬሮኒካ”…
“ማህሙድ ጋ” ቀጠሮ መያዝ እጅግ የሚመከር እንደሆነ በዚህ አጋጣሚ ሳልነግርህ አላልፍም፡፡ “ለምን?” በለኝ፡፡ አንደኛ ከማህሙድ ሙዚቃ ቤት የሚለቀቁ የማህሙድ ትዝታዎች በቀጠሮ ያስደገፈችህን ልጂትና ያደረሰችብህን ብስጭት የማስታገስ ኀይል አላቸው፡፡ አንዳንዴ ደግሞ የማህሙድ ወዳጅ የነበረው ጥላሁን ‹‹ቀጠሮ ይከበር›› ሲል ያንጎራጎረውን ዜማ ሊከፍቱልህ ይችላሉ፡፡ ሁለተኛ ‹‹ማሃሙድ ጋ›› አስተውለህ ከሆነ ብዙ ቆነጃጅት ብዙ ኮበሌዎችን ቆመው የሚጠብቁበት ስፍራ ነው፡፡ ዕድለኛ ከሆንክ ፍቅረኛዋ ቀርቶባት የተበሳጨችን ልጃገረድ ይዘህ እብስ ልትል ትችላለህ፡፡
ቀጠሮ ቦታ ሴቶች ቢያንስ ሰላሳ ደቂቃ አርፍደው እንደሚገኙ ሳታስተውል አልቀረህም፡፡ ማህሙድ ጋ ግን ለምን እንደሆነ ባላውቅም አረፈዱ ቢባል 20 ደቂቃ ነው፡፡ ቢያረፍዱብህም ከፊት ለፊትህ ብዙ የሚታይና የሚያዘናጋ ነገር አታጣም፡፡ ምሳሌ ለመጥቀስ ያህል ትልቁ የሀገራችን የህዝብ ሽንት ቤት የሚገኘው “ማህሙድ ሙዚቃ ቤት” ማዶ ነው፡፡ በቀን ሦስት ሺህ ሰዎች ይሳለሙታል፡፡ ሽንታቸው እንዳያመልጣቸው የሰጉ አዛውንት ምንትሳቸውን በእጃቸው ደግፈው ወደዚህ ሽንት ቤት እየተወላገዱ ሲገቡ እያየህ መሳቅ ትችላለህ፡፡ ከፈለክ “ሰው የተፈጥሮን ጥሪ ለመመለስ እንደሚጣደፈው ለቀጠሮም ምን አለ ተመሳሳይ ጥድፊያ ቢያሳይ” እያልክ ትፈላሰፋለህ፡፡
ሽንት ያጣደፋቸውን ምእመናን ማየት ከሰለቸህ ቀና በል፡፡ አይንህ ከሕዝብ ሽንት ቤት ወደ ሕዝብ ሶኒክ ስክሪን ይወረወራል፡፡ ፒያሳ በቅርቡ ራሷን ከእህት ከተሞች ጋር ለማስተካከል ያስተከለችው ይህ ትልቅ ዲጂታል ስክሪን የማያሳይህ ነገር የለም፡፡ ከቶሚና ጄሪ አባሮሽ ጀምሮ እስከ ሕገ መንግሥቱ አንቀጾች ይተነትንልኻል፡፡ ሕገ መንግሥቱ የብሔር ብሔረሰቦችን እኩልነት እንዴት እንዳስከበረ ካልገባህ አንቀጽ በአንቀጽ ያስረዳኻል፤ ትንሽ ከቆየህም የሴቶች እኩልነት በአገራችን በአያሌው እየሰፈነ እንደሆነ ያሳይኻል፤ ይሄኔ ከሴት ጓደኛህ ጋር የያዝከው ቀጠሮህ ትዝ ይልኻል፡፡ ሶኒክ ስክሪኑ ላይ በሚታየው የሕገ መንግስቱ አንቀጽ ውስጥ እንዲህ የሚል ነገር እንዲካተትልህ ትመኛለህ፡፡ ‹‹የሴቶች እኩልነት ቀጠሮ በማክበርም ጭምር ይረጋገጥ።››
አይንህን ከሶኒክ ስክሪኑ ስትነቅል የቀጠርካት ልጅ አበባ መስላ ከተፍ ትላለች፡፡ ጉንጮችህን ሳም ሳም፣ እቅፍ እቅፍ ስታደርግህ ንዴትህ ድራሹኑ ይጠፋል፡፡ ጭራሽ ቀጠሮ ማርፈዷ ተዘንግቶህ አንተው ራስህ “አረፈድኩብሽ አይደል” ልትል ይቃጣኻል፡፡ ፒያሳ! (ክፍል ሁለት ይቀጥላል)



hahaha, I like your way of expression that helps me to imagine piassa’s surrounding as an old movie. Thanks|!
እጅግ ደስ ብሎኝ ነው ያነበብኩት: አዲስ ነገር ሁሌም አዲስ ነው——–
ዋው ቢያሳ በደምብ ተገልጿል፡፡ ደስ ይላል ያዝናናል፡፡ @ጸሃፊው ምነው እነ ሳሬምን ስታነሳ “ቲ ሩም”ን ዘለልከው፡፡ ምነው ስለኬክ ስታነሳ “ቲ ሩም” ስላለው ቦክሰኛ ኬክ አላነሳህም?
esu eko ye shebawoch new
i second u on that elu..lol
Love it, keep the good work
wow. I like it.
I feel like – do I know piassa?
wow,muhamad,
you are amazing writer. i bet, you will be one of the famous writers in Ethiopia. wow!
you took me somewhere else. i cannot stop reading you. Egzer yibarkih
I like it, very much eager to read part 2.
Thanks
እንዴ የቲሩም ፒዛስ? ሲኒማ ኢትዮጵያስ? እነ የፒያሳ ቬጋስስ?
ታላቅ አድናቆትና ምስጋና ለጸሓፊው ይድረስ!
Waw, I like this article so mach. I can’t wait to read z second part. Regarding Mehamud, my wife used to say me “ende fara mehamud gar atekteregn” I never forget this in my life…………
Woy Addis Abeba woy Arada hoy,
Agerim indesew yinafiqal woy?(courtesy Mengistu Lemma)
Immiye Trianon inna Capucinowa, Immiye King George Bar inna esspressowa.Qidime Enricho inegnih neberu Wannawochu.
Ganochu tteffunna minchetoch Gaan honu.Benie ayn malet new.
Woy Gizie!!!!!!!!!!
Arqaadeuos…this is our time, and therefore our own cafes!!
Thanks , it shows Piassa like a fim.
i cant wait to read Part 2.
What an interesting way of writing… it catches readers’ attention.
I can’t wait to read the second part…
Keep it up man! I hope AddisNegerOnline will sign you as their regular columnist (if you aren’t already).
GBU
Isubalew
Ke addis ababa seferoch hulu piassan endemiafeqir sew and hulet neger,
1. Sunshine Bar / and its unparalled music
2. Krayasis Pastry next to it / and their ever same famous Gojo cakes
3. Mekonnen Bar and the Baklaba famous for decades
4. Gebretensae where i ate my first baklaba
4 Dalol |Music shop next to cinema ethiopia that always gives the soundtrack of a Piassa scenery
5. The Itegue Taytu Hotel and its surrounding that literally never sleeps
6. Mekonnen Bridge
Ere benatih betizita atasmezmizegn
Mohammed,
It looks like we have a rough diamond in you waiting to be cut out into another Adam Reta!! Thumbs Up!!
ብራቮ ማሜ…ጣመን ድገመን!!!
Lal
You are right.
‘Hulum duroo qerre’ honobign noew.
Bravoooooooooooo Article!!!
Tell us about ye arada lijoch too.
i like it
What a nice piece and what an amazing descriptive skill. I almost forgot how much I miss Addis and Piasa. Thanks for reminding me how beautiful life could be.
Very nice writing i like it ! Keep up the good work !!! 10Q.
i read this three times. so entertaining and so engaging. i saw some quality from the writer. something different.
Wow Wow Wow I cant stop reading it again and again I do appreciate Mamhammed for his extraordinary and entertaining article. Yebeza Misgana lante yehun!
simply wonderful…no words for it. hurry to read part two and hurry to return my country and seee enat building..loooool
Please write part two as soon as possible;you are special though you don’t disclose your talent.Waiting for, mahammed.
i love zt area. i used to go zr every single day. walking from cinema empire to ras makonne bridge and back or just standing near sun shine bar watching those beautyful girls, i miss all that. who knows one day, very soon, i will be there. where i belong. god bless u. u brought back all good
memories.c u just outside omar kayam
A very good writing. It’s descriptive and entertaining. But I guess you forget the Baklaba. You should also mention about Kryiazis and Ras Mekonen Bar. It’s just a suggestion. Bye
I used to work in Piassa for seven years.My memory was the sudanese,Asian and oldies musik from the famous musik shop ????…every mornning they will open a fine musik (the place is next to cenema Ethiopia and Triannon).Because of this I will take a long way taxi (paying 1 birr), rather than the short way (for 50 cents)…every dayyyyyyyyy…..oooooooo old piassa!