ነፃነትን የሚሻ ሠራዊት
ብርሃን ከበደ (በመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኮሌጅ መምህር የነበረ)
በጥቅምት 1998 ዓ.ም በተደረገው የአዋሽ አርባ ስብሰባ ኢሕአዴግ በግልጽ ለሰራዊቱ ያለውን ንቀት የገለጸበት ነበር፡፡ እዚህ ላይ ቢሰፍሩ ጸሐፊውንም ጭምር የሚያስገምቱ ንግግሮች ከአቶ መለስ ይደመጡ ነበር፡፡ ጉዳዩ በዚህ ብቻ አላበቃም ነበር፡፡ በቅንጅት ደጋፊነት የተጠረጠሩ ያለ ፍርድ እስር ቤት ተላኩ፡፡ “በፓርቲዎች ክርክር ወቅት የቅንጅትን አድምጠህ የኢሕአዴግ ሲመጣ ከቴሌቪዠን ክፍል ወጥተህ ሄደሃል” ተብሎ ግምገማ የተደረገበት ሁሉ ሳይቀር ለእስር ተዳረገ፡፡ 20 ሺህ ሠራዊት በአንድ ቅጽበት ተራገፈ፡፡ ታጠቅ መሙላቱን አስታውሳለሁ፡፡ በዚህ ወቅት አፋር በረሃ ላይ ለአራት ወር ያህል በማሰር አሰቃይተው ለቀዋቸዋል፡፡
ኢሕአዴግ ለሰራዊቱ ያለው ንቀት በብዙ መልክ የሚገለጽ ነው፡፡ መብቱን ከመግፈፍ አንስቶ ብሔር ከብሔር እያጋጨ ለሥልጣን ማራዘሚያ እየተጠቀመበት ነው፡፡ ጓደኛ ለጓደኛ እንዳይተማመኑ በማድረግ እንዲሁም የበታች አለቆች የላይኞቹን እንዲያዙ በማድረግ ሠራዊቱን የብሔራዊ ስሜት አሳጥቶታል፡፡
ይህ ከላይ በወፍ በረር የተመለከትኩት እውነታ ዛሬ ኢትዮጵያ አለኝ የምትለው ሠራዊት ማንነት ነው፡፡ ለነፃነት የቆመ የሚባለው ሠራዊት እንደሌላው የማህበረሰብ ክፍል ሁሉ ነጻነትን የሚሻ ነው፡፡ ድምጽ ማሰሚያ ቀዳዳ አጥቶ እንጂ የነጻነት ጥሪው ከሌሎች ቢልቅ እንጂ የሚያንስ አይደለም፡፡ . . .

ግልጽ የኾነ ሎጂክ አለ፤ የኢትዮጵያ ሠራዊቱ ተብሎ ለሚጠራ አባል ሁሉ የሚተረክ፡፡ “ኢሕአዴግ የሕገ መንግሥቱ ጠባቂ ነው፡፡ ኢሕአዴግን መጠበቅ ደግሞ ሕገ መንግስቱን መጠበቅ ነው፡፡ ስለዚህም ሠራዊቱ ግንባሩን መጠበቅ ትልቁ ኃላፊነቱ ነው፡፡” ይህ ከአገር ጥቅም በላይ የገዢ ግንባሩን የሥልጣን ጥማት ለማርካት የሚነገር የሠራዊቱ መመርያ ከሁሉ የአገሪቱ ሕጎች በላቀ ትልቅ ሥፍራ የሚሰጠው ነው፡፡ እያንዳንዱ አባልም የስሙን ያህል ያውቀዋል፡፡ ዘወትር እንዲያነበንበውም ይጠበቃል፡፡ እኔም በ1994 ዓ.ም የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኮሌጅን በተማሪነት ከመቀላቀሌ መመሪያውን መተዳደርያዬ እንዳደርግ ከወታደራዊ ሳይንስ ስልጠናዎች ይልቅ አብዮታዊ ዴሞክራሲን በሚሰብኩ ስብሰባዎች ተነገረኝ፡፡ ያንጊዜ ከልቤ ላገለግለው በፍቃደኝነት የተቀላቀልኩት ሠራዊት ዘለቂ በኾኑ ብሔራዊ ጥቅሞች አንጻር ተንሸራንቶ መገኘቱ ውሳኔዬ የተሳሳተ መኾኑን ለመገንዘብ ያስቻለኝ ነበር፡፡
ዛሬ በስደት በምኖርበት ባህር ማዶ ያሉ ወገኖችም ኾኑ የ20 ዓመታቱ የአቶ መለስ አገዛዝ ያንገፈገፋቸው በአገር ውስጥ የሚገኙ ዜጎች ስለመንግስት ለውጥ በስፋት የሚነጋገሩበት ነው፡፡ የነጻነት እጦቱ፣ መራብና መጠማቱ እንዲሁም ያለ አግባብ በእስር መንገላታቱ በቂ ምክንያቶች ቢኾኑም፤ በሰሜን አፍሪካ እና በመካከለኛው ምሥራቅ አገራት የተገኙት ሕዝባዊ ድሎች ለዛሬው የዜጎች መነቃቃት ግብዓት ናቸው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞም በማንኛውም ጊዜ ሊከሰት ለሚችለው የኢትዮጰያ የሕዝብ የአደባባይ ተቃውሞ የሠራዊቱ ሚና ምን ይኾናል የሚለው ዋነኛ መነጋገርያ መኾኑ አልቀረም፡፡
በግብጽ እንዲሁም ሕዝባዊ ተቃውሞ ውጤት ባስመዘገበባቸው ሌሎች አገራት የታዩ የሠራዊቱ የገለልተኝነት ሚና ዛሬ የኢትዮጰያ ሠራዊት ከሚገኝበት ወታደራዊ ስነ ሥርዓት እና መዋቅር አንጻር መመልከቱ ተገቢ እንደሚኾን በማሰብ በሠራዊቱ ውስጥ በተማሪነት እንዲሁም በመምህርነት በቆየሁባቸው ሰባት ዓመታት ውስጥ ያገኘኋቸውን እውነታዎች መሰረት በማድረግ ጥቂት ነጥቦችን ለማካፈል ወደድኩ፡፡ አንድም የብሔራዊ ጥቅምን ዋጋ ከፍ ከማድረግ አኳያ በሌላም በኩልም ደግሞ ተገቢውን ወታደራዊ ሥነ ምግባር ከመጠበቅ አንጻር ዝርዝር አገራዊ ጉዳዮችን ከመተንተን ይልቅ አንኳር በሚመስሉኝ የሠራዊቱ ጉዳዮች ላይ ብቻ ለማተኮር እወዳለሁ፡፡
በፕሮፓጋንዳ ማደንዘዝ
ወታደራዊ ሳይንስ በዲሲፕሊን የታነጸ ጠንካራ ሠራዊት ለመፍጠር ዋነኛው ግብዓት ነው፡፡ እያንዳንዱ የሠራዊቱ አባል ዘመኑ ከደረሰበት ወታደራዊ ብልሃት የቻለውን ያህል እንዲቀስም ሳይንሱን ያለማቋረጥ መመርመር ግዴታውም ጭምር ነው፡፡ ማወቅ ወታደሩን የበለጠ ለሕዝቡ ታማኝ እንዲኾንና የሚጠበቅበትን አገራዊ ግዴታ እንዲወጣ ይረዳዋል፡፡ እውነታው ይሄ ቢኾንም እኔ ባሳለፍኩብት የኢሕአዴግ ሠራሽ ሠራዊት ውስጥ “ማወቅ” የሚለው ቃል ብያኔው ከዚህ የራቀ ነው፡፡
ማወቅ፣ መሠረታዊ የሰው ልጆችን መብት ከመካድ እና ያለማቋረጥ በኢሕአዴግ ካድሬዎች የሚነገሩትን ፕሮፓጋንዳዎች ከማነብነብ ጋር እጅጉን የተቆራኘ ነው፡፡ ሠራዊቱ ከመብቱ ይልቅ ግዴታዎቹን እንዲያብሰለስልና እንዲፈጽም ይጠበቅበታል፡፡ ግዴታ እንጂ መብት የሠራዊቱ አካል አይደለም፡፡ ዘወትር በሚነገረውም ፕሮፓጋንዳ ተገዢ በማድረግ የህሊና እስረኛ ይኾናል፡፡ ለመጥቀስ ያህል ለተራ ወታደር ቴክኒካል ስልጠናዎች ለሶስት ወር ብቻ ያህል ሲሰጡ አብዮታዊ ዴሞክራሲ እና መሰል ኢሕአዴግ ፕሮፓጋንዳ ሥራዎች እሰከ ስድስት ወር ያህል ይዘልቃሉ፡፡ በየስብሰባውም በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ማጥመቅ እና መደንዘዝ ይቀጥላል፡፡ ብዙ ጊዜም እንደሚስተዋለው በስብሰባዎች የብዙሃኑ የሚመስሉ ጥያቄዎችን መጠየቅ ትልቅ ወንጀል ተደርጎ ነው የሚወሰደው፡፡ አገራዊ አጀንዳዎችም የሠራዊቱ ያልኾኑ ያህል ከከፍተኛ ባለስልጣናት እስካልፈለቁ ድረስ አባላት በስብሰባዎች መካከል እንዲያነሱ አይፈቀድም፡፡
ቀደም ሲል እንደጠቀስኩትም የፕሮፓጋንዳዎቹ ዓላማ ሰራዊቱ መብቱን እንዳይጠይቅ፣ ኢሕአዴግን መጠበቅ ሕገ መንግስቱን መጠበቅ ነው ብሎ እንዲያምን እና የፕሮፓጋንዳቸው ተገዢ እንዲኾን ማድረግ ነው፡፡ ይህም አብዛኛው ሠራዊት መንግስት ከሚሰጠው ግዳጅ ውጪ በወሳኝ አገራዊ ጉዳዮች ውስጥ ሚና እንዳይኖረው እንዲሁም ስለብሔራዊ ጥቅም እንዳያስብ ኾን ተብሎ የተደረገ ነው፡፡
ሠራዊቱ ራሱን ችሎ ህልውና እንዲኖረው ማድረግ በኢሕአዴግ ሰዎች ልብ ውስጥ የሚታሰብ አይደለም፡፡ ብዙ ጊዜ በተለያዩ ስብሰባዎች እንደሚደሰኩሩልን “ኢሕአዴግ ከሌለ ሠራዊቱ ህልውናውን ያጣል፡፡” ስልጠናዎች ሁሉ ከኢሕአዴግ ውጪ የትኛውም አካል የሠራዊቱ ወዳጅ እንዳልኾነ እና የመንግስት ለውጥ ቢመጣ ኣባላቱ ተጎጂ እንደሚኾኑ የሚሰብኩ ናቸው፡፡
እዚህ ላይ በ1997ቱ ምርጫ ወቅት የኾነውን ማስታወስ ተገቢ ይመስለኛል፡፡ ቅንጅት አዲስ አበባ ላይ ድል ማስመዝገቡ ሲነገር በሠራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች ዘንድ መደናገጥ ተፈጥሮ ነበር፡፡ በሠራዊቱ ውስጥ ተደጋጋሚ እና አሰልቺ ስብሰባዎች የበዙበት፤ አይን ያወጣ ወንጀልም የተስተዋለበት ጊዜ ነበር፡፡ በወቅቱም ከተደረጉት ስብሰባዎች ውስጥ እኔ በነበርኩበት መከላከያ ኢንጂነሪንግ ኮሌጅ ውስጥ በጥቅምት 1998 ዓ.ም እንዲህ የሚል ውሳኔ ላይ ተደርሶ ነበር፡፡ “ሕዝቡ ተሳስቶ ሊመርጥ ይችላል፡፡ እነዚህ ሰዎች (ቅንጅቶች) ሕገ መንግስቱን ሊንዱ የመጡ ሰዎች ናቸው፡፡ ስለዚህ መንግስት አዲስ አበባን ለቅንጅት ሰዎች ቢያስረክብም ሠራዊቱ ግን ማስረከብ የለበትም፡፡” ይህ ኣባባል መንግስትና ሠራዊቱ የተለያየ አቋም ያላቸው ለማስመሰል እንጂ የዚህ ሐሳብ ጠንሳሽ አራት ኪሎ እንደሚገኝ ማንም የሚስተው ጉዳይ አልነበረም፡፡
ባይተዋር ወታደር
ይህ በኢንጂነሪንግ ኮሌጅ ውስጥ የኾነ ታሪክ ነው፡፡ በሰኔ 1997 ዓ.ም አንዲት የሠራዊቱ አባል በላይቤሪያ የሰላም አስከባሪ ግብረ ኃይል ውስጥ መካተቷ ይነገራታል፡፡ ብዙዎች ከግቢው ለመራቅም ይኹን ዳጎስ ላለው ክፍያ ላይቤሪያ መጓዝን እንደ ልዩ ዕድል ያዩት ስለነበር ወታደሯም በአጋጣሚው ደስተኛ ነበረች፡፡ ከደስታዋ ጋር ግን ብዙ አልተጓዘችም፡፡ ለአመራሮቹ ቅርብ የኾነ የሠራዊቱ አባል በላይቤሪያው ጉዞ አልተካተተ ኖሮ በብስጭት ባለዕድለኛ ጉዞውን ሰርዛ ለእርሱ እንድትሰጠው ይጠይቃታል፡፡ እርሷም ቀድሞ ትሻው የነበረው ዕድል እንደኾነ በመግለጽ እንደማትችል ትገልጥለታለች፡፡ እርሱ አልተናደደም ይልቁንም “እኔ ቀድሜ አንቺን ላማክር ብዬ እንጂ ቢሮ ብሄድ ያንቺን ዕድል ለእኔ ይሰጡኛል” ብሎ የሚፈልገውን አደረገ፡፡ የእርሷ ጉዞ ያለፍቃዷ ተሰርዞ ለሌላ ሰው ተሰጠ፡፡
እንዲህ አይነት አድሎ ስራዎች እጅግ የተለመዱ ናቸው፡፡ በአንድ ወቅትም በጥረቱ ያገኘውን የውጭ ትምህርት ዕድል የሌላ ብሔር ስለኾነ ብቻ የተከለከለ የመከለካከያ ኮሌጅ መምህር ራሱን ማጥፋቱ ብዙዎቻችን የሠራዊቱ አባላት በቁጭት የምናስታውሰው ነው፡፡
ይህ የግቢው ለአንድ ብሔር የማድላት ነገር የተለመደ ነው፡፡ ሌሎች ራሳቸውን ባይተዋር እንጂ የሠራዊቱ አካል መኾን የሚያኮራቸው ነገር የለም፡፡ የሻምበልነት ማዕረግ ያለውን ነገር ግን ከትግራይ ክልል ውጭ የመጣን የሌላ ብሔር ተወላጅ ተራ ወታደር መመርያ ሊሰጠው ይችላል፡፡ በተለይ ከ1997 ምርጫ ወዲህ የሌሎች ብሔር ተወላጆች ሚና ጭራሹኑ እየጠፋ ነው፡፡ ከፍተኛ ስልጣን የያዙ ጥቂቶች አሁንም ቢኖሩም እምነት የሚጥልባቸው ባለመኖሩ በሠራዊቱ ውስጥ አሉ መባላቸው ለቁጥር ካልኾነ በቀር ፋይዳ የለውም፡፡
ላይ ላዩን ለተመለከተው የሠራዊቱ የብሔር ተዋጽኦ ምጥጥን የሚታይበት ይመስላል፡፡ ይሁንና የቁጥር መመጣጠን እና የስልጣን መጋነን ከፍተኛ ልዩነት አላቸው፡፡ የትግራይ ተወላጆች ቁጥር አነስተኛ ቢኾንም የያዙት የስልጣን ድርሻ ግን እጅግ ከፍተኛውን የያዘ ነው፡፡ ለይምሰል ከሌሎች ብሔረሰቦች የተውጣጡ ስልጣን ቢይዙም ቀደም ሲል እንደተገለጸው ዋናው የስልጣን ሞተሩ ያለው በሕወሃት እጅ ነው፡፡ ሠራዊቱ ይህንን በሚገባ ያውቃል፡፡ ነገር ግን ጥያቄ እንዳያነሳ በሕግና በደንቦች ቀንብበው ይዘውታል፡፡ የጋራም ኾነ የግል ጥያቄ እንዲነሳ አይፈለግምና፡፡
በዚህም ወቅት ብዙዎች አማራጭ አድርገው የወሰዱት ከሠራዊቱ ወጥቶ መኮብለልን ነው፡፡ ብዙዎች በተለያየ ምክንያት ከአገር እየወጡ መቅረትን መርጠዋል፡፡ በተለይ የትምህርት ደረጃቸው ከፍ ያሉት (የትግራይ ተወላጆችን ጨምሮ) በሠራዊቱ ውስጥ ያላቻው ቁጥር ከጊዜ ጊዜ እየመነመነ ነው፡፡ ብዙዎቹም እንደወጡ መቅረትን መርጠዋል፡፡
የሥርዓቱ ፈጣሪዎች ለሠራዊቱ ያላቸው ንቀት
በ1997 ቅንጅት አዲስ አበባን ማሸነፉ ሲገለጽ የመሬት መቀራመቱ ለሠራዊቱም ደርሶት ነበር፡፡ በወቅቱ የነበረው ሩጫ ጥቂት በማይባሉ የሠራዊቱ አባላት የተወደደ ባይኾንም ከመንግስት የመጣ መመርያ ነው በማለት ብዙሃኑ አባላት በመሬት ቅርጫው ተሳትፏል፡፡ እውነታውን በወቅቱ ለታዘበ የእናት አገር መሬት ሳይኾን የባእድ ይመስል ነበር፡፡ ነገሩ እንዲህ ታለፈ፡፡ ቅንጅት አዲስ አበባን ሳይረከብ ቀረ፤ መንግስትም እፎይ አለ፡፡
መንግስት መረጋጋቱን ሲያውቅ የመጀመረያው ርምጃ በሰበብ አስባቡ ለቅንጅት አድልቷል የተባለውን አባል መቅጣት ነበር፡፡ እኔም እንደማስታውሰው በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ አንድ ስብሰባ አዋሽ አርባ ላይ ተደርጎ ነበር፡፡ በወቅቱም መንግስት ራሱ በመመሪያ የፈቀደውንና ያስፈጸመውን የመሬት መቀራመት ጉዳይ አንስቶ “ስግብግብ” የሚል ቅጥያ ለሠራዊቱ በመስጠት ቂሙን መወጣት ጀመረ፡፡ በምርጫው ሂደትም “ሕገ መንግስቱን አልጠበኩም” እንዲል እና ሂሱንም “እንዲውጥ” ተደርጎ ነበር፡፡
በጥቅምት 1998 ዓ.ም በተደረገው የአዋሽ አርባ ስብሰባ ኢሕአዴግ በግልጽ ለሰራዊቱ ያለውን ንቀት የገለጸበት ነበር፡፡ እዚህ ላይ ቢሰፍሩ ጸሐፊውንም ጭምር የሚያስገምቱ ንግግሮች ከአቶ መለስ ይደመጡ ነበር፡፡ ጉዳዩ በዚህ ብቻ አላበቃም ነበር፡፡ በቅንጅት ደጋፊነት የተጠረጠሩ ያለ ፍርድ እስር ቤት ተላኩ፡፡ “በፓርቲዎች ክርክር ወቅት የቅንጅትን አድምጠህ የኢሕአዴግ ሲመጣ ከቴሌቪዠን ክፍል ወጥተህ ሄደሃል” ተብሎ ግምገማ የተደረገበት ሁሉ ሳይቀር ለእስር ተዳረገ፡፡ 20 ሺህ ሠራዊት በአንድ ቅጽበት ተራገፈ፡፡ ታጠቅ መሙላቱን አስታውሳለሁ፡፡ በዚህ ወቅት አፋር በረሃ ላይ ለአራት ወር ያህል በማሰር አሰቃይተው ለቀዋቸዋል፡፡
ኢሕአዴግ ለሰራዊቱ ያለው ንቀት በብዙ መልክ የሚገለጽ ነው፡፡ መብቱን ከመግፈፍ አንስቶ ብሔር ከብሔር እያጋጨ ለሥልጣን ማራዘሚያ እየተጠቀመበት ነው፡፡ ጓደኛ ለጓደኛ እንዳይተማመኑ በማድረግ እንዲሁም የበታች አለቆች የላይኞቹን እንዲያዙ በማድረግ ሠራዊቱን የብሔራዊ ስሜት አሳጥቶታል፡፡
ይህ ከላይ በወፍ በረር የተመለከትኩት እውነታ ዛሬ ኢትዮጵያ አለኝ የምትለው ሠራዊት ማንነት ነው፡፡ ለነፃነት የቆመ የሚባለው ሠራዊት እንደሌላው የማህበረሰብ ክፍል ሁሉ ነጻነትን የሚሻ ነው፡፡ ድምጽ ማሰሚያ ቀዳዳ አጥቶ እንጂ የነጻነት ጥሪው ከሌሎች ቢልቅ እንጂ የሚያንስ አይደለም፡፡ . . .
Your account of the story is pure myth
Informative!
teshome
who will expect anything different from you?
@Teshome…Do you really have to oppose every criticism about woyane? At least the writer was there. you seem to know everything like Google!
Bire, minew chekolk, gena rasihin sew mehonih sataregagit, malawes jemerk. arifeh serteh bitilewet yishalahal, ayitekimihim.
yes we too we feel there is a problem in defence, but I don’t think that it is in the way u explained that will help us. it is a very narrow idea from a narrow minded. you need time to say the reality. all you said is emotional sayings … I am sorry of you … I observed from wht u have written that u are too confused … “yet yidersal yetebale bahirzaf kebele koretew new neger”
I have not ever thought that you have such spoiled personality. No one benefits from wht you wrote except the enemies of Ethiopia & Ethiopians…
sim-min- yaregal, ewnetehen new, sem yeleleh!
what is wrong with the writer? why dont you criticize his idea instead of his personality? Besides, i doubt that you have enough exposure on ‘what it seems living in total freedom’. Still you want to scare him by saying ‘aytekemehim’ ‘arfeh serteh’ etc.
@Teshome,
I remember one proverb from my childhood. It is about loudness of a Drum. one day in community gathering, the drum ask why i am louder than anybody, and many tries to answer but failed, but somebody open the drum and found empty, then everybody got the answer that emptiness makes noise. Therefore, Teshie, I know you can remember many quotes,but please do not undermine the power of commonsense, nothing can replace it. At the beginning, i was thought that you are fake person whom created by the addis neger online, to make the debate hot, … but day by day, you make the intellects forum……..
The writer has raised an important issue,, something out there in reality. It is a credible story. We have heard the same stories from other people too. Such kind of corrupt, undisciplined, and divisionary practices within the Army is very dangerous. Everyone concerned about the country should consider it very seriously. Such kind of dangerous games have been rampant in the past few years – questioning the very exsistence of the country (Ethiopia), mocking the flag, inciting ethnic and religous conflicts, seceding the territory of the country to Sudan,,, and now turning the army into an ethnicaly divided and disaffected group. Rather than dismissing it as baseless, it is better to think about it seriously.
Oda and henny
It is ridiculously easy and bizarre puzzle to take the writer’s story at face value. For any person with an inquisitive mind, it is as such an easy job to know who is the guy with black suit.
This unverified report was taken for long time as a play ground for politics among the functionally illiterate die hard diaspora Ethiopians and it doesn’t come as surprise if this infantile scribble put forward at this point in time to serve its evil purpose.
The story was based on unfolded allegation to discredit the military segments of one particular ethnic origin. This is nothing but as usual ‘the rule rather than the exception’ and we know this cheap politics and monos tries are half way between man and ape.
You were witnessed several times to stand against the Ethiopian military forces in Ethio-Eritrea war and recently a war on Somalia. Who knows, we are seeing spark of light that you will be in lined with a potential foreign aggressors in a disputable Abay Dam. Yet you are doing these things in the name and clouds of democracy, the good thing is you were eventually made at loss of the trust of Ethiopian people.
But It is an inconvenient truth for you, the Ethiopian people and its patriots military forces will be hand in gloves than ever before to make Ethiopia a better place to live with.
In the mean time, don’t let your dream die because it is a good stimulus for us and we bring strength out of it
anyone who understand Woyane should know it is the enemy of Ethiopia, pure and simple.
Teshome is a cadre, only a cadre can scream all the time againest Ethiopians
Ask teshome which Woyane killil he came from. He would not tell the truth, he is ashemed of who he is because he is not Ethiopian.
@piassa, if you want the reality, here it is: I am from the college where birhane is and I know him very well, I did not say that the soldier don’t have any complain, yes it has, for example we complain that the salary is low, specially the professionals we feel that our salary is unfair, but this is for all of us (Ethiopians), but I don’t think it is done to hurt any particular tribe nor politics related. If it were done to benefit the tigrays as Birhane said, the educated Tigryans wouldn’t have leaved. it is not politics problem as he said.
he said that scholars is given to the tigryans, if so why he is given scholars, he is my batch mate, he got scholar but there were tigrayns who has graduated with him who has better result but they didn’t got. among around 10 people who has got scholars with him there was only one from Tigray and he knows how they were selected. any way, I could have said many things, but it is difficult to say it in written, more ever, I am not good at writing.
if his mission was to see Ethiopia changed, he could have said the reality and help us our rights reserved.
They let him learn till his masters (though it is Ethiopians many, it was b/c of their signature he had it), then he is going to dare to say them ‘dedeboch’ as his elders …
let me advice you again, Bire, this game won’t benefits you, just keep on your study and change your self then change your family …
The twisted people won’t help you, rather make you go wrong, don’t waste your time, use your valuable time for the good of Ethiopia, if you really want see Ethiopia changed, it is only by working hard we can change it, work hard then change your self then you can have the power to change Ethiopia, such spoiled politics won’t help Ethiopia changed, keep your self far apart from the evils, concentrate on your study.
I think this is the right time to change your self. Bire don’t forget that it is the people you dare to insult who are the reason for your change. you could have said the realities having respected them.