"; _gaq.push(['_trackPageview']);(function() { var ga = document.createElement('script'); ga.type = 'text/javascript'; ga.async = true; ga.src = ('https:' == document.location.protocol ? 'https://ssl' : 'http://www') + '.google-analytics.com/ga.js'; var s = document.getElementsByTagName('script')[0]; s.parentNode.insertBefore(ga, s); })();

የጎግል ጋዜጣ ባለቤት እና ሥራ አስኪያጅ በመንግሥት ጫና አገር ለቀው ተሰደዱ

ጋዜጣው ከመንግሥት ሰዎች ጋራ በመመሳጠር ከመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት የሚወጡ መረጃዎችን ያትም እንደነበር የሚናገሩት አቶ አዲስ “በተለይ በምርጫው ወቅት መንግሥት በጋዜጣው ላይ የነበረው ጣልቃ ገብነት ከቁጥጥር ውጪ ኾኖብን ነበር” ይላሉ።
“ምርጫው አንድ ሳምንት ሲቀረው በመንግሥት ትዕዛዝ የመንግሥትን ሐሳብ ሙሉ ለሙሉ የያዘ 50 ሺሕ የጎግል ጋዜጣ ቅጂ ታትሞ በገበያ ላይ ውሎ ነበር” ሲሉ ምሳሌ ጠቅሰው ያስረዳሉ።

This post is available in: ኸንግሊስህ

የሳምንታዊው የአማርኛ ጋዜጣ “ጎግል” ሥራ አስኪያጅ እና ከባለቤት የኾኑት አቶ አዲስ ተስፋ በመንግሥት በኩል ደረሰብኝ  ባሉት ጫና ምክንያት አገር ለቀው መሰደዳቸውን ለአዲስ ነገር ገለጹ።

ጋዜጣው ከመንግሥት ሰዎች ጋራ በመመሳጠር ከመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት የሚወጡ መረጃዎችን ያትም እንደነበር የሚናገሩት አቶ አዲስ “በተለይ በምርጫው ወቅት መንግሥት በጋዜጣው ላይ የነበረው ጣልቃ ገብነት ከቁጥጥር ውጪ ኾኖብን ነበር” ይላሉ። “ምርጫው አንድ ሳምንት ሲቀረው በመንግሥት ትዕዛዝ የመንግሥትን ሐሳብ ሙሉ ለሙሉ የያዘ 50 ሺሕ የጎግል ጋዜጣ ቅጂ ታትሞ በገበያ ላይ ውሎ ነበር” ሲሉ ምሳሌ ጠቅሰው ያስረዳሉ። ይህ በምርጫው ወቅት የነበረው የቅጂ ብዛት ግን ከጎግል የኅትመት ቁጥር ጋራ ታሪካዊ ትይይዝ የሌለው እና ድንገተኛ የመንግሥት ጫና ውጤት ነው ሲሉም ያስረዳሉ።

አቶ አዲስ በመንግሥት በኩል በጋዜጣው ላይ ይወጡ ነበር ለሚሏቸው ጹሑፎች ተጠያቂ የሚያደርጉት የጋዜጣውን ማኔጂንግ ኤዲተር አቶ ብርሃኑ በላቸውን እና ዋና አዘጋጁን አቶ ኤርምያስ ውብሸትን ነው። የጋዜጣው ዋና አዘጋጅ ግን የአቶ አዲስን ክስ አይቀበሉትም “ይኼ ሙሉ ለሙሉ ሀሰት ነው” ይላሉ አቶ ኤርሚያስ በምርጫው ወቅት ታተመ ስለተባለው 50 ሺሕ ቅጂ ሲገልጹ፤ “ጋዜጣው በሚኖረው ይዘት ሁሉ የእርሱ እጅ አለበት። እርሱ በሚለው እንጂ እኛ ባልነው የኾነ ነገር አልነበረም። በውጭ ተጽዕኖ ምክንያት እኔ እና ብርሃኑ የለወጥነው የጋዜጣው ይዘት አልነበረም።” ሲሉ ይገልጻሉ።

አቶ አዲስ በበኩላቸው ጋዜጣው አሁንም ድረስ ሥራውን “በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ኾኖ” እየሠራ እንደሚገኝ ይናገራሉ። በመንግሥት በኩል ይደረግ ነበር ያሉትን ተደጋጋሚ ጣልቃ ገብነትን ሲቃወሙ መቆየታቸውን የሚናገሩት በደኅንነት ሰዎች ደረሰብኝ ባሉት ጫና እና ድብደባ ምክንያት አገር ለቀው ለመሰደድ እንደበቁ ይገልጻሉ።

ከአገር ከመውጣታቸው ከሳምንት በፊት ሕጋዊ የጋዜጣው ማኅተም ከቢሮ ተሰርቆ መወሰዱን እና የባንክ ሒሳቡም እንዳይንቀሳቀስ መደረጉን የሚያስረዱት አቶ አዲስ ከ500 ሺሕ ብር በላይ አውጥቼበታለሁ የሚሉት ድርጅት “አደጋ ላይ ወድቋል” ይላሉ። በዚህም ምክንያት ቤተሰቦቸው ለችግር መጋለጣቸውንም ጨምረው ተናግረዋል።

አቶ ኤርሚያስ ግን ይህንንም መረጃ አይቀበሉትም። “ጋዜጠኝነት መሸሻ መኾን የለበትም” ሲሉ የቀድሞ ባልደረባቸው አድርሰውታል የሚሉትን ጥፋት ይዘረዝራሉ። “ገንዘብ ለማንቀሳቀስም ኾነ ሌላ ሥራ ለመሥራት ሙሉ ለሙሉ ሥልጣኑ የእሱ ነው። መተዳደሪያ ደንቡም የሚለው ይኼንኑ ነው። በመኾኑም ከእርሱ ዕይታ እና ቁጥጥር ውጪ የነበረ ነገር አልነበረም።”

“ጎግል” የ1997 ምርጫን ተከትሎ መንግሥት በወሰደው ርምጃ የግል ጋዜጦች ከተዘጉ ከሁለት ዓመታት በኋላ ወደ ገበያው ብቅ ካሉ የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ጋዜጦች አንዱ ነው።

One Response to “የጎግል ጋዜጣ ባለቤት እና ሥራ አስኪያጅ በመንግሥት ጫና አገር ለቀው ተሰደዱ”

  1. Zemenew Woubalem 1 September 2010 at 12:51 am

    the link for Dereje Haile’s news is mistakenly connected to Googlenewspaper. Please, fix it. Otherwise, it is a superb online media!
    Keep it up!
    -

Leave a Reply

You must be to post a comment.

የአዲስ አበባ መስተዳድር “ኪራይ ሰብሳቢ” የተባሉ ሦስት ሺህ ሠራተኞችን ሊያባርር ነው

This post is available in: ኸንግሊስህበአቶ ኩማ ደመቅሳ የሚመራው የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ሰሞኑን ባደረገው ግምገማ በ”ኪራይ ሰብሳቢ”ነት  የፈረጃቸውን ሦሰት ሺሕ ሠራተኞች ሊያባርር ነው።  ከሥራ እንዲባረሩ ውሳኔ የተላለፈባቸው አብዛኞቹ ሠራተኞች በ2001 ዓ.ም እና 2002 ዓ.ም የበጀት ዓመት መስተዳድሩ የቀጠራቸው የመጀመሪያ ዲግሪ የያዙ ወጣት ምሩቃን ናቸው። እነዚህ ወጣቶች በአላጌ የግብርና ማሠልጠኛ ተቋም የኢሕአዴግን “አቅጣጫ እና ስትራቴጂ” [...]

This post is available in: ኸንግሊስህ

በአቶ ኩማ ደመቅሳ የሚመራው የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ሰሞኑን ባደረገው ግምገማ በ”ኪራይ ሰብሳቢ”ነት  የፈረጃቸውን ሦሰት ሺሕ ሠራተኞች ሊያባርር ነው።  ከሥራ እንዲባረሩ ውሳኔ የተላለፈባቸው አብዛኞቹ ሠራተኞች በ2001 ዓ.ም እና 2002 ዓ.ም የበጀት ዓመት መስተዳድሩ የቀጠራቸው የመጀመሪያ ዲግሪ የያዙ ወጣት ምሩቃን ናቸው። እነዚህ ወጣቶች በአላጌ የግብርና ማሠልጠኛ ተቋም የኢሕአዴግን “አቅጣጫ እና ስትራቴጂ” ሥልጠና ለአንድ ወር ከወሰዱ በኋላ የአባልነት ፎርሙን አብዛኛዎቹ በግዴታ ጥቂቶቹም በውዴታ የሞሉ ናቸው።

ወጣቶቹን በምርጫ ማግስት ከሥራ ማሰናበት በቤተሰቦቻቸው እና በአዲስ አበባ ማኅበረሰብ ላይ ቅያሜ ሊፈጥር ይችላል በሚል ሥጋት በአንድ ጊዜ ሳይኾን ደረጃ በደረጃ ከሐላፊነት እንዲገለሉ እና ከነበራቸው ደረጃ በታች እንዲሠሩ በመስተዳድሩ በኩል መወሰኑን የአዲስ ነገር ምንጭ ያስረዳሉ።

ከሥራ ማባረሩ በእነዚህ ወጣቶች ብቻ እንደማይገታ እና ሌሎች ”ኪራይ ሰብሳቢ” ተብለው የሚፈረጁ ሠራተኞችም ይኸው ዕጣ እንደሚጠብቃቸው ውስጣዊ መረጃዎች ይጠቁማሉ። “በምርጫ 2002 ዓ.ም ኢሕአዴግን ወክለው የመወዳደር ዕድል ተሰጥቷቸው የተመረጡ ነባርም ኾኑ አዳዲስ አባላት፣ በሙስና እና በኪራይ ሰብሳቢነት ከተጠረጠሩ ጉዳያቸው እየተጣራ ክስ እንደሚመሠረትባቸው ተወስኗል” ይላሉ የመስተዳድሩ ምንጭ።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

የአምስት ዓመቱ ሕልም ወይስ እቅድ?

የአምስት ዓመቱ ዕቅድ ቀድሞ የተሰላ እና በጥናት ላይ የተመሠረተ አይደለም። የአዲስ ነገር ምንጮች እንደሚናገሩት የምርጫ 2002ን ውጤት ተከትሎ ለገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር የአስቸኳይ ጊዜ የቤት ሥራ ነበር። ባለሞያዎቹ ከሁለተኛው የዘላቂ እና ፈጣን ልማት ዕቅድ ላይ አንኳር ጉዳዮችን በመውሰድ አጣጥመው መሥራት ይችሉ እንደ ነበር ነገር ግን የፖለቲካው ግለት የተጫናቸው ካድሬ ባለሞያዎች በመኾናቸው ዕቅዱን የማይጨበጥ እንዳደረጉት ይናገራሉ። ጥድፈት የበዛበት በመኾኑም ለማስተካከል ዕድል አልነበረም። የምዕተ ዓመቱን የልማት ዕቅዶች መሠረት አድርጎ የተዘጋጀው ሁለተኛው የዘላቂ እና ፈጣን ልማት ዕቅድ የኢኮኖሚያዊ ሽግግር የሚለውን የሚጠቅስ ቢኾንም እስከ 15 በመቶ የሚገመት የዕድገት ምጣኔ አላስቀመጠም።

This post is available in: ኸንግሊስህ

በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ውስጥ ስምንት ሺሕ ኪሎ ሜትር አዳዲስ የባቡር መሥመሮች ግንባታ!? አዲስ አበባ ሌላ ወረት ላይ ያለች ትመስላለች። የምርጫ ወከባው ጋብ ካለላት በኋላ ደግሞ ሰሞኑን ሌላ የመወያያ ርእሰ ጉዳይ አግኝታለች። ከባለፈው ማክሰኞ ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት የቀበሌ አዳራሾች ሌላ ዲስኩር ለማኅበረሰቡ እንዲያዘንሙለት ዕቅድ ተይዞላቸዋል። በየደረጃው ያሉ የኢሕአዴግ ካድሬዎች ስለ አዲሱ የአምስት ዓመት የእድገት እና የሽግግር ዕቅድ ምንነት ገለጻ ያደርጋሉ። ማክሰኞ ዕለት በተጀመረውም ውይይት ላይ አነጋጋሪ የነበረው የዕቅድ ሙሉ ዝርዝር መተንተን ሳይቀጥል የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ አቶ ጁነዲን ሳዶ ሌላ ተጨማሪ ጉዳይ ለተወያዩ ተናገሩ፤ በአምስት ዓመታት ውስጥ ስምንት ሺሕ ኪሎ ሜትር የባቡር መሥመር እንደሚገነባ። እንዲያደምጥ እንጂ ሐሳብ እንዳይሰጥ የተከለከለ የሚመስለው ተወያይ በልቡ “እንዴት ኾኖ” የሚል ጥያቄን ማጉላላቱ አልቀረም። የዕቅዱ የተዓማኒነት አቅም ውስንነት ለብዙኀኑ ታዳሚ ግልጽ ነው። መንግሥት 781 ኪሎ ሜትር ከሚገመተው የአትዮ-ጅቡቲ መሥመር ውስጥ ባለፉት ሁለት ዓመታት 114 ኪ.ሜ በአዲስ መልክ ለማሠራት አቅዶ የነበረ ቢኾንም የዕቅዱን 40 በመቶ ያህል እንኳ እስካሁን ድረስ እንዳላሳካ መረጃዎች እውነቱን አበጥረው ያሳያሉ። ይህ ደረቅ እውነታ ከፊት ለፊት እያለ መንግሥት ግን አዲሱ የባቡር መሥመር ዝርጋታ “እመኑኝ ይሳካለኛል” እያለ በወኪሎቹ በኩል የስበከት ዲስኩሩን እያቀረበ ነው፡፡ በአዲሱ ዕቅድ እንደተቀመጠው ያቀደውን ሙሉ ለሙሉ ለማሳካት ቢያንስ በየዓመቱ 1600 ኪ.ሜ የባቡር መሥመር ዝርጋታ ተግባራዊ መኾን ይኖርበታል። ይህ እንደማይኾንለት ግን በቂ መውጫ ቀዳዳ ቀድሞውኑ አዘጋጅቷል፡፡ ዕቅዱን በተባለው ጊዜ የሚፈጽሙ ኩባንያዎች ቢኖሩ እንኳ ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ መንግሥት ያስፈልገዋል ተብሎ የተቀመጠው በቢሊዮን የሚገመት ዶላር የመገኘት አለመገኘቱ አደጋ የዕቅዱ ሌላኛው ክፈተት ነው። “በአየር ላይ የተንጠለጠለ” ኢኮኖሚስቶች “የማክሮ ኢኮኖሚ ሞዴል ያልጎበኘው” የሚሉት እና ለውይይት መነሻ ሐሳብ በሚል በ24 ገጾች የተዋቀረው ይኼው የቀጣዩ አምስት ዓመት (2003-2007) የዕድገት እና የሽግግር ዕቅድ “Growth and Transformation Plan” በምትኀት የተገኙ የሚመስሉ “ወፍ ዘራሽ” የኢኮኖሚ ትንበያዎችን የያዘ ነው። እንደ ዕቅዱ አገላለጽ ከኾነ ግን ከአምስት ዓመታት በኋላ በኢትዮጵያ ረኀብ ታሪክ ይኾናል። “የምግብ ዋስትናን በቤተሰብ፣ በአካባቢ እና በአገር ደረጃ ሙሉ በሙሉ ማረጋገጥ” በሚል ቃል የተቀመጠው ርእስ ረኀብን ታሪክ ለማድረግ ማስደገፊያ ነው። የግብርና ዘርፉም ዓመታትን የሚሻገር ትንበያ ተቀምጦለታል። በ2007 ዓ.ም በእጥፍ ለማሳደግ ታቅዷል፤ አጠቃላይ ኢኮኖሚውም በተመሳሳይ። ይህም እውን ይኾን ዘንድ ማብራሪያዎች ያልታከሉበት እና የተሻለ እና ተጨባጭ ትንበያን የሚያሳዩ የኢኮኖሚክስ ሞዴሎች ያልተቀመጡለት ዕቅድ ኢኮኖሚውን በአመካይ በየዓመቱ በ15 በመቶ ለማስጋለብ እንደተፈለገ ይገልጻል። የኢኮኖሚ ሞዴሎች በትክክለኛ መረጃ እና ኀልዮት ላይ ተመሥርተው የተዋቀሩ እስከኾነ ድረስ ለትንበያው የቀረበ የዕድገት ዕቅድ በማሳየት ተጨባጭ የልማት ግስጋሴን ያግዛሉ። ይኹንና አዲሱ ዕቅድ በምን ዐይነት ሞዴሎች ተመሥርቶ እንደተሰላ የማይገልጥ እንዲሁ “በአየር ላይ የተንጠለጠለ” ዐይነት ነው::  ከዚህም ባሻገር የትንበያዎች ከነባራዊው ኹነት ማፈንገጥ “የአገሪቷን የሰው ኃይል፣ የሀብት መጠን እና የማደግ አቅም ግንዛቤ ውስጥ ያልከተተ ትንበያ” ሲሉ  የኢኮኖሚ ባለሞያዎች ይተቹታል፡፡ “ወገብ የሚቆርጥ” Vs “ወገብ የለም”’ ከሳምንት በፊት በጉዳዩ ላይ ለጋዜጠኞች ጥያቄዎች መልስ የሰጡት አቶ መለስ ዕቅዱን “ወገብ የሚቆርጥ” እንደኾነ ቢገልጹም ለእርሳቸው የማይሳካ ዓይነት አይደለም:: ወገብ “እስኪበጠስ” ይታገላሉ፡፡ ይህ የ“ወገብ” ጉዳይ ግን ነገር ማጣፈጫ ኾኖ የሚያልፍ ወግ አይደለም፡፡ ይልቁንም “ቀድሞውንስ ምን ወገብ አለና” ብለው ለሚሞግቱ የኢኮኖሚ ባለሞያዎች በር ከፍቷል፡፡ የመጀመሪያው ሙግት የሚመጣው መንግሥት ራሱ ከወር በፊት ይፋ ካደረገው “Ethiopia: 2010 MDGs Report” ከሚለው ሪፖርቱ ጋራ ያለውን ተቃርኖ በማሳየት ነው፡፡ ይኼው በተባበሩት መንግሥታት ተወካዮች እና በገንዘብ እና የኢኮኖሚ ልማት ትብብር ሚኒስቴር የጋራ ጥምረት ይፋ የኾነው ሪፖርት እንደሚያሳየው የምዕተ ዓመቱን ግብ ለማሳካት እንኳን በርካታ ተግዳሮቶችን ኢትዮጵያ ማለፍ ይጠበቅባታል፡፡ በብዙኀኑ ድኻ ማኅበረሰብ እና በአናሳው ሀብታም ከተሜ ያለ የገቢ ኢ-እኩልነት (Income Inequality)፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ቁጥሩ እያደገ የመጣ ለረኀብ ተጋላጭ የኾነ ማኅበረሰብ መኖር እና ሌሎች ውስጣዊ እና ዓለም አቀፋዊ የዕድገት ማነቆዎች ተጠቃሽ ተግዳሮቶች ናቸው። እነዚህ ወሳኝ የሚባሉ ጉዳዮች በኢኮኖሚው አውታር ላይ የሚኖራቸው ተጽዕኖ ከፍተኛ ነው። ለምሳሌ የገቢ ኢ-እኩልነት እና የኢኮኖሚ ዕድገት ቀጥተኛ ዝምድ እና ያላቸው ሲኾን የገቢ ኢ-እኩልነት እየሰፋ በሚሄድባቸው አገሮች የሚኖር የኢኮኖሚ ዕድገት ዝቅተኛ ነው።  ዶ/ር እንዳስቀመጡት ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት ፍትሓዊ የገቢ ድርሻ መኖር ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ወሳኝ ጉዳይ ነው። የገቢ ኢ-እኩልነት ምጣኔ በአንድ በመቶ ሲጨምር የድህነት መጠን በአንጻሩ በ1.8 በመቶ ይጨምራል። ከራሱ ከመንግሥት የተገኙ መረጃዎች እንደሚያሳዩት በተለይ በከተሞች ያለው የገቢ አለመመጣጠን ትልቅ ችግር እየኾነ መጥቷል። ይህም ብዙኀኑን ደኻ ከሸመታ ጉዳይ ስለሚያርቀው የተፈለገውን ያህል የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት ፈተና ይኾናል። ሌላው የመንግሥት ዕቅድ መሳካት ላይ ጥያቄ የሚያስነሳው ጉዳይ የግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚው የአርሶ አደሩን ኑሮ እንኳን የሚደግፍ አለመኾን እና ከዚህም አልፎ አራሹን ለረኀብ የሚያጋልጥ መኾኑ ነው። እንደ መንግሥት ዕቅድ ከኾነ የግብርናው በ2007 ዓ.ም በእጥፍ ያድጋል። ይህም ኢኮኖሚው ወደ ተሻለ መዋቅር የሚያደርገውን ጉዞ ያቀላጥፋል። በጉዳዩ ላይ የተደረጉ ጥናታዊ ጽሑፎች እንደሚያሳዩት ከኾነ ግን በዝናም ሙሉ ለሙሉ ጥገኛ ነው የሚባለው ግብርና በመሬት ጥበት፣ በግብርና ቴክኖሎጂ እጥረት እና በመንግሥት ፖሊስ ምክንያት አመርቂ አይደለም። ከትላንት በስቲያ ለቪ.ኦ.ኤ ሐሳባቸውን ያካፋሉት ፕሮፌሰር ጌታቸው በጋሻው እና ዶክተር አክሎግ ቢራራ አሁን መንግሥት የሚናገርለት የግብርና ዕድገት የማይታመን የመዋቅር ለውጥም ያልታየበት መኾን ዕቅዱን “መለኮታዊ” ያስመስለዋል ሲሉ ይተቻሉ። በግብርና ቴክኖሎጂ እጦት ምክንያት ምርታማነት (Productivity) ደካማ መኾን በኢትዮጵያ የግብርና ምርትን ለማሳደግ የሚኖረው ብቸኛ አማራጭ የመሬት ይዞታን ማስፋት ነው። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በተለይ ለጥራጥሬ ሰብሎች የመሬትን ይዞታ ማስፋት በቸኛው የምርት ማሳደጊያ መንገድ ተደርጎ ይወሰዳል። ለምሳሌ መንግሥትን ፖሊሲ ደግፈው የሚወጡ ጥናታዊ ጽሑፎች እንኳ እንደሚገልጹት በ1990ዎቹ የጥራጥሬ ሰብሎች የሚውል የመሬት ይዞታ በአማካይ በ5.8 በመቶ ይጨምር ነበረ። ይኹንና እ.ኤ.አ ከ 2001 እስከ 2008/9 ባሉት ዓመታት በአማካይ ወደ 3.1 በመቶ ዝቅ ብሏል። በእነዚህ ዓመታት የምርት መጠንም ዝቅ ብሎ ተገኝቷል። የመሬት ይዞታን ብቻ በማሳደግም የሚመጣ ምርታማነት ህልም ነው። ከዚህም ባሻገር የተስተካከለ የዝናም ሥርጭት ይኖራል ተብሎ ቢገመት እንኳ በዚህ ወቅት የሚመረተውን እጥፍ የሚኾን ምርት ለማግኘት አሁን ካለው የግብርና መሬት ይዞታ ያልተናነሰ ስፍራ ያስፈልጋል፡፡ ይህም መንግሥት የግብርና ምርታማነትን በእጥፍ ለማሳደግ የያዘውን ዕቅድ ጎዶሎ የሚያደርግ ነው። ወደ ኢንዱስትሪውም የሚደረግ ጉዞ በዕቅዱ ላይ እንደተቀመጠው ከግብርናው ጋራ በእጅጉ ከግብርና ምርታማነት ጋራ የተቆራኘ በመኾኑ የኢኮኖሚያዊ መዋቅር ሽግግር አይኖርም። ሲሮጡ የታጠቁት . . . የትኛውም መንግሥት ይኾንልኛል የሚለውን ኢኮኖሚያዊ ዕቅድ ትንበያ ማስቀመጡ የሚጠበቅ ነው። ነገር ግን የኢኮኖሚ ትንበያ (Economic Forecasting) ጠቀሜታ አንድ አገር በደረሰበት የቴክኖሎጂ ደረጃ፣ የኢኮኖሚ መዋቅር እና የመረጃ ፍሰት መጠን የሚወሰን በመኾኑ በዘፈቀደ የሚከወን አይኾንም። ትክክለኛ መረጃ በማይገኝባቸው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሚኖሩ ትንበያዎች በአብዛኛው የተጋነነ እና ከእውነታው በእጅጉ የሚርቁ ስለሚኾኑ በጥርጣሬ እንዲታዩ ይኾናሉ። የአምስት ዓመቱ ዕቅድ ቀድሞ የተሰላ እና በጥናት ላይ የተመሠረተ አይደለም። የአዲስ ነገር ምንጮች እንደሚናገሩት የምርጫ 2002ን ውጤት ተከትሎ ለገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር የአስቸኳይ ጊዜ የቤት ሥራ ነበር። ባለሞያዎቹ ከሁለተኛው የዘላቂ እና ፈጣን ልማት ዕቅድ ላይ አንኳር ጉዳዮችን በመውሰድ አጣጥመው መሥራት ይችሉ እንደ ነበር ነገር ግን የፖለቲካው ግለት የተጫናቸው ካድሬ ባለሞያዎች በመኾናቸው ዕቅዱን የማይጨበጥ እንዳደረጉት ይናገራሉ። ጥድፈት የበዛበት በመኾኑም ለማስተካከል ዕድል አልነበረም። የምዕተ ዓመቱን የልማት ዕቅዶች መሠረት አድርጎ የተዘጋጀው ሁለተኛው የዘላቂ እና ፈጣን ልማት ዕቅድ የኢኮኖሚያዊ ሽግግር የሚለውን የሚጠቅስ ቢኾንም እስከ 15 በመቶ የሚገመት የዕድገት ምጣኔ አላስቀመጠም። ዕቅዱ በተገቢው የኢኮኖሚ ሞዴል የታገዙ ትንበያዎችን ባይዝም መንግሥት ከሕዝብ ጋራ ውይይት እያደረገበት ይገኛል። በንባብም በደመነፍስም የዕቅዱ መጋነን የገባቸው የልባቸውን በአደባባይ ባይተነፈሱም ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ የቀልድ ምንጭ ማድረጋቸው አልቀረም። “መንግሥት በአምስት ዓመታት ውስጥ ረኀብን አጠፋለሁ አለ እኮ” ይረላል አንዱ። ሌላኛው “ድህነት የተጻፈው በእርሳስ ነበር እንዴ!!” ሲል ይመልሳል። ቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ግን እንደ ቀልዱ ፈገግታን ላይጭሩ ይችላሉ።

2 Responses to “የአምስት ዓመቱ ሕልም ወይስ እቅድ?”

  1. Zemenew Woubalem 1 September 2010 at 12:51 am

    the link for Dereje Haile’s news is mistakenly connected to Googlenewspaper. Please, fix it. Otherwise, it is a superb online media!
    Keep it up!
    -

Leave a Reply

You must be to post a comment.

የአቶ ሰየ አብርሃ “ነጻነት እና ዳኝነት በኢትዮጵያ” በአዲስ አበባ በገበያ ላይ ዋለ

This post is available in: ኸንግሊስህ የቀድሞ የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስትር እና የአሁኑ የመድረክ ፓርቲ አመራር አባል በኾኑት በአቶ ስየ አብርሃ የተጻፈው “ነጻነት እና ዳኝነት በኢትየጵያ” በሚል ርእስ የቀረበው ባለ 440 ገጽ መጽሐፍ ነሐሴ 20 ቀን 2002 ዓ.ም በገበያ ላይ ዋለ። የአቶ ስየ መጽሐፍ በኢትዮጵያ ያለውን የዳኝነት ሥርዐት ከራሳቸው የእስር ልምድ ጋራ በማያያዝ የሚተርኩበት እና ስለ [...]

This post is available in: ኸንግሊስህ

የቀድሞ የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስትር እና የአሁኑ የመድረክ ፓርቲ አመራር አባል በኾኑት በአቶ ስየ አብርሃ የተጻፈው “ነጻነት እና ዳኝነት በኢትየጵያ” በሚል ርእስ የቀረበው ባለ 440 ገጽ መጽሐፍ ነሐሴ 20 ቀን 2002 ዓ.ም በገበያ ላይ ዋለ።

የአቶ ስየ መጽሐፍ በኢትዮጵያ ያለውን የዳኝነት ሥርዐት ከራሳቸው የእስር ልምድ ጋራ በማያያዝ የሚተርኩበት እና ስለ ነጻነትም የሚያወሱበት ነው። በተለያዩ የአዲስ አበባ አከፋፋዮች ዘንድ ትላንት ለገበያ የቀረበው ይኸው መጽሐፋቸው የመጀመርያ ኅትመቱ 10 ሺሕ ኮፒ እንደኾነ ታውቋል። በሶፍት ኔክ ማተሚያ ቤት የታተመው የአቶ ስየ መጽሐፍ ዋጋው 70፡00 ብር ነው።

አቶ ስዬ አብርሃ የመጽሐፉን መታሰቢያነት ለአባታቸው ለግራዝማች አብርሃ ሐጎስ፤ ወንድማቸው መምህር ገብረስላሴ አብርሃን ጨምሮ ፍትህ ተነፍገው በግፍ ለተገደሉት ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያውያት አድርገዋል። መጽሐፉ “ልዩነቱ”፣ “ከማእከላዊ እስከ ፍርድ ቤት”፣ “ሙግት፣ ቃሊቲ እና ምርጫ 97” እና “ፍርድ እና ነጻነት” በተሰኙ አራት ክፍሎች እና ዐሥራ አንድ ምዕራፎች የተጠናቀረ ሲኾን አቶ መለስ ዜናዊ፣ አፈ ጉባኤ ዳዊት ዮሐንስ እና ሌሎችም ለእርሳቸው የጻፏቸውን ደብዳቤዎች እንዲሁም የእነ አርከበን የምስክርነት ቃል በአባሪነት አካቷል።

አቶ ስዬ በመጽሐፉ መግቢያ ላይ “በመጋቢት ወር 1993 ዓ.ም የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ለሁለት መሰንጠቁን ተከትሎ ጠ/ሚኒስትርና የህወሐት ሊቀመንበር በነበረው በአቶ መለስ ዜናዊ የተመራው ቡድን እኔ የነበርኩበትን ቡድን በጉልበት ከፓርቲ እና ከመንግሥት ገፍትሮ ማስወጣቱን ተከትሎ እኔን ከሰባት የቤተሰቤ አባላት ጋር አስሮኛል . . . የተዘጋጀው ክስና የችሎት ድራማ እውነትን ለመሸፈን የተዘየደ ስልት መኾኑን ብናውቅም የነበረን አማራጭ በሂደቱ አልፈን እውነቱን ማውጣት እና ለትውልድ ማስተማሪያነት እንዲኾን በጽሑፍ ማስቀመጥ ነበር። የዚህ መጽሐፍ አላማም ይኸው ነው” ሲሉ አስፍረዋል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

ኮሜዲያን ደረጄ ኀይሌ “የሳቅ እልፍኝ” የተሰኘ አዲስ የኮሜዲ ቪሲዲ ሊያወጣ ነው

This post is available in: ኸንግሊስህ ከኻያ ዓመታት በላይ በኮሜዲ ሥራዎቹ የሚታወቀው ኮሜዲያን ደረጄ ኀይሌ መጪውን አዲስ ዓመት አስመልክቶ “የሳቅ እልፍኝ” የተሰኘ አዲስ የኮሜዲ ቪሲዲውን ለገበያ እንደሚያቀርብ ገለጸ። ከ 15 ዓመታት በላይ የኮሜዲ ሥራዎችን ለሕዝብ ሲያቀርቡ ከነበሩት ሟች የሞያ አጋሩ ሀብቴ ምትኩ ሕልፈት በኋላ ኮሜዲያን ደረጄ ኀይሌ እንደ “ግቢው”  “እየሳቁ መኖር” እና ሌሎችም የኮሜዲ ፊልሞች [...]

This post is available in: ኸንግሊስህ

ከኻያ ዓመታት በላይ በኮሜዲ ሥራዎቹ የሚታወቀው ኮሜዲያን ደረጄ ኀይሌ መጪውን አዲስ ዓመት አስመልክቶ “የሳቅ እልፍኝ” የተሰኘ አዲስ የኮሜዲ ቪሲዲውን ለገበያ እንደሚያቀርብ ገለጸ። ከ 15 ዓመታት በላይ የኮሜዲ ሥራዎችን ለሕዝብ ሲያቀርቡ ከነበሩት ሟች የሞያ አጋሩ ሀብቴ ምትኩ ሕልፈት በኋላ ኮሜዲያን ደረጄ ኀይሌ እንደ “ግቢው”  “እየሳቁ መኖር” እና ሌሎችም የኮሜዲ ፊልሞች ላይ በትወና የተሳተፈ ቢኾንም የራሱን ሥራዎች በቪሲዲ ሲያቀርብ ይህ የመጀመሪው ነው። በተለያዩ ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩረው የኮሜዲያኑ አዲስ ቪሲዲ ከአዲስ ዓመት በዐል በፊት ለገበያ እንደሚቀርብ ለማወቅ ተችሏል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

“ጥበብን እንቀመስ” የተሰኘ ወርሃዊ የሥነ ጥበብ ፕሮግራም በፑሽኪን አዳራሽ መቅረብ ጀመረ

This post is available in: ኸንግሊስህ ከነሐሴ 19 ቀን 2002 ዓ.ም ማምሻውን ጀምሮ የኢትዮጵያ ሴት ደራስያን ማኅበር “ጥበብን እንቃመስ” የተሰኘ ፕሮግራሙን በርካታ የሥነ ጥበብ ሰዎች እና የጥበብ አፍቃሪያን በተገኙበት በፑሽኪን አዳራሽ ማቅረብ ጀምሯል። በፕሮግራሙ ላይ የተለያዩ ሥነ ጽሑፋዊ ሥራዎች የቀረቡ ሲኾን “ፈተና” በተሰኘው ግለ ታሪክ መጽሐፏ የምትታወቀው እና ለበርካታ ዓመታት በደቡብ አፍሪካ በስደት የቆየችው አስቴር [...]

This post is available in: ኸንግሊስህ

ከነሐሴ 19 ቀን 2002 ዓ.ም ማምሻውን ጀምሮ የኢትዮጵያ ሴት ደራስያን ማኅበር “ጥበብን እንቃመስ” የተሰኘ ፕሮግራሙን በርካታ የሥነ ጥበብ ሰዎች እና የጥበብ አፍቃሪያን በተገኙበት በፑሽኪን አዳራሽ ማቅረብ ጀምሯል።

በፕሮግራሙ ላይ የተለያዩ ሥነ ጽሑፋዊ ሥራዎች የቀረቡ ሲኾን “ፈተና” በተሰኘው ግለ ታሪክ መጽሐፏ የምትታወቀው እና ለበርካታ ዓመታት በደቡብ አፍሪካ በስደት የቆየችው አስቴር ሰይፈ በተጋባዥ እንግድነት ተገኝታለች። የኢትዮጵያ ሴት ደራስያን ማኅበር ከዚህ ቀደም “ግጥም በማለዳ” የሚል ፕሮግራም በአገር ፍቅር ቲአትር ቤት ያካሄድ የነበረ ሲኾን ይህም ፕሮግራም በመጪው አዲስ ዓመት እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

አውራምባ ታይምስ የመረጃ ምንጮቹን እንዲያሳውቅ በመንግስት መጠየቁን ገለጸ

This post is available in: ኸንግሊስህሳምንታዊው የአማርኛ ጋዜጣ አውራምባ ታይምስ ለዜና ዘገባ የሚጠቀምባቸውን የመረጃ ምንጮች በአንድ ሳምንት ውስጥ እንዲያሳውቅ  በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን መጠየቁን ገለጸ። ጋዜጣው በድረ ገጹ እንደገለጸው ባለስልጣኑ ጥያቄውን ያቀረበው በዋና ዳይሬክተሩ አቶ ደስታ ተስፋው ተፈርሞ ለጋዜጣው በትናትናው ዕለት በደረሰው ደብዳቤ አማካኝነት ነው። የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ቀድሞ በማስታወቂያ ሚኒስቴር ስር ይካሄድ የነበረውን ለጋዜጦች ፍቃድ  [...]

This post is available in: ኸንግሊስህ

ሳምንታዊው የአማርኛ ጋዜጣ አውራምባ ታይምስ ለዜና ዘገባ የሚጠቀምባቸውን የመረጃ ምንጮች በአንድ ሳምንት ውስጥ እንዲያሳውቅ  በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን መጠየቁን ገለጸ።

ጋዜጣው በድረ ገጹ እንደገለጸው ባለስልጣኑ ጥያቄውን ያቀረበው በዋና ዳይሬክተሩ አቶ ደስታ ተስፋው ተፈርሞ ለጋዜጣው በትናትናው ዕለት በደረሰው ደብዳቤ አማካኝነት ነው። የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ቀድሞ በማስታወቂያ ሚኒስቴር ስር ይካሄድ የነበረውን ለጋዜጦች ፍቃድ  የመስጠት፣ ክትትል እና ቁጥጥር የማድረግ ተግባራት የተረከበ መስሪያ ቤት ነው።

አውራምባ ታይምስ የመረጃ ምንጮቹን እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2002 ዓ.ም እንዲያሳውቅ ቀነ ገደብ እንደተሰጠው በድረ ገጹ ላይ አስፍሯል። “በኢትዮጵያ ሕገ መንግስት መሠረት አንድ ጋዜጠኛ ለፍርድ ቤቶች ሳይቀር የመረጃ ምንጭ የማሳወቅ ግዴታ እንደሌለበት በግልጽ የተደነገገ ቢሆንም ብሮድካስት ባለስልጣን በ‹ሬጉላቶሪ› ሽፋን ሕገ መንግስቱን የሚጥስ ጥያቄ መጠየቁ የጋዜጣው ባልደረቦችን አስገርሟል” ሲል በጋዜጣው በኩል ያለውን ስሜት አንጸባርቋል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋዜጣው ከሽያጭና ከማስታወቂያ የሚያገኘውን የፋይናንስ ሪፖርት እንዲያሳውቅ በደብዳቤው ጨምሮ መጠየቁን የሚገልጸው አውራምባ ታይምስ መስሪያ ቤቱ “በአዋጅ ከተሰጠው ሀላፊነት ውጪ” ጥያቄውን ማቅረቡን ያስረዳል። “ይህን የመጠየቅ ኃላፊነት የተጣለበት የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን መሆኑ እየታወቀ ብሮድካሰት ባለስልጣን ይህንን መጠየቁ ብዙዎችን አስገርሟል” ሲል በድረ ገጹ አስነብቧል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

“ሚዪዚክ ካፌ” ! የት ነው?

አዲሱ ካፌ ማርኮዎት ወደ ውስጥ የሚገቡ ከኾነ በስተቀኝ በኩል ባለው በውኃማ ብጫ ቀለም በተቀባው ግድግዳ ላይ ቀይ ጊታር ተሰቅሎ ያያሉ። ከአንድ ሜትር ርቀት ላይ ደግሞ ሳክስፎን። ከመግቢያው በስተ ግራ ባለው ግድግዳ ላይ በጥቁር እና ነጭ ፎቶ ግራፍ አለ። በዚህ ፎቶ ግራፍ ላይ “የወርቃማው የሙዚቃ ዘመን” ፍሬ የኾኑት ጥላሁን ገሰሰ፤ ግርማ ነጋሽ እና መሐሙድ አሕመድ በአንድ ላይ ኾነው ይታያሉ። የዘፋኞቹ ፎቶ ግራፍ ለቤቱ ግርማ ሞገስን ችሮታል።

This post is available in: ኸንግሊስህ

(ገዛኸኝ ይርጋ)

በሙዚቃ ሥራቸው ታዋቂ የኾኑ ሁለት ባለሞያዎች እና አንድ የሙዚቃ ተማሪ በአንድ ጠረጴዛ ላይ ከበው እየተሳሳቁ ያወራሉ፤ እዚህ ፒያሳ ከመሐሙድ ሙዚቃ ቤት 60 ሜትር  ያህል ዝቅ ብሎ በተከፈተ አንድ አዲስ ካፌ ውስጥ። የኢትዮጵያ ሙዚቀኞች ማኅበር ፕሬዝዳንት እና ፒያኒስቱ ዳዊት ይፍሩ፣ የሙዚቃ ሐያሲ እና ባለሞያው ሰርጸ ፍሬ ስብሐት እና የሙዚቃ ተማሪው። ጥቂት የውጭ አገር ዜጎች የተለያየ ቦታ ላይ በተን ብለው ቡና እና ማኪያቷቸውን እየቀማመሱ ቁጭ ብለዋል። ካፌው “ሙዚቃ”፣  ሙዚቃ” ይሸታል።

አዲሱ ካፌ ማርኮዎት ወደ ውስጥ የሚገቡ ከኾነ  በስተቀኝ በኩል ባለው በውኃማ ብጫ ቀለም በተቀባው  ግድግዳ ላይ ቀይ ጊታር ተሰቅሎ ያያሉ።  ከአንድ ሜትር ርቀት ላይ ደግሞ ሳክስፎን። ከመግቢያው በስተ ግራ ባለው ግድግዳ ላይ በጥቁር እና ነጭ ፎቶ ግራፍ አለ። በዚህ ፎቶ ግራፍ ላይ “የወርቃማው የሙዚቃ ዘመን” ፍሬ የኾኑት ጥላሁን ገሰሰ፤ ግርማ ነጋሽ እና መሐሙድ አሕመድ በአንድ ላይ ኾነው ይታያሉ። የዘፋኞቹ ፎቶ ግራፍ ለቤቱ ግርማ ሞገስን ችሮታል። ያሉት ፒያሳ ነው፤ በቅርቡ በዐሥር ሙዚቀኞች ጥምረት በተከፈተው “ሚዩዚክ ካፌ”።

ከዐሥሩ መሥራቾች መካካል መዝሙር ዮሐንስ ፣ አሰፋ ማሞ፣ እንዳሻው ነጋሽ፣ ጌታሁን ወርቅነህ፣ እና አሸብር ዓለሙ ጥቂቶቹ ሲኾኑ ሌሎችም ይገኙበታል። ፒያኒስቱ ዳዊት ይፍሩ እና የሙዚቃ ሐያሲው ሰርጸ በካፌው ውስጥ መገኘታቸው አስደስቷቸዋል። በቀጥታ ከሙዚቃ ጋራ ግንኙነት ያለው ካፌ በዚህ ስፍራ በመከፈቱ። መሥራቾቹ  ካፌው የተከፈተበት ዋና ዓላማ የሙዚቃ ባለሞያዎች እርስ በርሳቸው እና ከአድማጮች ጋራ የሚገናኙበትን መድረክ መክፈት እንደኾነ ይናገራሉ። ከመሥራቾች አንዱ የኾነው እንደሻው ነጋሽ “አርቲስት እና ሕዝብ ተቀራርቦ ሻይ ቡና የሚልበትን ምቹ ኹኔታ መፍጠር፤ አርቲስት እና አርቲስትም እርስ በርሱ በካፌ ውስጥ የሚገናኝበትን መድረክ ማዘጋጀት ትልቁ ግባችን ነው” ይላል።

ሌላኛው ከመሥራቾቹ አንዱ የኾነው መዝሙር ዮሐንስ ካፌው የሙዚቃ አፍቃርያን መሰባሰቢያ መኾን በመቻሉ አዲስ ደስታ እንደፈጠረለት የሚያሳየው ከፊቱ ላይ በማይጠፋ የማያቋርጥ ፈገግታ ነው። ከእነ ፈገግታው አንድ የውጭ አገር ዜጋ ከበሩ አቅጣጫ ሲመጣ ዐይቶ በእንክብካቤ ተቀበለው። እንግዳውን መቀመጫ ከሰጠው በኋላ ወደ እነ ዳዊት ይፍሩ ጠረጴዛ አመራ። ሒሳብ ለመክፈል ጥያቄ ሲያቀርቡለት “እናንተን የመሰለ ሰው በቦታው እንዲገኝ አስበን በመምጣታችሁ ጋባዦቹ እኛ ብንኾን እንመርጣለን” አላቸው።

ያኔ ኩልል ብሎ እንደ ወንዝ ውኃ ይወርድ የነበረው በመሣርያ የተቀነባበረ ሙዚቃ በስሱ ይሰማ ነበር። “በአብዛኛው ቤቱ ከተከፈተ ጀምሮ ወደዚህ እየመጣሁ ምን ዐይነት ሙዚቃ እንደሚከፈት ታዝቤያለሁ። ያለማቋረጥ የሰማሁት በ50ዎቹ እና በስድሳዎቹ የተዘፈኑ ዘፈኖችን ነው፤ እነርሱ በመሣርያ ተቀነባብረው እዚህ ይሰማሉ” ይላል ሰርጸ በተመላለሰበት አጋጣሚ የተከታታለውን ሲያስረግጥ።

ከመግቢያው በስተ ግራ ባለው ግድግዳ ላይ የተሰቀለውን የጥላሁን ገሠሠ፣ ማሕሙድ አህመድ እና ግርማ ነጋሽን  ባለ ጥቁር እና ነጭ ፎቶ ግራፍ በተመስጦ የሚመለከት አንድ ወጣት፣ በካፌው ውስጥ ብዛት ያለው የሙዚቀኞችን ፎቶ ማየት ፈልጓል። “ይኹንና ቤቱ የታሰበውን ያህል ምስል በቦታው ላይ ለዕይታ አስቀምጧል ብዬ አላስብም፤ ሚዩዚክ ካፌ ነው ብዬ አስቤ ስመጣ ከአገር ውስጥም ኾነ ከአገር ውጭ ያሉ ሙዚቀኞችን እና የሙዚቃ ታሪክን የሚያስታውሰኝ ነገር እንዳይ እሻለኹ” ይላል። ለወጣቱ ካፌው ገና የልቡን አላደረሰለትም።

የሙዚቃ ባለሞያዎቹ ይህን አስተያየት እና ሐሳብ እንዳለስፈላጊ ነገር አልቆጠሩትም፤ ይልቁንም ሐሳቡ በእነርሱም ውጥን ውስጥ ያለ እና ተጨማሪ ፎቶዎች እንዲኖሩ ማድረግ ነው። ይኹን እንጂ ካፌውን ሙሉ ለሙሉ የፎቶ ጋላሪ የማድረግ ሐሳብ የላቸውም፤ በእነርሱ እምነት እጅግ የተሻሉ የሚባሉትን እና ተመራጭ ናቸው ብለው የሚያስቧቸውን ፎቶዎች በቅርቡ ለማምጣት ማሰባቸውን ተናግረዋል።

የሚዩዚክ ካፌ ሐላፊዎች እና መሥራቾች የአርቲስቱንም ኾነ የሌላውን ደንበኛ ትኩረት ለመሳብ አንድ ተጨማሪ አገልግሎትም እንደመሳቢያ አድርገው ያቀርባሉ። ጠዋት ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ግድም ለሚመጣ እና ለሚገኝ ታዳሚ በቄጤማ የተዋበውን የቡና ማፍያ ስፍራ እየተመለከተ በነጻ የጀበና ቡና ይጋበዛል። ከሰዓት በኋላም እግር የጣለው ታዳሚ ተመሳሳዩ የነጻ ግብዣ በድንገት ይመጣለታል። ሙዚቀኛን እና ሙዚቀኞችን፣ እንዲሁም ሙዚቀኞችን እና አድማጮቻቸውን የማገናኘት ሐሳብ ያለው ካፌ የትኛውም የካፌው ደንበኛ ባዶ እጁን እንዳይመለስ የኦርጂናል ካሴት ሽያጭም ያካሂዳል። ሐሳቡ ኦሪጅናል ካሴት በመግዛት ለራስም የተሻለ ሙዚቃ መስማትን ለማበረታታት እና ሙዚቀኛውም በሕገ ወጥ አታሚዎች ከሚደርስበት የኮፒ ራይት የሕግ ጥሰት እግረ መንገድ ለመታደግ ነው። “ሙዚቃውን እና ሙዚቀኛውን ለማሳደግ ይህ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል” ይላሉ መሥራቾቹ። አንድ ደንበኛ የሚፈልገውን ካሴት በሰዓቱ ማግኘት ባይችል እንኳን ስሙን እና አድራሻውን ትቶ በመሄድ የሚፈልገውን እንዲያገኝ ምቹ ኹኔታም ተፈጥሮለታል፤ በቀጠሮ መጥቶ እንዲወስድ። “የሚገርመው ግን አብዛኛው ታዳሚ የሚፈልጋቸው ሙዚቃዎች የጥንቶቹን መኾኑን እያየን ነው” ይላሉ እስከ አሁን ባላቸው ጥቂት መረጃ።

ከተከፈተ አንድ ወር ከዐሥራ አምስት ቀን የኾነው ካፌ ገና ከአሁኑ በደራ ገበያ ከታወቁት መካከል አንዱ ለመኾን እየተንደረደረ ነው። መሥራቾቹ እንደሚያስረዱት ከኾነ ይህን ካፌ ለመክፈት ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ተደርጎበታል። የእነርሱ ሐሳብ በአንድ ካፌ ብቻ ተገድቦ መቆየት ሳይኾን የራሱ የኾነ ቅርንጫፍ እንዲኖረው ማድረግ ጭምር ነው። ከአዲስ አበባ ስፋት አንጻር ሁሉም አርቲስትም ኾነ ታዳሚ በአንድ ቦታ ላይ እንዲገኝ ማድረግ ወይም እንዲመጣ ማሰብ የሚቻልበት ጊዜ ላይ አለመኾናቸው በቅርጫፍ የማስፋፋት ሐሳብን እንዲያተኩሩበት እንዳደረጋቸውም ያስረዳሉ።

ባለፉት 90 ቀናት ውስጥ ወደዚህ ካፌ ጎራ ብለው ሻይ ቡና ካሉት ውስጥ ሐመልማል አባተ፣ ፀሐዬ ዮሐንስ፣ ማዲንጎ አፈወርቅ፣ ገረመው አሰፋ፣ መስፍን በቀለ፣ ጌቱ ኦማሂሬ፣ ሃይማኖት ግርማ፣ ዘሪሁን ደምሴ እና ጌታቸው ኀይለ ማርያም ከብዙዎቹ ጥቂቶቹ ናቸው። ገና ብዙዎች ጎራ እንዲሉ እንፈልጋለን የሚሉት መሥራቾቹ የሞያ አጋሮቻቸው እንዲጎበኟቸው እና ሐሳባቸውን እንዲያጋሯቸው ይሻሉ። የሐሳብ ፍጭት፣ የእርስ በርስ የሙዚቃ ውይይት እና ስለ ዕድገቱ የመነጋገሪያ ጊዜ ማግኘት ዋነኛ ዓላማው በኾነው ካፌ ውስጥ የአድማጭን የሙዚቃ ፍላጎት ለማርካት መሥራት የሁሉም ሙዚቀኛ ግብ መኾን አለበት የሚል መነሻ አለው። ካፌው ከተከፈተ ጀምሮ ግን የአገር ውስጥም ኾነ የውጭ አገር የሙዚቃ አፍቃሪዎች የሚጠይቁት የካሴት ዐይነት ወደ ጥንቱ ያጋደለ ነው፤ ወርቃማ ተብሎ ወደሚጠራው ዘመን። አብዛኞቹ የእነ ሜሪ አርምዴን፣ የአስናቀች ወርቁን፣ የአሰፋ አባተን፣ እና የካሳ ተሰማን ሥራዎች ያለማቋረጥ ይጠይቃሉ። በሚዩዚክ ካፌ ውስጥ የታየው ጥቂት የኾነው የአድማጭ ፍላጎት መመዘኛ ወደ 50ዎቹ እና ስድሳዎቹ ሄዷል። የዚህ ዘመን ሙዚቀኞችም ኾኑ ባለፈው ዘመን የነበሩት ሙዚቀኞች ወደ ካፌው ጎራ እያሉ አድማጫቸው እንዴት እንደሚያያቸው እና እንደሚለካቸው መመልከት ሳይኖርባቸው አይቀርም፤ በዚያውም የካፌውን ሐሳብም ምሉዕ ለማድረግ፤ በሙዚቀኞች እና በአድማጮቹ መናኸርያ።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

በአዲስ አበባ ከተማ ለነዋሪዎች አዲስ መታወቂያ ሊታደል ነው

አዲሱን መታወቂያ መምጣት የኢሕአዴግ መንግሥት ለደኅንነት ሥራ ይበልጥ ሊጠቀምበት እንደሚችል እየተነገረ ነው

This post is available in: ኸንግሊስህ

(ሙሉ  ገ.)

የአዲስ አበባ ክልል መስተዳድር በከተማዋ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን በቅጡ ማወቅ ስለተሳነው በ2003 ዓ.ም የበጀት ዓመት መጀመርያ አዲስ መታወቂያ ሊሰጥ መኾኑንን ምንጮቻችን ገለጹ። አዲሱ መታወቂያ የነዋሪውን ሰፊ ዝርዝር መረጃ እንደሚይዝ እና ተመሳሳይ በኾነ ስም ከሌላ ክፍለ ከተማ እና ክልል ሐሰተኛ መታወቂያ እንዳይወጣ የሚረዳ ዲጂታል የመረጃ መረብም ይኖረዋል ተብሏል። አዲሱ መታወቂያ የአገር ውስጥ ፓስፖርት ኾኖ ስለሚያገለግል መንግሥት  ለደኅንነት ሥራ  ይበልጥ ሊጠቀምበት እንደሚችል ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡ቀደም ሲል ጥቅም ላይ የዋሉ መታወቂያ ካርዶችን እና የያዙትን የተሳሳቱ መረጃዎች መስተዳድሩ በቅርቡ እንደሚያመክን ምንጮቻችን ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ከዚህ ጋራ በተያያዘ በአዲስ አበባ የሚገኙ 99 ቀበሌዎች ታጥፈው ወደ ወረዳነት ሊያድጉ እንደኾነም ታውቋል። በዚህ መሠረትም የአገልግሎት ደረጃቸው ከፍ ብሎ በክፍለ ከተማ ደረጃ ይሰጡ የነበሩ አገልግሎቶች የፍትሕ ቢሮ፣ የልደት፣ የሞት፣ የጋብቻ እና የፍቺ ሰርተፍኬት አገልግሎቶች ወደ ወረዳ ሥራ እንዲወርዱ ይደረጋል። “ለደኅንነት ሥራ ሊያግዝ እንደሚችል የተነገረለት ይኸው የመታወቂያ ዕደላ ቀበሌዎቹ ወደ ወረዳነት በሚሸጋገሩበት በሚቀጥለው ዓመት መጀመሪያ ተግባራዊ  ይኾናል ተብሏል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

ኢሕአዴግ አዲስ የአባልነት ምልምላ ሊጀምር ነው

- ከዩኒቨርስቲዎች፣ ከመሰናዶት ትምህርት ቤቶች እና ከንግዱ ማኅበረሰብ መካከል ብዛት ያላቸውን አባላት ለመመልመል ዕቅድ ተይዟል
- ሁሉን አቀፍ የአባላት ምልመላው ከኢሕአዴግ የአውራ ፓርቲነት ዕቅድ ጋራ ይያያዛል

This post is available in: ኸንግሊስህ

(ሙሉ ገ.)

ኢሕአዴግ ከሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል አዲስ አባላትን ለመመልመል የሚያስችለውን አሠራር ወደ አስፈፃሚው አካል በማውረድ በተጠናከረ መልኩ አዲስ ምልመላ ለማድረግ ሰፊ እንቅስቃሴ እንደሚጀምር የፓርቲው የውስጥ ምንጮች ለአዲስ ነገር ተናገሩ።

የግንቦቱ ምርጫ ካለፈ ከወራት በኋላ በግምገማ ተወጥረው ካሳለፉት የኢሕአዴግ አባላት መካከል ብዙዎቹ የሚንሳፈፉ ሲኾን በእነርሱ ምትክ አዲስ አባላቶች ወደ ድርጅቱ ለማስገባት እንቅስቃሴ ተጀምሯል። የአሁኑ እንቅስቃሴ ከምርጫው በፊት ከነበረው የአባላት ምልመላ የሚለየው የአባላትን ቁጥር ከመጨመር ይልቅ ጥራት ላይ ማመዘን  የሚል ዕቅድ ወደ አስፈጻሚው አካል በመምጣቱ ነው ሲሉ የዜና ምንጮቻችን አስረድተዋል።

በዚህ የፓርቲው “የአባላት ማስፋፊያ እና ማጠናከሪያ ፕሮጀክት” ላይ አዲስ አባል ለመመልመል ትኩረት ከሚሰጥባቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ውስጥ ዩኒቨርስቲዎች እና የመሰናዶ ትምህርት ቤቶች፣ የወጣት ማእከላት እና  ሊጎች፣ የመንግሥት መሥርያ ቤቶች፣ የንግዱ ማኅበረሰብ እና አገልግሎት ሰጪዎች ይገኙበታል፡፡

ምልምል አባላት ለአንድ ወር በዝነኛው የአላጌ የግብር እና ማሠልጠኛ ተቋም በመግባት በኢሕአዴግ ፕሮግራም እና ሕገ ደንብ ላይ ተወያይተው በእጩነት ይመዘገባሉ፤ ከዚያም በሕዋስ ተደራጅተው በወቅታዊ ኹኔታዎች ላይ ከነባር አባላት ጋራ በመወያየት በድርጅቱ ልሳን በአዲስ ራዕይ እና በሕዳሴ ጋዜጣ ላይ በሚወጡ ጽሑፎች ላይ በመወያየት የፖለቲካ አቋማቸውን እያዳበሩ በፓርቲ ሥራ ውስጥ ይሳተፋሉ፡፡

ይህ ሁሉን ዓቀፍ የአባላት ምልመላ ኢሕአዴግ በአገሪቱ ውስጥ ብቸኛው አውራ ፓርቲ ኾኖ ለረዥም ጊዜ እንዲቆይ ከሚያደርገው ዕቅድ ጋራ ቀጥተኛ የኾነ ተያያዥነት አለው መኾኑን ምንጮቻችን ለአዲስ ነገር አስረድተዋል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

የኣዳም ረታ “ማኅሌት” በገበያ ላይ ዋለ

በ1981 ዓ.ም በኩራዝ አሳታሚ አማካኝነት ለገበያ ቀርቦ የነበረው የአዳም ረታ የመጀመርያ የአጫጭር ልብ ወለዶች መድብል ከሌሎች ሥራዎች ጋራ ዛሬ ለአንባብያን በይፋ ቀረበ።ከ21 ዓመት በኋላ ለዳግም ኅትመት የበቃው “ማኅሌት” ያለ ምንም አርትኦት እንደወረደ የቀረበ ሲኾን “ኣባ ደፋር እና ሌሎችም አጫጭር ታሪኮች” ከሚለው እና በ1977 ዓ.ም ከታተመው መጽሐፍ ውስጥ የተካከተቱት አራት አጫጭር ልብ ወለዶች በማኅሌት ውስጥ እንዲቀርቡ ተደርገዋል።

This post is available in: ኸንግሊስህ

በ1981 ዓ.ም በኩራዝ አሳታሚ አማካኝነት ለገበያ ቀርቦ የነበረው የአዳም ረታ የመጀመርያ የአጫጭር ልብ ወለዶች መድብል ከሌሎች ሥራዎች ጋራ ዛሬ ለአንባብያን በይፋ ቀረበ። ይህን ለአዲስ ነገር የገለጹት የማኅሌት አሳታሚ የኾኑት አቶ አቤል ሰይፈ ናቸው። ከ21 ዓመት በኋላ ለዳግም ኅትመት የበቃው “ማኅሌት” ያለ ምንም አርትኦት እንደወረደ የቀረበ ሲኾን “ኣባ ደፋር እና ሌሎችም አጫጭር ታሪኮች” ከሚለው እና በ1977 ዓ.ም ከታተመው መጽሐፍ ውስጥ የተካከተቱት አራት አጫጭር ልብ ወለዶች በማኅሌት ውስጥ እንዲቀርቡ ተደርገዋል።

ከዚሁ የማኅሌት ኅትመት ጋራ አያይዘው አቶ አቤል ሰይፈ ለአዲስ ነገር እንዳስረዱት “ከዚህ በፊት ለኅትመት የበቃው የአዳም ረታ ማኅሌት በአርትኦት ምክንያት ብዙ ነገሮች ተቆርጠው ወጥተውበት ነበር” ሲሉ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ በ“ማኅሌት”ም ኾነ በ“አባ ደፋር” ውስጥ ያሉትን የደራሲውን ሥነ ጽሑፋዊ ሥራዎች በዚህ ዘመን ውስጥ ያሉ አንባብያን ሊያገኟቸው ስላልቻሉ ይህን የአንባብያኑን ተደጋጋሚ ጥያቄ ለመመለስ ስንል ለማሳተም ችለናል” ብለዋል።  በዚሁ ሁለተኛ ሕትመት ውስጥ ከዚህ ቀደም ለኅትመት ያልበቃ አንድ የአዳም ረታ የአጭር ልብ ወለድ ድርሰት ተካቷል።  ዛሬ በገበያ ላይ የዋለው የአዳም ረታ “ማኅሌት” 256 ገጾች ያሉት ሲኾን በ25 ብር በይፋ መሸጥ ተጀምሯል። ይህን መጽሐፍ ያሳተመው ኤማይ ማተሚያ ቤት  ነው።

አዳም ረታ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በ “ግራጫ ቃጭሎች”፣ በ“እቴ ሜቴ የሎሚ ሽታ”፣ በ“አለንጋ እና ምስር” እንዲሁም “ከሰማይ የወረደ ፍርፍር” በሚሉት መጻሕፍቱ ተነባቢነትን እና ተወዳጅነትን ያተረፈ ደራሲ ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘ ዜና የፍቅረ ማርቆስ ደስታ “የዘርሲዎች ፍቅር” በድጋሚ ሊታተም መኾኑ ታውቋል። ከገበያ ጠፍቶ የነበረው የደራሲ ፍቅረማርቆስ ደስታ ሥራ የኾነው “የዘርሲዎች ፍቅር” የተሰኘው ልብ ወለድ መጽሐፍ በማኅሌት አሳታሚ በሚቀጥለው ሳምንት መጀመርያ ላይ ለገበያ ይቀርባል።።

ይህ መጽሐፍ ባለ 180 ገጽ ሲኾን በንግድ ማተሚያ ቤት እንደሚታተምም ታውቋል። ይኸው መጽሐፍ በ22 ብር ለአንባብያን ይቀርባል። ደራሲ ፍቅረ ማርቆስ ደስታ “ከቡስካ በስተጀርባ ድንግል ውበት”፣ ”ኢቫንጋዲ” ፣ “አቻሜ”፣ “የንስር ዐይን”፣ የጀነራል ጃጋማ ኬሎን የሕይወት ታሪክ የሚዳስስ “ጃጋማ ኬሎ” የተባለውን ግለ ታሪክ እና  “The Land of The Yellow Bull”  በተሰኘው   መጽሐፉ ይታወቃል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

በረመዳን የጁምዐ ስግደት ላይ መጠነኛ ችግር ደረሰ

ይህ የመፈንከት አደጋ ከደረሰ በኋላ ኹኔታው እየከተካረረ በመሄዱ የፌደራል ፖሊስ በአካባቢው በመገኘት ችግሩን ለመፍታት ሙከራ አድርጓል። ይኹንና ሰጋጆቹ ድርጊቱን የፈፀመው ወጣት ተላልፎ ካልተሰጠን አንሄድም በማለት ለረዥም ሰዓት ከፎቁ መግቢያ ላይ በመኮልኮል ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ ነበር። ፖሊስ በበኩሉ ጥፋተኛው ግለሰብ ማን እንደኾነ እያጣራን ስለኾነ ወደ ጅምር ሕንፃው መግባት አትችሉም በሚል ተከላክሏል።

This post is available in: ኸንግሊስህ

በትላንትናው ዕለት  በጁምዐ የሶላት ስግደት ወቅት በግንባታ ሂደት ላይ ባለው የድር ተራ የገበያ ማእከል ፎቅ ማንነቱ ባልታወቀ ግለሰብ ተወረወረ በተባለ ድንጋይ በአንድ ሰጋጅ ላይ መጠነኛ የመፈንከት አደጋ ደረሰ።

ይህ የመፈንከት አደጋ ከደረሰ በኋላ ኹኔታው እየከተካረረ በመሄዱ የፌደራል ፖሊስ በአካባቢው በመገኘት ችግሩን ለመፍታት ሙከራ አድርጓል። ይኹንና ሰጋጆቹ ድርጊቱን የፈፀመው ወጣት ተላልፎ ካልተሰጠን አንሄድም በማለት ለረዥም ሰዓት ከፎቁ መግቢያ ላይ በመኮልኮል ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ ነበር።  ፖሊስ በበኩሉ ጥፋተኛው ግለሰብ ማን እንደኾነ እያጣራን ስለኾነ ወደ ጅምር ሕንፃው መግባት አትችሉም በሚል ተከላክሏል።

በአንዋር መስጊድ የረመዳን ጁምዐ ሶላት ወቅት ከፍተኛ የትራፊክ መስተጓጎል የተከሰተ ሲኾን ከተክለሃይማኖት እና ከጎጃም በረንዳ መሥመር ምንም ዐይነት የመኪና መተላለፍ እንዳይኖር ተደርጎ ቆይቷል። የሰጋጆቹ ቁጥር በአንድ አቅጣጫ ብቻ እስከ ምዕራብ ሆቴል አካባቢ ይደርስ እንደነበረ ታውቋል። የተክለሃይማኖት እና የጎጃም በረንዳ ዋና ዋና መንገዶችም ለትራፊክ ዝግ ኾነው ቆይተዋል። የሰጋጆች ቁጥር በከፍተኛ መጠን መጨመር ከረፋዱ አምስት ሰዓት ጀምሮ የትራፊክ መስተጓጎል ያስከተለ ሲሆን በርከት ያሉ የትራፊክ ፖሊሶች በአራቱም የመስጊዱ አቅጣጫ በመገኘት ችግሩን ለማቃለል ጥረት ሲያደርጉ ነበር፡፡

የሶላት ስግደቱ ከተጠናቀቀ በኋላ ኹኔታው ወደ አላስፈላጊ አቅጣጫ እንዳያመራ በመስጋት ፖሊስ ከአንዋር መስጊድ አስተባባሪዎች ጋራ በመነጋገር አማኙ ወደመጣበት እንዲበተን ባደረገው ከፍተኛ የማረጋጋት ሥራ ችግሩ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ ሊረግብ ችሏል። ድርጊቱን ፈጽመዋል የተባሉ ሁለት ግለሰቦችም በቁጥጥር ሥር እንደዋሉ ዋሉ ታውቋል።

ከዚህ በፊት በተመሳሳይ የጁምዐ ሶላት ወቅት “ማርስ ሆቴል” ተብሎ ከሚጠራ ፎቅ ላይ በአማኞች ላይ ውሃ ደፍቷል የተባለን ወጣት ፖሊስ አሳልፎ ባለመስጠቱ የሕንፃው መስታወት ሙሉ በሙሉ መርገፉ የሚታወስ ነው።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

ሼ-መንደፈር በመርካቶ

አንዋር መስጊድና ራጉኤል ቤተ-ክርስቲያንን በሚለዩት አጥሮች መሀል ባለው ጎዳና እነዚህ አስፈሪ ጭብጥ ያላቸው የህትመት ውጤቶች እንደቆሎ ይቸረቸራሉ፡፡ ከሁለቱም ጎራ፡፡ ይህንን ፅሁፍ ለማሰናዳት በስፍራው ባንዣበብኩባቸው ቅፅበቶች ብቻ ያየኋቸውን የህትመት ውጤቶች ብቻ ብዘረዝር ፍርሃቴን ይበልጥ ያሳይልኝ ይሆናል፡፡
‹‹የእየሱስ ማንነት ተደረሰበት…
‹‹ ሚዛኑ ቢጠፋ ወርቁ ጠፋ፣ ሴቶችን የበደለ ክርስቲያን ወይስ ኢስላም››
‹‹ኢየሱስ ነብይ ወይስ ፈጣሪ››
‹‹ቁርአንን ማን ደረሰው››
‹‹የኢየሱስ ማንነት ለእስላሞች መልስ›› ሙሉውን ጽሑፍ ለማንበብ የአማርኛውን ክፍል ይጎብኙ

This post is available in: ኸንግሊስህ

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

ሼ-መንደፈር በመርካቶ

ከሁለቱም ጎረቤት የእምነት ስፍራዎች በድምፅ ማጉያ የሚስተጋቡት ድምፆች እርስበርስ ስለሚራበሹ ምእመናኑ ሁለቱንም ከማዳመጥ ውጭ ምርጫ ያጣሉ፡፡ከሁለቱም ጎራ ያሉ አማኞች ይህ ሁኔታ የሚፈጥርባቸውን እውነተኛ ስሜት ባለውቅም ለእኔ ግን ትርጉሙ የትየለሌ ይሆንብኛል፡፡ በአረብኛና በግእዝ ወደ አምላክ የሚተላለፉ ተማፅኖዎች፡፡…የሁለቱም እምነት ተከታዮች በሀይማኖታዊ ክብረ-በአሎቻቸው ተከታዮቻቸውን ሆ- ብለው አደባባይ እንዲወጡ በማባበል እግረ መንገዳቸውን ጡንቻቸውን ለማሳየት ተጠቅመውበታል፡፡ አንዳንዴ የሀይማኖቶቻቸውን መሰረታዊ አስተምህሮዎች ጭምር በሚጣረስ መልኩ አፀያፊ ቃላት ጨዋ በሚመስል መንገድ ተለዋውጠዋል፡፡

This post is available in: ኸንግሊስህ

(መሐመድ ሰልማን-ከመርካቶ )

ይቺ አገር ፈሪሃ -እግዚአብሔር (በዐረብኛ/ተቅዋ) ያለ ልክ የሰፈነባት የምድራችን ክፍል ናት፡፡ ሕዝቦቿም ለፈጣሪ ተንበርካኪ እና ጨዋዎች ናቸው፡፡ ይህን መግቢያዬን የሚጠራጠር ሰው ካለ በፒያሳ ወይም በመርካቶ እንደ ገብስ ተሰጥቶ እና ተዘርግቶ የሚቸረቸረውን የወርቅ ብዛት ጎራ ብሎ ይመልከት፡፡ በአንድ ወቅት ዛሬ በሕይወት በሌለችው “አዲስ ነገር ጋዜጣ” ላይ (ነፍሷን ይማር) “ኢትዮጵያዊ ድኻ ለምን አይሰርቅም” የሚል ውብ መጣጥፍ ማንበቤ ትዝ ይለኛል፡፡ ጽሑፉ ለመንደርደርያነት ያነሳኹትን ሐሳብ እንደ አንድ ምክንያት የሚቀበለው ይመስለኛል፤ ይቀበለዋልም፡፡

ንቅሳት እንኳ የመስረቅ አቅም አላቸው የሚባሉት የመርካቶ ሌቦች “ኪስ ሲያወልቁ” ያገኙትን መታወቅያ እና ጠቃሚ ሰነድ ለባለቤቱ የመመለስ ጥሩ ባህል አላቸው፤ ምንም ቢሰርቁ ሰው እስከመግደል ድረስ የሚጨክን አንጀት የላቸውም። እንዲያው ሳስበው የእንጀራ ጉዳይ ኾኖባቸው እንጂ ባይሰርቁ ደስ የሚላቸው ይመስለኛል፡፡ የአገሬ ሌቦች ፈሪሃ-እግዚአብሔር ያደረባቸው ለመኾናቸው “ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ” የለኝም የምለውም ለዚሁ ነው፡፡

ኢትዮጵያ በሁለቱም ታላላቅ ሃይማኖቶች ቅዱሳት መጻሕፍት ላይ ተጠቅሳለች፤ ለያውም በተደጋጋሚ፡፡ አሜሪካም ኾነች እንግሊዝ ይህን የመጠቀስ ዕድል አላገኙትም፡፡ አሜሪካ ለከፋቸው ስደተኞች መጠለያ መኾን የጀመረችው ገና በቅርቡ ነው፡፡ አገሬ ኢትዮጵያ ግን ገና ያኔ ጥንት በሰባተኛው ክፍለ ዘመን የነቢዩ መሐመድን ደቀ መዛሙርት (ሰሀባዎች) ‹‹ግሪን ካርድ›› ሰጥታለች፡፡ ለነገሩ ከአሜሪካ ጋራ ምን አፎካከረን?!ኢትዮጵያ በቅዱሳት መጻሕፍት በተደጋጋሚ ተጠቀሰች ስንል መርካቶንም እንደሚያጠቃልል ልብ ማለት ያሻል፡፡ ምክንያቱም መርካቶ የምትገኘው ኢትዮጵያ ውስጥ ነው፤ ኢትዮጵያም መርካቶ ውስጥ አለች።

በልጅነቴ ከሌባ ጋራ የተዋወቅኩት በታላቁ አንዋር መስጊድ ውስጥ ነው፡፡ የመርካቶው ታላቁ አንዋር መስጊድ በታላላቅ ሌቦች በተደጋጋሚ ይደፈራል፡፡ ለሶላት ጫማቸውን ያወለቁ ምዕመናን ፊታቸውን ወደ ፈጣሪ መልሰው ጎንበስ ቀና ሲሉ የጫማ ሌቦች ምድራዊ ተግባራቸውን ያከናውናሉ። በዚህ ኹኔታ ቢያንስ በቀን አንድ ሌባ መስጊድ ውስጥ ይያዛል፡፡ በዚህን ጊዜ ሌባው ከመቅደስ ወደ መስጊዱ ግቢ ይወሰድ እና “የዱላ እንካ ቅመሱን” እስኪጠግብ ይሰጠዋል። ሁሉም ሰው ጡቻ፣ ጥፊ፣ ቡጢ፣ ጫማ-ጥፊ፣ ቃሪያ ጥፊ፣ የፊት ጠረባ/የኋላ ጠረባ ወዘተ ያቀምሰዋል፡፡ ጀለቢያ ያጠለቁ ትልልቅ እና ወፋፍራም እንዲሁም ቦርጫም ሰዎች እንኳ ሳይቀሩ ቀሚሳቸውን ሽቅብ እየሰበሰቡ እግራቸውን ሌባው ላይ ለማሳረፍ ይሞክራሉ፡፡ ያ ሁሉ ምዕመን አንድ ሌባ ሲደበድብ የሚፈጠረው ትዕይንት ትንግርት የሚሉት ዐይነት ነው። እኔም የድርሻዬን በነጻነት የመሰንዝር አጋጣሚው ስለሚፈጠርልኝ መስጊድ ውስጥ ሌባ በተገኘ ቁጥር ውስጥ ውስጡን ደስ ይለኝ ነበር፡፡ በልጅነት ለወላጆቻቸው ሳይናገሩ መስጊድ አብረውኝ ይመጡ የነበሩ ክርስቲያን ጓደኞቼም በዚሁ ሌባን ተጋግዞ በመደቆሱ ተግባር ይዝናኑበት ነበር፡፡

እኔ ባደኩባት መርካቶ ጥቂት ክርስቲያን ጎረቤቶች ነበሩን፡፡ ‹‹ራጉዔል አይደል ወይ የአንዋር ጎረቤቱ›› እንዲል ቴዲ አፍሮ፡፡ እንደ ዛሬ ረመዳን ሲመጣ አብሮነታችን ይደረጃል፡፡ አብረን ‹‹እናፈጥራለን››፣ ፀሐይ እስክትጠልቅ ጠብቀን ተምር እና ሳምቡሳ አንዳንዴም ሾርባ እንጋራለን፡፡ አንዳንዴ በረመዳን ወቅት ቁርሳቸውን እስከተሲያት ባለመብላት ጭምር በፆም ያግዙኝ ደግሞም ይተባበሩኝ ነበር፡፡ በርግጥ ደህና ቁርስ ሳያገኙ ቀርተውም ሊኾን ይችላል፡፡ በልጅነታችን ከእነዚሁ ጓዶቼ ጋራ በፆም ጉዳይ ላይ መበሻሸቃችን የተለመደ ነበር፡፡ እነርሱ ”ማታ ማታ እየበሉ ቀን ቀን መፆም ምኑ ያስደንቃል?” እያሉ ይሞግቱኛል፡፡ እኔም የተራበችዋን ትንሽ ሆዴን እያሻሸሁ “ሽሮ እና ምስር ግጥም አርጎ እየበሉ ፆምኩኝ እንዴት ይባላል?”  ስል የመልስ ምት እሰጣለሁ፡፡ በብሽሽቁ የማሸነፍ ዕድል የነበረኝ እኔ ነበርኩ፡፡ ምክንያቱም ጓደኞቼ ስጋ እና የስጋ ወጤቶችን የሚያገኙት አልፎ አልፎ በበዐላት ሰሞን ብቻ ነበር፡፡ ይህ ኹኔታም ”እናንተኮ ዓመቱን ሙሉ ሁዳዴ ላይ ናችሁ” እያልኩ እንድዘባበትባቸው አግዞኛል፡፡ያም ኾኖ በረመዳን “ከሲኒማ ራስ” ቴምር እየገዛን እንዝናናለን፣ ቴምር መግዣ ሳንቲም ካጣንም ጥቂት ቴምር እና ጥቂት ሳምቡሳ ከቤት እየደበቅኩ ይዤላቸው እሄድ ነበር፡፡ ክርስቲያን የሰፈር ጓደኞቼ ረመዳን ሲመጣ የሚከፋቸው ዘወትር እሁድ ጠዋት አስፋልት ላይ በምናደርገው የእግር ኳስ ጫወታ ደከም ስለምልባቸው ብቻ ነበር፡፡

እነርሱም ቢኾን ውለታ ለመመለስ ለጥምቀት ጃንሜዳ ይዘውኝ መሄዳቸው አይቀርም፡፡ ለዚያውም አርሞኒካ አስታጥቀው፡፡ “ሆያ-ሆዬ” ጭፈራ ከልጆች ገቢ ማስገኛነቱ ባሻገር ራሱን የቻለ ሃይማኖታዊ ትርጉም እና ሥርዐት ያለው መኾኑን ያወቅኹት ከጎረመስኹ በኋላ ነው፡፡ በልጅነታችን የሃይማኖት ሥርዐቶችን እንፈጽም የነበረው እንደ ባህል እንጂ ከጽድቅ ቆጥረነው አልነበረም።

ማን እንደጀመረው ባይታወቅም በአገሬ ሙስሊም እና ክርስቲያን ተቻችለው ሳይኾን ተዋደው ኖረዋል፡፡ (ተቻችለው የሚለው ቃል ምንኛ ይጎረብጣል!) የእኔ የልጅነት ትውስታ በራሱ በምስክርነት መቅረብ የሚችል ነው፡፡ ከእኒያ የልጅነት ወዳጆቼ መሀል አሁን ብዙዎቻችን ከሃይማኖት መንሸራተት ጀምረናል፡፡ አንዳንዶቻችን በተቃራኒው አምርረናል፡፡ አንዳንዴ “ሆያ-ሆዬ” ክርስቲያናዊ ተግባር እንደኾነ ሲሰበክ እሰማለኹ፡፡ ከሃይማኖቴ ውጭ ሌላ ወዳጅ እንዳላፈራ እጎተጎታለኹ፡፡ በየአጋጣሚው የማነባቸው አዳዲስ መንፈሳዊ መጻሕፍትም ስለ ፍቅር የሚሰብኩበት ቃላት ጎድለውባቸዋል፡፡ ይልቁንም መጪው ዘመን በሃይማኖቴ ላይ አደጋ የሚያንዣብብበት እንደሚኾን የሚተነብዩ እና ነቅቼ እንድጠብቅም የሚያስጠነቅቁ ናቸው፡፡

በተቃራኒው ጎራ የሚጻፉ መጻሕፍትም በተመሳሳይ መልኩ ተናዳፊ ናቸው፡፡ ሃይማኖትን የሚያክል የማይጨበጥ ነገር ቤተ-ሙከራ አስገብተን መረመርነው፣ ዘረዘርነው የሚሉ ቀሳውስት ውዝግብ የሚያስነሱ ነጥቦችን እያነሱ ይሰብካሉ፡፡ ከቤተ-ሙከራው ሲወጡም አማኙን የሚያስቀይም ውጤት ይዘው ይንጎራደዳሉ፡፡ ያንኑ በመጽሐፍ ፣ በሲዲ፣ በቲ-ሸርት ካልታተመልን ይላሉ፡፡የኔዋ የአሁኗ መርካቶ በዚህ ሁሉ ተቃርኖ የተሞላች ናት፡፡ ከሰሞኑ በጋራ የተጀመሩት የፍልሰታ እና የረመዳን ፆሞች ደግሞ ተቃርኖውን አጉልተው እያሳዩኝ ነው፡፡ በተለይም በመርካቶው ሼ- መንደፈር፡፡

ረመዳን እና ፍልሰታ- የሁለት ሳንቲም አንድ ገፅታ

እንዲህ ምዕመናን ልብ በሚገዙበት የፆም ወቅት ግርግር ትንፋሽ ባሳጣት መርካቶ በተሽከርካሪዎች ላይ ተንቀሳቃሽ ቤተ-ክርስቲያኖችን እና መስጊዶችን ታሰማራለች፡፡ በድምፅ ማጉያ ስብከቶች አቅሏን ትስታለች፡፡ መንዙማ እና መዝሙር፣ ዳእዋ እና ስብከት ልክ ባጣ ላንቃ የ“ካሴት ግዙን ትድናላችሁ” ተማጽኖ ያቀርባሉ፡፡ ገነት እና ጀነት የሚገባውን ምዕመን ቁጥር ለማሳደግ የሞንታርቦ ድምፅ ይጨምራሉ፡፡ በድምፅ ጉልበት መንግስተ-ሠማያት ይወረስ ይመስል።

የ16 ቀናት ዕድሜ ያለው የፍልሰታ ፆም ከሁዳዴ ቀጥሎ ምዕመናኑን ወደ ቤተክርስቲያን ደጃፎች የሚጠራ ነው፡፡ ነጠላ ያጣፉ ሴት ምዕመንት በአያሌው ወደ ደብረ ኀይል ቅዱሰ ራጉዔል ቤተክርስቲያን ይጎርፋሉ፡፡ ቁጥራቸው ከፍ ያለ ሙስሊም ምዕመናንም ወደ ታላቁ አንዋር መስጊድ ያለ ልክ ይተማሉ፡፡ 15ኛ ቀኑን ያስቆጠረው የረመዳን ፆም ለዚህ ምክንያት ትመት ነው፡፡ የቀሳውስቱ ቆብ እና የሙስሊም ኮፍያ፣ የምዕመኑ ነጠላ እና የሙስሊም ጀለቢያ ተጣምረው ወደ ጎረቤታሞቹ አንዋር እና ራጉዔል ይገባሉ። ትዕይንቱ በተለይም ዘወትር አርብ የተለየ ግርምትን ይፈጥራል፡፡

በአንዋር መስጊድ እና በቅዱስ ራጉዔል ቤተክርስቲያን አጥሮች መካከል ያለው ርቀት አንድ መኪናን ብቻ ማሳለፍ የሚያስችል ነው። በእነዚህ የአምልኮ ስፍራዎች የሚገኘው ሕዝብ ደግሞ አጥሮቹን አልፎ የሚፈስ ነው። በመኾኑም ምዕመናኑ በዐቢይ የጸሎት ወቅቶች በዙርያቸው የሚገኙትን የተሽከርካሪ ጎዳናዎችን ለመጠቀም ይገደዳሉ፡፡

በተለይም አንዋር መስጊድ በረመዳን የጁምዐ ስግደት የምዕመናኑ ቁ|ጥር በአራት እና አምስት እጥፍ ስለሚጨምር የመርካቶን ሲሶ በጸሎት ስፍራነት ለመጠቀም ይገደዳል፡፡ በደቡብ በኩል እስከ “ሲኒማ ራስ”፣ በምዕራብ እስከ “ጣና ገበያ” አንዳንዴም እስከ “ምዕራብ ሆቴል”፣ በሰሜን እስከ “ጎጃም በረንዳ”  እንዲሁም በምሥራቅ እስከ አሜሪካን ግቢ ድረስ ይዘልቃል፡፡  ይህ ኹኔታ ከሚፈጥራቸው አስገራሚ ትዕይንቶች አንዱ ሰጋጆቹ የራጉዔልን ዙርያ አጥር ለመጠቀም መገደዳቸው ነው፡፡ በዚያን ጊዜ ነጠላ እና አባያ፣ ጥምጣም እና ጀለቢያ ባይፈቅዱትም ትከሻ ለትከሻ፣ መሳ ለመሳ ለመቆም ይገደዳሉ፡፡

ዘወትር ምሽት በረመዳን ወር የሚሰገደው የ‹‹ተራዊህ›› ስግደት ዘለግ ያለ ሰዓትን ይወስዳል፡፡ አማኞች መኪናዎቻቸውን በሁለቱም የእምነት ስፍራዎች ዙርያ እየኮለኮሉ ያቆሟቸዋል፡፡ ሶላት ሲሰግዱም የራጉዔልን አጥር ተደግፈው ጭምር ነው፡፡ መስገጃዎቻቸው የራጉዔልን ሕንፃ በረንዳዎች ጭምር አካሎ ይይዛል፡፡ ዘወትር ምሽት ይህንን አስገራሚ ክስተት ባስተዋልኹ ቁጥር በካሜራ ቀርጾ ለማስቀረት ይዳዳኛል፤ ተሳክቶልኝ ባያውቅም።

የጁምዐ ስግደት ላይ ሃይማኖታዊ ዲስኩር (ኹጥባ) በአሰጋጁ (ኢማሙ) አማካኝነት ይቀርባል። አንዳንድ ጊዜ በተመሳሳይ ከራጉዔል የቅዳሴ ዜማ ይለቀቃል፡፡ ከሁለቱም ጎረቤት የእምነት ስፍራዎች በድምፅ ማጉያ የሚስተጋቡት ድምፆች እርስ በርስ ስለሚራበሹ ምእመናኑ ሁለቱንም ከማዳመጥ ውጭ ምርጫ ያጣሉ። ከሁለቱም ጎራ ያሉ አማኞች ይህ ኹኔታ የሚፈጥርባቸውን እውነተኛ ስሜት ባላውቅም ለእኔ ግን ትርጉሙ የትየለሌ ይኾንብኛል፡፡ በዐረብኛ እና በግዕዝ ወደ አምላክ የሚተላለፉ ተማጽኖዎች፡፡

የቅዱስ ራጉዔል ቤተክርስቲያን እንደ ብዙዎቹ አቻዎቹ አጥሩን አስታኮ ያስገነባው ግዙፍ ሕንፃ ፎቁ ለደብረ ኀይል ቅዱሰ ራጉዔል ትምህርት ቤትነት ሲያገለግል ምድሩ ላይ ያሉት ቤቶች ደግሞ የንግድ ቤት ኾነው ያገለግላሉ። በእነዚህ ሱቆች በአመዛኙ የሞባይል መለዋወጫዎች፣ በስተ ምዕራብ ባሉት ሱቆች ሻንጣ እና ብርድ ልብስ፣ ኦርቶዶክስ ዘ-ተዋህዶ መዝሙር ቤቶች እና በስተ ምሥራቅ ባሉት ሱቆቹ ደግሞ ኢስላማዊ ቁሳቁሶች የሚሸጡባቸው ናቸው፡፡ በዚሁ ሕንፃ ላይ የሚገኘው ዘመናዊው “ሄኒ-ፔኒ ካፌ” ለረመዳን ኢስላማዊ ምግብ እና መጠጦችን ያቀርባል፡፡ ይህ የቅዱስ ራጉዔል ሕንፃ የአርክቴክት ዲዛይኑ የመስቀል ቅርጽ እንዲኖረው ተደርጎ የተሠራ ነው። ኾኖም በሥሩ ከሚገኙት ሱቆች ውስጥ አባያ ( ሙስሊም ሴቶች የሚለብሱት ቀሚስ)፣ ኒቃብ (ፊትን በከፊል የሚሸፍን)፣ ሂጃብ (ጸጉርን የሚሸፍን)፣ ቡርቃ (ከዐይን በስተቀር መላ ሰውነትን የሚሸፍን)  እንዲሁም ጀለቢያ እና መስገጃዎች ይሸጡበታል፡፡ ይህ ኹነት ለአንዳንዶች ከቢዝነስ ፍልስፍና ከፍ ያላለ ትርጉም ሊኾን ይችላል፡፡ ለእኔ ግን ከዚያም የላቀ ትርጉም አለው።

ድህነታችን እና ባህላችን ተጋግዘው የፈጠሩት ጥብቅ ጉርብትና ማኅበራዊ ሕይወታችንን ይጫኑታል፡፡ ይህ ኹኔታ በሃይማኖት መሥመሮችም የሚገለጥበት ጊዜ አለ።  እናቴ እነ መምሬ ቤት ጠበል ቅመሱ ሲባል ከመሄድ አትቦዝንም። ከክርስቲያን አብሮ አደጎቼ ጋራ የነበረን ወዳጅነት አንድ ጊዜም ቢኾን በሃይማኖት ስሜት የተቀኘበት ወቅት ትዝ አይለኝም። አንዳንድ ጓደኞቼ አሁንም ድረስ የኢስላም አቡጊዳ የኾኑትን የዐረብኛ ፊደላትን እና ጥቂት የቁርዐን አንቀጾችን በቃላቸው ማነብነብ እንደሚችሉ አስተውያለኹ፤  እንደ እኔ ከሙስሊም ቤተሰብ ለወጡ ብዙ ዜጎች ቄስ ትምህርት ቤት ሙዋዕለ-ሕፃናት እንጂ የክርስትያን ተቋም ኾኖ ተሰምቶን አያውቅም፡፡

ይህ ስሜት በአዲሱ ትውልድ እየተሸረሸረ ይመስለኛል። የአሁን ሙስሊም ወዳጆች አገራዊ ከኾኑ ጉዳዮች አልፈው ለኢራቅ ሕዝቦች አለኝታነት ይሰማቸዋል። ይህን እንደ ስኅተት ባላየውም ከስሜታቸው ጀርባ ያለው ምስል ግን ያስፈራኛል። ቤታቸው ውስጥ አሁን አሁን የማያቸው መጻሕፍትም ኾኑ ሲዲዎች የጽዮናዊት እሥራዔልን ሤራ እንዴት መበጣጠስ እንደሚቻል የሚያትቱ፤ አልያም ደግሞ ሌሎች ሃይማኖቶች እንዴት ኢስላምን ለማጥፋት ቀን ተሌት እየሠሩ እንደኾኑ ለማሳመን የሚጥሩ ናቸው። በየሳምንቱ አርብ የሚወጡ መንፈሳዊ ጋዜጦችም ቢንላደን በኔቶ ሠራዊት ላይ ያደረሰውን ጥፋት አጋነው የሚዘግቡ ናቸው፡፡

አንዋር መስጊድን እና ራጉዔል ቤተ-ክርስቲያንን በሚለዩት አጥሮች መሀል ባለው ጎዳና እነዚህ አስፈሪ ጭብጥ ያላቸው የኅትመት ውጤቶች እንደ ቆሎ ይቸረቸራ፤ ከሁለቱም ጎራ። ይህንን ጽሑፍ ለማሰናዳት በስፍራው ባንዣበብኩባቸው ቅጽበቶች ብቻ ያየኋቸውን የኅትመት ውጤቶች ብቻ ብዘረዝር ፍርኀቴ ይበልጥ ግልጽ የሚኾን ይመስለኛል።

“የኢየሱስ ማንነት ተደረሰበት…

“ሚዛኑ ቢጠፋ ወርቁ ጠፋ፣ ሴቶችን የበደለ ክርስቲያን ወይስ ኢስላም”

“ኢየሱስ ነቢይ ወይስ ፈጣሪ”

“ቁርዐንን ማን ደረሰው”

“የኢየሱስ ማንነት ለእስላሞች መልስ”

የመርካቶ የአንዋር መስጊድ እና የደብረ ኀይል ቅዱሰ ራጉዔል ቤተ ክርስቲያን ፍጥጫ፣ ፍቅር እና ተቃርኖ የመላ አገሪቱን ስሜት አይወክልም ለማለት ያዳግታል፡፡ እየቀጨጨ ያለ አብሮነት፣ እየጎመራ የሚመስል የሌላውን የማንኳሰስ አባዜ፣ የእኔን ብቻ ስሙኝ የሚለው ውትወታ፣ ጠበብ ያለ ሃይማኖታዊ አቋም ወዘተ …፡፡

በቅርቡ የ“ሚሊቴሪ ተራ” ነጋዴዎች አክሲዮን ማኅበር አባላቱን በራጉዔል ቤተ ክርስቲያን አዳራሽ ስብሰባ ይጠራቸዋል፡፡ በሚያስገነቡት ሕንፃ ጉዳይ ላይ እንዲመክሩ፡፡ አንዳንድ የማኅበሩ አባላት ታድያ ሙስሊሞች በመኾናቸው የሙስሊም ቆባቸውን አድርገው ወደ ስብሰባው ይገባሉ። ሰብሳቢዎቹም ያሉት ቤተ ክርስቲያን ቅጽር በመኾኑ ቆባቸውን እንዲያወልቁ ይጠይቃሉ። ሙስሊም አባላትም “ይህን ካወቃችኹ ለምን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሰበሰባችሁን?” በሚል ስብሰባውን ረግጠው ይወጣሉ። አንዳንዶችም ለፀብ ይጋበዛሉ። እንዴት መታገስ ተሳናቸው?

ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ ሃይማኖታዊ ፉክክሩ እና ትንኮሳው የመንግሥትን ጣልቃ ገብነት ጭምር የጠየቀ ነበር። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደኅንነት አማካሪ አቶ አባይ ፀሐዬ ትኩሳቶችን ለማርገብ ላይ ታች ባዝነዋል።  የሁለቱም እምነት ተከታዮች በሃይማኖታዊ ክብረ-በዐሎቻቸው ላይ ተከታዮቻቸውን ሆ- ብለው አደባባይ እንዲወጡ በማባበል እግረ መንገዳቸውን ጡንቻቸውን ለማሳየት ተጠቅመውበታል። አንዳንዴ ከሃይማኖታቸው መሠረታዊ አስተምህሮዎች ጭምር በሚጣረስ መልኩ አስጸያፊ ቃላት ጨዋ በሚመስል መንገድ ተለዋውጠዋል፡፡ የክሩሴድ ጦርነት ክተት የታወጀ እስኪመስል ዛቻን ያዘሉ ጽሑፎችን በአልባሳት እያተሙ ለአደባባይ አብቅተዋል። ይህች ደሴት እኔ ከምከተለው ሃይማኖት ሌላ ለማስተናገድ ቦታ የላትም ሲሉም ያወጁ ነበሩ። ይህን መሰሉን ነገር ስመለከት አብሮነታችን በቋፍ ያለ መስሎ ይሰማኛ፤ እንዲህም አስባለኹ፡፡ ብዙ የተባለለት የ‹‹ሼ-መንደፈር›› ታሪካችን ታሪክ ብቻ ሊኾን ይችላል። አላህ እና እግዚአብሔር ካልታደጉት በቀር።

24 Responses to “ሼ-መንደፈር በመርካቶ”

  1. Zemenew Woubalem 1 September 2010 at 12:51 am

    the link for Dereje Haile’s news is mistakenly connected to Googlenewspaper. Please, fix it. Otherwise, it is a superb online media!
    Keep it up!
    -

Leave a Reply

You must be to post a comment.

“አያዋጣም” የሚል የሙዚቃ አልበም ለገበያ ቀረበ

This post is available in: ኸንግሊስህባለፈው ሐሙስ ነሐሴ 6 ቀን 2002 ዓ.ም ድምጻዊት ማኅሌት ደመረ “አያዋጣም የሚለውን የመጀመርያ አልበሟን በሐረር መሶብ ባር እና ሬስቶራንት አስመረቀች። ይህ አልበም የመጀመሪያ ሥራዋ ሲኾን በግጥም እና ዜማው አበበ ብርሃኔ፣ ሱራፌል አበበ፣ ብሥራት ጋረደው እና መላኩ ጥላሁን ተሳትፈውበታል፡፡ መሐመድ ኑር ሁሴን እና ካሙዙ ቅንብሩን ሰርተውታል፡፡ ሚክሲንጉን ክብረት ዘኪዎስ እንደሠራው ለማወቅ [...]

This post is available in: ኸንግሊስህ

ባለፈው ሐሙስ ነሐሴ 6 ቀን 2002 ዓ.ም ድምጻዊት ማኅሌት ደመረ “አያዋጣም የሚለውን የመጀመርያ አልበሟን በሐረር መሶብ ባር እና ሬስቶራንት አስመረቀች። ይህ አልበም የመጀመሪያ ሥራዋ ሲኾን በግጥም እና ዜማው አበበ ብርሃኔ፣ ሱራፌል አበበ፣ ብሥራት ጋረደው እና መላኩ ጥላሁን ተሳትፈውበታል፡፡ መሐመድ ኑር ሁሴን እና ካሙዙ ቅንብሩን ሰርተውታል፡፡ ሚክሲንጉን ክብረት ዘኪዎስ እንደሠራው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ኢንዱ ኢንቴርቴይመንትም አልበሙን በማከፋፈል ላይ ይገኛል። ይህ ባለፉት ጊዜያት በኢትዮጵያ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ ቀዝቅዞ እና ጠፍቶ የነበረውን የአልበም ማሳተም ሥራ የሚያነቃቃ የመጀመርያው ኅትመት እንደኾነም ታውቋል። ከዚህ በተጨማሪም አዲስ አባባ በየቦታው በባህላዊ እና በዘመናዊ የሙዚቃ አልበም ፖስተሮች እየተሞላች እንደኾነም ታውቋል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

የአዲስ አበባ አዳዲስ ፊልሞች “ሥሥት” እና “ይሉኝታ”

This post is available in: ኸንግሊስህ“ሥሥት”  የተሰኘው የአብነት አጎናፍር ፊልም ተመረቀ “ድብቅ ውበት” እና “ውለታ” በተሰኙት ተወዳጅ የሙዚቃ አልበሞቹ በሚታወቀው አርቲስት አብነት አጎናፍር ተደርሶ ፕሮውዲውስ የተደረገው እና ፍጹም ካሳሁን ያዘጋጀው “ስስት” የተሰኘ ልብ አንጠልጣይ የቤተሰብ ፊልም  ትላንት ነሐሴ 9 ቀን /2002 ዓ.ም በ11፡30 በሐርመኒ ሆቴል ተመረቀ፡፡ ፊልሙ በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሠረተ ሲኾን ከ30 በላይ ተዋንያን [...]

This post is available in: ኸንግሊስህ

“ሥሥት”  የተሰኘው የአብነት አጎናፍር ፊልም ተመረቀ

“ድብቅ ውበት” እና “ውለታ” በተሰኙት ተወዳጅ የሙዚቃ አልበሞቹ በሚታወቀው አርቲስት አብነት አጎናፍር ተደርሶ ፕሮውዲውስ የተደረገው እና ፍጹም ካሳሁን ያዘጋጀው “ስስት” የተሰኘ ልብ አንጠልጣይ የቤተሰብ ፊልም  ትላንት ነሐሴ 9 ቀን /2002 ዓ.ም በ11፡30 በሐርመኒ ሆቴል ተመረቀ፡፡ ፊልሙ በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሠረተ ሲኾን ከ30 በላይ ተዋንያን ተሳትፈውበታል፡፡

አብነት “ልርሳህ ልጄ” እያለ በዘፈነው ዘፈን ታሪክ ላይ ባጠነጠነው በዚህ ፊልም ላይ ዮሐንስ ተፈራ፣ ማክዳ አፈወርቅ፣ ዳዊት አባተ እንዲሁም ትነበብ ተረፈ ተውነውበታል። ከኤቢ የፊልምና የሙዚቃ ፕሮዳክሽን ባገኘነው መረጃ መሠረት አዘጋጆቹ ለፊልሙ ከ200 ሺሕ ብር በላይ እንዳወጡበት ገልጸዋል፡፡ ፊልሙ 1፡50 ሰዓት ርዝመት አለው፡፡ አብነት አጎናፍር እና ፍጹም ካሳሁን ከዚህ ቀደም “አላዳንኩሽም” የተሰኘ ፊልም ለሕዝብ ማቅረባቸው ይታወቃል፡፡

“ይሉኝታ” የተሰኘ ፊልም  ማክሰኞ ዕለት ይመረቃል

“የሞርያም ምድር” የተሰኘውን ፊልም ፕሮዲዩስ ያደረገው ሩት ፊልም ፕሮዳክሽን “ይሉኝታ” የተሰኘውን የሚሊዮን ዓለሙን አዲስ ፊልም ማክሰኞ ነሐሴ 11 ቀን 2002 ዓ.ም በብሔራዊ ቲአትር በ 11፡00 ሰዓት ላይ ያስመርቃል፡፡ የፊልሙ ድርሰት የቢኒያም ወርቁና የደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ሲኾን እመቤት ወ/ገብርኤል፣ ሜሮን ጌትነት፣ ግሩም ኤርሚያስ፣ ሸዋፈራው ደሳለኝ እንዲሁም ሌሎች ተዋንያን ይሳተፉበታል፡፡

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

አዳዲስ መጽሐፍት በገበያ ላይ

ባለፈው ሳምንት አዳዲስ መጽሐፍት ወደ ገበያ ገብተዋብረል። ስብሀት ገብረ እግዚአብሔር፣ አንዱዓለም አባተ እና እንዳለጌታ ከበደ በአዲስ ሥራ ብቅ ብለዋል።

This post is available in: ኸንግሊስህ

ስብኀት ገብረ እግዚአብሔር የፈረንሳያዊ ውን ደራሲ የሬይሞን ልብ ወለድ ተረጎመ

ደራሲና ጋዜጠኛ ስብኀት ገብረ እግዚአብሔር የታዋቂውን የረይሞን ከኖን  “Zazie Dans Le Metro” የተሰኘ ልብ ወለዱን “ዛዚ” በሚል ርእስ ተርጉሞ በያዝነው ሳምንት ለንባብ አብቅቷል፡፡

የደራሲ ስብኀት የትርጉም ሥራ በ189 ገጾች የተጠናቀረ ሲኾን ዋጋው 34.99 ብር ነው። ይህ መጽሐፍ በገበያ ላይ የዋለው የስንዱ አሳታሚ እና የፈረንሳይ ኤምባሲ ባደረጉት ትብብር ነው። እ.ኤ.አ ከ1903 እስከ 1976 የኖረው ታዋቂው የፈረንሳይ ደራሲ እና ሐያሲ ሬይሞን ከኖ በ1920ዎቹ አጋማሽ “የሱራሊዝም” አቀንቃኝ በሚል ይታወቅ ነበር። በልብ ወልድ ሥራዎቹም በጎዳና ላይ የሚነገሩ ዘዬዎችን በመጠቀምም አዲስ አጻጻፍን ለሥነ ጽሑፍ እንዳበረከተ ይነገርለታል። ሬይሞን አስቂኝ የኾነውን እና በከፍተኛ ኹኔታ ተሻጭ የነበረውን “Zazie Dans Le Metro” የተባለውን መጽሐፍ ለኅትመት ያበቃው እ.ኤ.አ በ1959 ነበር። ስብኀት ይህን መጽሐፍ ከመተርጎሙ በፊት “አምስት ስድስት ሰባት”፣ “ትኩሳት”፣ “ሰባተኛው መልአክ”፣ “ሌቱም አይነጋልኝ” እና “የፍቅር ሻማዎች” የተሰኙት ወጥ ሥራዎችን ያቀረበ ደራሲ ነው። በጋዜጣ ላይ በሚጽፋቸው ጽሑፎች እና በመጽሐፉ ውስጥ በሚያነሳቸው ሐሳቦቹ የብዙ አንባብያንን ቀልብ በመሳብ እና ወሲባዊ ቃላት በመጠቀም ባለው ነጻነት ስብኀት አነጋጋሪ ከኾኑት ደራስያን የመጀመርያው ነው።

የቶልስቶይ “አና ካራኒና” ተተረጎመ

በኢትዮጵያ አንባቢያን ዘንድ ከፍተኛ ክብር የሚሰጠው እና ስመ ጥር የኾነው የሩሲያዊው ደራሲ ሊዮ ቶልስቶይ ብሉይ (classic) ድርሰት የኾነው “አና ካራኒና” የተሰኘው ረጅም ልቦለድ በተመሳሳይ ርእስ በነጻ ትርጉም በወጋየሁ በለው ወደ አማርኛ ተተርጉሞ በዚህ ሳምንት ለንባብ በቅቷል፡፡ 549 ገጾች ያሉት የዚህ መጽሐፍ ትርጉም ፈታኝ እና ረጅም ጊዜ የወሰደ እንደ ነበር የማኅሌት አሳታሚ ሥራ አስኪያጅ እና ባለቤት የኾኑት አቶ አቤል ሰይፈ ለአዲስ ነገር ገልጸዋል፡፡ የዚህ መጽሐፍ ዋጋ በ50 ብር ነው፡፡

ሁለት አዳዲስ መጻሕፍት ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ተሽጠው አለቁ

በትኩእ ባህታ የተጻፈው “መለስ ከልጅነት እስከ ሕይወት” የሚለው በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሕይወት ዙሪያ የሚያጠነጥነው መጽሐፍ 5000 ኮፒ በሁለት ቀናት ውስጥ ተሽጦ ማለቁን አከፋፋዮች ገለጹ፡፡  በዚህ መጽሐፍ ትኩእ ባህታ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያየ ጊዜ ለተለያዩ የኅትመት እና የኤሌክትሮኒክ ሚዲያዎች የሰጧቸውን ቃለ ምልልሶች መርጦ እና ቅደም ተከተልን በጠበቀ ኹኔታ አጠናቅሮ የጻፈው ነው። የጠቅላይ ሚኒስትር መለስን የሕይወት ታሪክ የሚተነትነው መጽሐፍ በዚህ ሳምንት 5000 ሺሕ ኮፒ ከመጠናቀቁ ባሻገር በሕዝቅያስ ፀጋዬ የተደረሰው እና “ያልተፈታው ህልም” የተሰኘው ልቦለድ መጽሐፍም ለንባብ በቀረበ በሳምንት ጊዜ ውስጥ ለመጀመሪያ ዕትም ያቀረበውን 5000 ኮፒ እንደጨረሰ አሳታሚው አቶ ፋሲካ ግዛው ለአዲስ ነገር ገልጿል።

ይኸው 263 ገጾች ያሉት የሕዝቅያስ መጽሐፍ መነሻውን ኤርትራ ባድመን በወረረችበት ጊዜ ላይ አንተርሶ ይጀምራል።  ደራሲው በሕይወት ያሉ ሰዎችን ስም ሳይቀይር በመጽሐፉ ውስጥ የተጠቀመ ሲኾን በመጽሐፉ መግቢያ ላይ ግን በራሱ ፈጠራ አመለካከቱን እንደሚያራምድ አድርጎ አስቀምጧል። በመጽሐፉ ላይ በተጠቀሱት ከባድ ምስጢሮች አማካኝነት ሊደርስበት የሚችል ምንም ነገር ቢኖር ሐላፊነቱን ሙሉ ለሙሉ እንደሚወስድም በዚሁ መግቢያ ላይ ገልጿል።

እንዳለ ጌታ ከበደ አዲስ መጽሐፍ ይዞ ብቅ አለ

ጋዜጠኛ እና ደራሲ እንዳለ ጌታ ከበደ በዚህ ሳምንት “ደርሶ መልስ” የሚል አዲስ የረጅም ልቦለድ ሥራውን ይዞ ወደ ገበያው ተቀላቅሏል። የእንዳለ ጌታ አዲሱ “ደርሶ መልስ” የተሰኘው ባለ 248 ገጽ መጽሐፍ ከዚህ በፊት ለአንባብያን ካቀረባቸው ልብ ወለዶች የሚለይበት የራሱ የኾነ የአጻጻፍ ቴክኒክ አለው። እንዳለ በዚህ መጽሐፉ ከዋናው ባለታሪክ ሞያ እና ከየምዕራፎቹ መንፈስ ጋራ ቀጥተኛ ተያያዥነት ያላቸው የአንጋፋ ድምጻውያን የሙዚቃ ሥራዎችን ዜማ በኖታ አስቀምጧል፡፡ የዚሁ መጽሐፍ ዋጋ 26 ብር ሲኾን ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ “ከጥቁር ሰማይ ሥር”፣ “ዛጎል”፣ “ልብ ሲበርደው”፣ “የመኝታ ቤት ምስጢሮች”፣ እንዲሁም “ኬርሻዶ” የተሰኙ መጻሕፍትን ለንባብ አብቅቶ ነበር። እንዳለ ጌታ ከበደ በአጭር ዓመታት ውስጥ በተከታታይ መጻሕፍት በማሳተም ለአንባቢው አስተዋጽዖ እያበረከተ ያለ ወጣት ደራሲ ነው።

“ሦስቱ ትዝታዎች” የሚል መጽሐፍ በገበያ ላይ ዋለ

አንዱዓለም አባተ( ያፀደ ልጅ) “ሦስቱ ትዝታዎች” በሚል አዲስ መጽሐፍ ለንባብ አበቃ። “ሦስቱ ትዝታዎች” የተሰኘው ይኸው መጽሐፍ የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ ነው። ይኸው መጽሐፍ የሚሸጠው 16 ብር ነው።፡ ደራሲው ከዚህ ቀደም “የረዘመ ትንፋሽ” በሚለው የግጥም መጽሐፉ፣ “ሞት በቀጠሮ” እና “ረጃጅም ጥላ” በተሰኙ ቲያትሮቹ ይታወቃል፡፡ አንዱዓለም የፖፑሌሽን ሚዲያ ሴንተር ባሳተማቸው “ወንዞች እስኪሞሉ”፣ “የማለዳ ሸክም” እና “ውርስ” የተሰኙ አጭር ልብ ወለዶችን ለአንባቢ አበርክቷል፡፡

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር የአራት አንጋፋ ደራስያንን የመታሰቢያ የፖስታ ቴምብር አስመረቀ

50ኛ ዓመት የወርቅ እዮቤልዩ ክብረ በዐሉን ተከትሎ የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር ከኢትዮጵያ ፖስታ አገልገፍሎት ድርጅት ጋራ በመተባበር በኣራት አንጋፋ ደራስያን ምስል ያሳተመው የፖስታ ቴምብር ዛሬ ሐምሌ 30 ቀን 2002 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ በይፋ ተመረቆ ለገበያ ቀረበ። የመታሰቢያ የፖስታ ቴምብሩ በምስላቸው የተዘጋጀላቸው ደራስያን ክቡር ከበደ ሚካኤል፣ ክብርት ወ/ሮ ስንዱ ገብሩ፣ ክቡር ሀዲስ ዓለማየሁ እና ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድኅን ናቸው።

This post is available in: ኸንግሊስህ

50ኛ ዓመት የወርቅ እዮቤልዩ ክብረ በዐሉን ተከትሎ የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር ከኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት ጋራ በመተባበር በኣራት አንጋፋ ደራስያን ምስል ያሳተመው የፖስታ ቴምብር ዛሬ ሐምሌ 30 ቀን 2002 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ በይፋ ተመረቆ ለገበያ ቀረበ።

የመታሰቢያ የፖስታ ቴምብሩ በምስላቸው የተዘጋጀላቸው ደራስያን ክቡር ከበደ ሚካኤል፣ ክብርት ወ/ሮ ስንዱ ገብሩ፣ ክቡር ሀዲስ ዓለማየሁ እና ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድኅን ናቸው። የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር ፕሬዝዳንት የኾኑት አቶ ጌታቸው በለጠ የመታሰቢያ ቴምብሮች ታትመው ዛሬ ተመርቀው በይፋ ለገበያ እስከቀረቡበት ጊዜ ድረስ ሂደቱ ከሦስት ዓመታት በላይ እንደወሰደ በመግለጽ ለስኬቱ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት ፕሬዝዳንት የኾኑትን አቶ ግደይ ገብረ ዮሐንስን እና ርሆቦት ማተሚያ ቤትን አመስግነዋል።

አቶ ጌታቸው በለጠ አያይዘውም “ታኅሳስ ወር መጨረሻ ላይ የአፍሪካ ደራስያን ማኅበር ሲምፖዚየምን በአዲስ አበባ ለማዘጋጀት እንቅስቃሴ ጀምረናል። የአራቱ ደራስያን የመታሰቢያ ቴምብር መታተም በራሱ ጅምር እንጂ ግብ አይደለም። ደራስያኑ ለአገር ባበረከቱት ድርሰቶቻቸው እና ከእነርሱ በኋላ ለተፈጠሩት በርካታ ደራስያን እና ደራስያት አርአያ ስለኾኑ ቴምብር ታትሞላቸዋል።” ብለዋል።

በፕሮግራሙ ላይ የክቡር ከበደ ሚካኤል፣ የክብርት ስንዱ ገብሩ፣ የክቡር ሀዲስ ዓለማየሁ እና የሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድኅን አጭር የሕይወት ታሪክ ተቀንጭቦ እንዲሁም የግጥም እና የልብወለድ ሥራዎቻቸው ጭምር በጋዜጠኛ ጌጡ ተመሰገን፣ በኢየሩሳሌም ነጋ ፣ በተዋናይ ፍቃዱ ተክለማርያም፣ በደራሲ እንዳለ ጌታ ከበደ እና በደራሲ አበረ አዳሙ ተነቧል።

በፕሮግራሙ ላይ የባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር አምባሳደር ሙሐሙድ ድሪር፣ ሚኒስትር ዴኤታው ማሕሙድ አሕመድ ጋአስ፣ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ እንዲሁም የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት እንድርያስ እሸቴ በክብር እንግድነት በቦታው ላይ ተገኝተዋል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

“የኤርትራ መዘዝ” ወይስ ዜና መዋዕል?

የመጽሐፉን አብዛኛውን ክፍል የያዙት “ነገረ ደርግ” እና “የሰሜን አካባቢ ችግሮች” የሚሉት ሁለት ክፍሎች ናቸው። በእነዚህም የመጽሐፉ አስኳል የኾኑ ክፍሎች ያለፈው መንግሥት ሥልጣን የያዘበትን ሁኔታ በጥቂቱ ከዳሰሱ በኋላ የኤርትራን ጦርነት የሚገልጹትን ታሪኮች አሳይተዋል። የጦርነት ታሪኮቹን ሲተርኩም የግብረ ኀይል፣ የቀይ ኮከብ ሁለገብ አብዮታዊ ዘመቻን፣ “ድብቁ” ዘመቻ፣ የቀይባሕርን እና የባሕረ ነጋሽን ዘመቻዎች ከዕቅዳቸው ጀምሮ ውጤታቸውን እና የውጤታቸውን ግምገማዎች ግልጽ በኾነ ቋንቋ አቅርበዋል።

This post is available in: ኸንግሊስህ

“ሊቀመንበሩ (መንግሥቱ ኀይለማርያም) አንዳንድ ጊዜ ስሜታዊ በመኾን አላስፈላጊ ንግግሮችን ያደርጉ ነበር። በተለይ በናደው እዝ ተገኝተው የ3ኛ ክፍለጦርን ሠራዊት በሚያነጋግሩበት ወቅት በጣም ስሜታዊ ነበሩ። ሊቀመንበሩ 3ኛ ክፍለጦር ውስጥ ያገለገሉ በመኾናቸው እና ለዚህ ደረጃ ያበቃኝም ይኸው ክፍል ነው ብለው በማመናቸው እንደኾነ የብዙዎች ግምት ነው። ከንግግራቸው መሃል አንዱን ለመግለጽ ያህል፣ ‘ለዚህ ሠራዊት ላደርግ የምችለው ምንም ነገር ስለሌለ አዛዣችሁን ኮሎኔል ውበቱ ጸጋዬን የብርጋዲየር ጄኔራልነት ማእረግ ሰጥቼዋለሁ’ ብለዋል።”

ይህን የመሰሉ በርካታ ትዝታዎችን የያዘችው የኮሎኔል አምሳሉ ገብረዝጊ ገብሩ መጽሐፍ በቅርቡ በገበያ ላይ ውላለች። በአብዮቱ አፍላ ወቅት ከሐረር ጦር አካዳሚ ተመርቀው በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በመዘዋወር ወታደራዊ ግዳጃቸውን የተወጡት ኮሎኔል አምሳሉ፤ የውትድርናውን ዓለም ትዝታቸውን እና የጦርነት ማግስት ቁዘማቸውን ለአንባብያን እንካችሁ ብለዋል። ይህችኑ 316 ገጾች ያሏትን መጽሐፋቸውን ኮሎኔል አምሳሉ “የኤርትራ መዘዝ” የሚል ርእስ ሰጥተዋታል። በመጽሐፉ ውስጥ የተዳሰሱትም ታሪኮች ርእሱ እንደሚጠቁመው በአብዛኛው ጸሐፊው የተካፈሉባቸውን የኤርትራን ጦርነቶች የሚያስታውሱ ናቸው።

መጽሐፉ በአግባቡ የተደራጁ አራት ክፍሎች እና ጸሐፊው የተማሩበትን የቀዳማዊ ኀይለሥላሴ የጦር አካዳሚን የሚዘክር ረዘም ያለ አባሪ ተካቶበታል። ምንም እንኳን አልፎ አልፎ ጥራታቸው የማይስብ ፎቶግራፎች ቢካተቱባቸውም 13 ገጽ የሚይዙት ፎቶግራፎች ጸሐፊው በሚተርኩት የጦርነት ታሪክ ውስጥ ተዋንያን የነበሩትን ባልደረቦቻቸውን በመልክም እንድናውቃቸው እድልን ሰጥተውናል። የጦርነቶቹ እቅዶች በኤርትራ ምድር ውስጥ ምን ይመስሉ እንደነበረም የሚያሳዩት ካርታዎች መካተታቸው የጸሐፊውን ጥንቃቄ የተሞላ መረጃ አሰጣጥ የሚጠቁሙ የመጽሐፉ አካላት ናቸው። እነኚህ መረጃዎች ካቀረቧቸው የተለያዩ ቃለ ጉባዔ መሰል ትረካዎች እና ሰንጠረዦች ጋር ተዳምረው ጸሐፊው ቁልጭ አድርጎ ለማሳየት ያላቸውን ቁርጠኝነት አሳይተዋል።

“‘ታሪክ ሠሪው ሰፊው ሕዝብ ነው’ ይባላል። ካለፈው ሥርዓት መፈክሮች ውስጥ ዘመን ሊሽረው እና ‘አዲስ አመለካከት’ ሊገስሰው ያልቻለው እውነታ ይህ የታሪክ ቀጥተኛ ባለቤት ሕዝቡ መኾኑን የሚጠቁመው መሪ ቃል አንዱ ነው።” በሚል መነሻ መጽሐፋቸውን የሚከፍቱት ኮሎኔል አምሳሉ፤ አንድን ግለሰብ እንደ ታሪክ ባለቤት ላለመቀበል ይሟገታሉ። የአቋማቸውንም ብርቱነት የራሳቸውን ታሪክ በታሪኩ ውስጥ ላለማስገባት ባደረጉት ክርክር አሳይተዋል። “በመጽሐፌ ውስጥ የግለሰቦች የበላይነት እንዳይኖር የጣርኩበት አግባብ ተፈጻሚነቱ በሌሎች ላይ ብቻ አይደለም። በእኔ በመጽሐፉ አዘጋጅም ላይ ተተግባሪ ኾኗል። ” የሚሉት ኮሎኔል በአሳታሚ ድርጅቱ አርታኢዎች “ግፊት” ካስገቡት “ጥቂት ስለደራሲው” የምትል አጭር መቅድም በቀር ስለእርሳቸው እንድናውቅ የፈቀዱልን አንድ ነገር ብቻ ነው። በጦርነቱ ተሳታፊ መኾናቸውን። ይህም የተገኙባቸውን የጦር ዕቅድ እና የግምገማ ስብሰባዎች የሚያጠቃልል ነው። በመኾኑም ደራሲው እስከ ዛሬ ከነበሩት ግለታሪክን የሚያካትቱ የጦር ሜዳው ዘገባዎች በተለየ በጦርነቱ ላይ ብቻ ያተኮሩ ዘገባዎች ለአንባብያን አቅርበዋል።

በመጽሐፉ የመጀመሪያ ክፍል ትኩረታቸውን ያደረጉበትን የኤርትራን ጦርነት መነሻ ለመዳሰስ ሞክረዋል። በዚህ ክፍል ባካተቷቸውም ሦስት ምዕራፎች የኤርትራን ታሪክ እና በኤርትራ የተፈጠሩትን ተገንጣይ ቡድኖች አጀማመር ዳሰዋል። ለዚህም ታሪክ ዘገባቸው የተለያዩ የታሪክ መዛግብትን እና በታሪኩ ተካፋይ የኾኑ ሰዎችን ቃለመጠይቅ እንደተጠቀሙ ይናገራሉ። ያካተቷቸውም መረጃዎች ይህንን ይጠቁማሉ። ለዚህም ማሳያ የሚኾነው ሻዕቢያ ዓላማዬን አደናቅፈዋል ብሎ የገደላቸውን የኤርትራ ተወላጆች ያወሱበት ክፍል ነው። እንደ ጸሐፊው ዘገባ አሁን በኤርትራ ያለው አመለካከት ገዢ የኾነበት ምክንያት የተፈጠረው አዲስ ታሪክ ሁሉንም በማሳመኑ ብቻ ሳይኾን በተቃራኒው የቆሙትን የኤርትራ ተወላጆች በመጨረስ እንደኾነ ማስረጃ አቅርበዋል። ከማስረጃዎቻቸውም መካከል በሻዕቢያ የተገደሉትን 9 የሚኾኑ ግለሰቦች አጭር የሕይወት ታሪክ ያቀረቡበት ክፍል ይገኛል።

የመጽሐፉን አብዛኛውን ክፍል የያዙት “ነገረ ደርግ” እና “የሰሜን አካባቢ ችግሮች” የሚሉት ሁለት ክፍሎች ናቸው። በእነዚህም የመጽሐፉ አስኳል የኾኑ ክፍሎች ያለፈው መንግሥት ሥልጣን የያዘበትን ሁኔታ በጥቂቱ ከዳሰሱ በኋላ የኤርትራን ጦርነት የሚገልጹትን ታሪኮች አሳይተዋል። የጦርነት ታሪኮቹን ሲተርኩም የግብረ ኀይል፣ የቀይ ኮከብ ሁለገብ አብዮታዊ ዘመቻን፣ “ድብቁ” ዘመቻ፣ የቀይባሕርን እና የባሕረ ነጋሽን ዘመቻዎች ከዕቅዳቸው ጀምሮ ውጤታቸውን እና የውጤታቸውን ግምገማዎች ግልጽ በኾነ ቋንቋ አቅርበዋል።

በዘመቻ ዕቅድም ኾነ በሌሎቹ ስብሰባዎች ላይ የነበረውን ኹኔታም ሲያስረዱ የስብሰባዎቹን ሙሉ ኹኔታ ለመግለጽ ይሞክራሉ። የተሰብሳቢዎቹ ስም ከነ ማዕርጋቸው፣ በስብሰባው ላይ የቀረቡ የቀኝ እና የግራ ክርክሮች እና የየስብሰባዎቹ ውሳኔዎች ልቅም ተደርገው ተጽፈዋል። ጸሐፊው በወቅቱ የወሰዱትን ማስታወሻ እንደተጠቀሙ የሚጠቁም የቃለ ጉባዔነት ባህርይ ያለውም መረጃ ይበዛዋል።

ከስብሰባ ዘገባዎቻቸው አንዱ ይህን ይመስላል፤
“… በዚህ ስብሰባ ስለውጊያ ዝግጅት ተነስቶ ምክክር ሲደረግ ብርጋዲየር ጄኔራል አበራ አበበ ጦሩ በቂ ዝግጅት አለማድረጉን እና ውጊያው መዘግየት እንዳለበት ሐሳብ ሲያቀርቡ ሁለት የተራራ ክፍለ ጦር አዛዦች ግን ጦሩ ዝግጁ እንደኾነ እና ጦርነቱ በአስቸኳይ መጀመር እንዳለበት ሐሳባቸውን ገለጹ። ከእነዚህ አንዱ የ21ኛው ተራራ ክፍለ ጦር አዛዥ የነበሩት ኮሎኔል ውብሸት ማሞ ናቸው። ኮሎኔሉ በኋላ ላይ ለዚህ ዘመቻ ውድቀት ተጠያቂ ናቸው ተብለው ተገድለዋል። የብርጋዲየር ጄኔራል አበራ አበበ ሐሳብ ትክክለኛ እንደነበረ በኋላ በገሃድ ታይቷል።”

በየጦርነቶቹም የተገኙትን ድሎችም ኾኑ ሽንፈቶች በተለያዩ መረጃ የሌላቸው ምክንያቶች ከማሳበብ ይልቅ። በወቅቱ በተፈጠሩት ስልታዊ ብቃቶች ወይም ስህተቶች ምክንያት ብቻ አድርገው ይወስዱታል። በሌሎች የጦርሜዳ ዘገባዎች ላይ የምናያቸው በገንዘብም ይሁን በሌላ ምክንያት ለሻዕቢያ ይሰልልሉ ነበር የሚባሉ ባለስልጣናት ክስ በዚህ መጽሐፍ ስፍራ አልተሰጠውም። እንዲያውም ይቃወሙታል።

“…ይኹን እና ‘ከሻዕቢያ እና ከወያኔ ገንዘብ እየተቀበሉ ጦሩን ያስመቱ ነበር’ ሲባል እጅግ ይሰቀጥጣል። ለማመንም ያስቸግረኛል። አንዳንድ ጄኔራል መኮንኖች የአመራር ችግር ሊኖርባቸው ይችላል። ይህ የአመራር ችግር ግን ከብቃታቸው፣ ከልምድ ማነስ እና ከፍርሃት የመነጨ ነው።” የሚል መከራከሪያ ያቀርባሉ። በእያንዳንዱም የውጊያ ግንባር የነበረውን ሽንፈት በምን ምክንያት እንደተከሰተ አንድ ሁለት ብለው ምክንያት ያቀርባሉ። በዚህም ኮሎኔሉ የውጊያውን ጠቅላላ ኹኔታ የሚዳስስ ጥናታዊ የኾነ ጽሑፍ የማቅረብን ያህል መረጃን ለመተንተን ያደረጉት ጥረት አስደናቂ ነው።

ስለ ብዙ ጉዳዮች ያቀረቧቸውም ዘገባዎች ዝርዝር መረጃዎች ይበዙባቸዋል። በወቅቱ በነበረው ጦር ሠራዊት ውስጥ በኃላፊነት ያገለግሉ የነበሩ ሰዎችን ሁሉ በታሪኩ ውስጥ ያደረጉትን ነገር ከመጥቀስ አልፈው ዝርዝር የሕይወት ታሪካቸውን ይሰጡናል። የተወለዱበትን ሥፍራ፣ የተማሩበትን ትምህርት ቤት እና ያገለገሉባቸውን ቦታዎች አንዳንድ ጊዜም እስከ አሟሟታቸው ዝርዝር ሁኔታ ያስታውሷቸዋል። ይህም ጸሐፊውን እንድናደንቅ ብቻ ሳይኾን የያኔውን ጦር ሠራዊት ምንነት እንድናውቅ ቀላል የማይባል መረጃን ይሰጠናል።

ጸሐፊው ግልጽ መረጃን ለአንባብያን ለመስጠት ያደረጉት ጥረት በመጽሐፉ ይዘት የተገለጠ ነገር ነው። የቋንቋ አጠቃቀማቸው እና የፊደል ግድፈቶች እንኳን እንዳይገኙበት ለማድረግ ያደረጉት ትግል መጽሐፉ በቀላሉ እንዲነበብ አድርጎታል። ለሚያቀርቡዐቸውም ታሪኮች ከመላ ምት ይልቅ እውነታ ላይ የተመሠረቱ ጉዳዮችን በመተንተን ለማስረዳት ያደረጉት ጥረት ጸሐፊው የጦር ባለሙያ ብቻ ሳይኾኑ የአካዳሚ ጥናት የማድረግ ብቃታቸውን የሚያሳይ ነው። በመኾኑም መጽሐፋቸው ኤርትራ ውስጥ ተካሂዶ ስለነበረው ረጅም የጦርነት ታሪክ አስፈላጊ የኾነ መረጃን መያዙ አያጠያይቅም።

በመጽሐፉ የታዩት ድክመቶች ጸሐፊው የቀረቡትን መረጃዎች ምንጭ በአግባቡ አለማስቀመጣቸው ነው። የጽሁፍም ኾኑ የቃለ መጠይቅ መረጃዎቻቸው ለአንባብያን ግልጽ ቢኾኑ የመጽሐፉን ጥቅም እጅግ ሊያጎለብቱት ይችሉ ነበር። የመጽሐፉ ርዕስ “የኤርትራ መዘዝ” መባሉ ምክንያቱ ግልጽ አይደለም። ምክንያቱም በመጽሐፉ የተገለጸው ጉዳይ መዘዙ ላይ ያተኮረ ሳይኾን በጦርነቱ ሒደት፣ ውጤቱ፣ እና ምክንያቶቹ ላይ ያተኮረ በመኾኑ ነው። ለመጽሐፉ ክፍሎች ደራሲው የሰጧቸውን ስያሜዎች ስንመለከት ጸሐፊው ርዕስ የመስጠት ችግር አይታይባቸውም፤ “ነገረ ኤርትራ”፣ “ነገረ ደርግ”፣ “ከጦር ሜዳ ባሻገር” ዓይነት ውበት ያለው እና ምክንያታዊ የኾነ አገላለጽ በዋናው ርዕስ ላይ አልታየም።

በመጽሐፋቸው መግቢያ ላይ በመጽሐፋቸው እንደሚዳስሱት የነገሩንን እና ያልጻፉትን ጉዳይ ቢያካትቱበት ኖሮ ርዕሱ ምክንያታዊ ሊኾን እንደሚችል ግን ግልጽ ነው። “በሁለቱ ወንድማማች ሕዝቦች መካከል ተዳፍኖ አንድ ቀን ሊቀሰቀስ ስለሚችለው ጥፋት ትኩረት ሰጥቼ የራሴን መፍትሔ ለመስጠት እሞክራሁ።” የሚለውን ቃላቸውን አላከበሩም።
ያም ኾኖ የኮሎኔል አምሳሉ መጽሐፍ ያለፈውን የጦርነት ታሪክ ለማስታወስ ለሚፈልጉ ሁሉ ጠቃሚ መረጃዎችን በመያዟ ወቅቱን በተመለከተ ጥናት የሚያደርጉ ሁሉ የግድ ሊያነቧት የምትገባ መጽሐፍ ናት።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

ሐውልቱ፤ ባለሐውልቱ እና ሐውልተኞቹ- የድቀቱ ምስክሮች

ቤተ ክርስቲያኒቱ ካለችበት ቀውስ አንጻር አሁን የሚያስፈልጋት ጥልቅ ራስን የምር የመፈተን ቁርጠኝነት ነው። የቤተ ክርስቲያኒቱን መሠረታዊ አስተምህሮዎች፣ ትውፊት እና ታሪክ ግምት ውስጥ ያስገባ የመንፈሳዊ እና ተቋማዊ ለውጥ አብዮት/ተሐድሶ ሊያመጣ የሚችል ራስን የመፈተሽ ተጋድሎ ይጠብቃታል። ሐውልት የሚቆምለት ተጋድሎም እርሱ ይሆናል። ይህ የለውጥ አብዮት ከየት ይነሣል፣ እነማን ያሥነሱታል፣ እንዴትና እንደ ምን ተጀምሮ በምን ይጠቃለል ይሆን? የሚሉት ጥያቄዎች ቀላል መልስ የላቸውም።

እስከዚያው ግን ቢያንስ ለድቀቱ ማስታወሻ ይሆን ዘንድ ለአባ ጳውሎስ የቆመው ሐውልት ባለበት ይቆይ። ባይሆን ከግርጌው የሰፈረውን ጽሑፍ መቀየር ይሻላል። “ወደ መንበሩ ከመጡ ጀምሮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የገባችበት መንፈሳዊ እና ተቋማዊ ድቀት በየዓመቱ 99.6 በመቶ እንዲያድግ ስላደረጉት መንፈሳዊና ስጋዊ ተጋድሎ ምስክር ይሆን ዘንድ ልጆቻቸው ይህንን ሐውልት አቆሙላቸው።” ሐውልቱን አታፍርሱት።

AbaPaulosStatute

This post is available in: ኸንግሊስህ

በቅርቡ ለአቡነ ጳውሎስ የቆመላቸው ሐውልት ጉዳይ ለብዙዎች የመነጋገሪያ ጉዳይ ሆኗል። አዲስ አበባ በሚገኘው ቦሌ መድኀኔዓለም ቤተ ክርስቲያን የተተከለው ይህ ሐውልት የመጀመሪያ እንጂ የመጨረሻ እንደማይሆንም እየተገለጸ ነው። ይህ የሐውልት ግንባታ ያስከተለው ውዝግብ ግን በመሠረቱ የጉዳዩን ማዕከላዊ ጭብጥ እና መነሻ አድበስብሶ የሚያልፍ ከመሆን የሚታደገው ያገኘ አይመስልም።

በሐውልቱ ዙሪያ የሚነሡትን ክርክሮች ወይም ሐሳቦች በሁለት ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡ አንደኛው በሐውልቱ በራሱ ተፈጥሯዊ ምንነት እና ትርጉም ላይ ያነጣጠረ ነው። ጭብጡም “ሐውልት ምንድን ነው? በቤተ ክርስቲያኒቱ ትምህርት እና ትውፊትስ ያለው ቦታ ምንድን ነው? እንኳን መንፈሳዊ ውጊያውን ላልጨረሰ በሕይወት ላለ ሰው ቀርቶ ለሞቱት ቅዱሳንስ ሐውልት ቆሟል ወይ…” የሚሉትን ጥያቄዎች በመመለስ ዙሪያ የሚሽከረከር ነው። በአመዛኙ ይህ ክርክር በግልብ-ምሁራዊነት (ሱዶ ኢንተለክቹዋሊዝም) የተጣበበ ነው። በዚህም ምክንያት ክርክሩ ጎጂ ባይሆንም አንዳችም ምሁራዊ ጥልቀት የሌለው አንዱን አቋም ደግፎ ሌላውን የሚቃወም ጥቅስ እና ታሪክ/ምሳሌ የማግኘት ፉክክር ከመሆን አልዘለለም።

ሁለተኛው የክርክር ዘርፍ በሐውልቱ ትእምርታዊ (ሲምቦሊክ) ትርጉም ላይ ያነጣጠረ ነው። ይህ ምልከታ በአብዛኛው “ውጫዊ” በተለይም ፖለቲካዊ እና ብሔረሰባዊ ፍላጎቶች የሚጫነው ነው። እንደዚያም ሆኖ የሐውልቱን ውዝግብ ከጥቅስ እና ከትውፊት ክርክር አስፍቶ በመመልከት አገራዊ እና ማኅበረሰባዊ ገጽታ ለመስጠት በመሞከር የተሻለ ነው። ሆኖም ዞሮ ዞሮ ማጠንጠኛው አባ ጳውሎስ እና ጀሌዎቻቸው ብቻ ስለሆኑ የክርክሩ መጨረሻ እየጠበበ ሄዶ የአንድ ግለሰብ ጉዳይ ይሆናል። ሁለቱም ክርክሮች ድርጊቱ ከትምህርት፣ ከትውፊት እና ከፍ ሲልም ከባህላዊ ወግ አንጻር ተገቢ አለመሆኑን በመግለጽ ሐውልቱን፣ ሐውልቱን ያቆሙትን እና ሐውልቱ የቆመላቸውን በጋራ ያወግዛሉ።

ሁለቱም ወገኖች ሐውልቱ ቢፈርስላቸው የክርክራቸውን አጀንዳ ዘግተው ወደ ተለመደው ኑሮ ለመመለስ ብዙ ጊዜ አይፈጅባቸው ይሆናል። ግፋ ቢል ደግሞ ሌላ አባ ጳውሎስ እና በዙሪያቸው የተሰበሰቡት ሰዎች የሚፈጽሟቸውን ነጠላ ድርጊቶች እያነሱ በተመሳሳይ የክርክር እና የውግዘት አዙሪት ይጠመዳሉ። የአቡነ ጳውሎስ ደጋፊዎችም በፊናቸው “ሁሉ ለጳውሎስ፤ ሁሉ በጳውሎስ” በሚለው መርህ ስር ጉዟቸውን ይቀጥላሉ። ላለፉት 18 ዓመታት የታየውም ይህ ነው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በአገሪቱ ታሪክ ውስጥ ከነበራት እና ካላት ሚና (አዎንታዊም አሉታዊም) አንጻር የሐውልም ሆነ ሌላ ውዝግብ ሰፊ ትኩረት ቢስብ የሚገርም አይሆንም። ሆኖም ትኩረቱ በተሳሳተ ኢላማ ላይ ያነጣጠረ ነው እላለሁ። ሁለቱም የአተያይ አቅጣጫዎች አንድም አህያውን ፈርቶ ዳውላውን ናቸው፤ አንድም ደግሞ “ከሐውልቱ” ጀርባ ያለውን አሳፋሪና አስፈሪ ውስጣዊ የቤተ ክርስቲያኒቱ እውነታ ለመጋፈጥ የሚያስችል ብቃት አጥተው የመከኑ ናቸው። ቀሪዎቹ ደግሞ ግላዊ የገንዘብ፣ የዝና፣ የፖለቲካ ወዘተ ፍላጎት ለማሟላት ሰልፉን የተቀላቀሉ ናቸው። ላስረዳ። (በግሌ ሐውልት ማቆም ቢፈቀድም ቢከለከልም ለጊዜው የተለየ ትርጉም አይሰጠኝም።)

1.ሐውልቱን መርምሩት

ላለፉት 18 እና ከዚያም ለሚበልጡ ዘመናት ስለቤተ ክርስቲያኒቱ የሚነሡ ውዝግቦች መሠረታዊውን ችግር እያድበሰበሱ በእንጭፍጫፊ ጉዳዮች ላይ ጉልበት የሚያስጨርሱ ናቸው። የዚህ አንዱ ምክንያት ችግሩን ከምንጩ እና ከምልክቱ ለያይቶ የሚመለከት፤ ከዚያው በመነሣትም መሠረታዊ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል አቀራረብ መጥፋቱ ነው። ቤተ ክርስቲያኒቱን ይመራታል የሚባለው ሲኖዶስም ሆነ እንቆረቆራለን የሚሉት ወገኖች በአብዛኛው እነዚህን ሦስት ነገሮች አምታተው የሚመለከቱ ናቸው። ግራ ተጋብተው ግራ የሚያጋቡ ናቸው። ተቆርቋሪነትን በመግለጽ ብቻ የአደባባይ ምስጋና ከማሰባሰብ አልፈው ችግሩን በሁለንተናዊ መልኩ ለመረዳትም ሆነ ለመፍታት የማይችሉ ሆነው ቆይተዋል።

በሐውልቱ ምሳሌነት ቁም ነገሩን እንመልከተው። በእኔ አስተያየት ለአባ ጳውሎስ ሐውልት መቆሙ የሌላ ጥልቅ በሽታ ምልክት እንጂ ራሱን የቻለ በሽታ አይደለም። ሕይወት ያለው ተቋማዊ እና መንፈሳዊ ሚዛን ቢኖር ኖሮ ቢበዛ በቀላል የሊቃውንት ክርክር ሊያበቃ የሚችል ተራ ጉዳይ በሆነ ነበር። ከሐውልቱ መቆም የበለጠ አሳሳቢ ሊሆን ይገባ የነበረው ሐውልቱን ለመቆም ያስቻሉትና ያነሳሱት መንፈሳዊ፣ ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ምክንያቶች ናቸው። (ምሳሌውን በቀላሉ መቀየር ይቻላል።)

ቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊ/አገራዊ እና አስተዳደራዊ ሐላፊነቷን ሚዛኗን ሳትስት (ጠብቃ) እንድትጓዝ የሚያስችላት ተቋማዊ እና ሕሊናዊ ልጓም ከተሰባበረ ሰንብቷል፤ አለ ከተባለም ያለው በመጻሕፍት፣ በተራ ምእመናን፣ በእውነተኛ መናንያን እና በጥቂት አገልጋዮች ዘንድ ብቻ ነው። ይህ ደግሞ ቤተ ክርስቲያነቱን ከተዘፈቀችበት መንፈሳዊ እና ተቋማዊ ክስረት የማውጣት አቅምም ተልእኮም ሊሸከም የሚችል አካል አይደለም። ማንኛውም ታዛቢ በመጋረጃ ወደሚሸፈነው “ቤተ መቅደስ” እየቀረበ በሔደ መጠን ይህ ቀውስ በሚያስደነግጥ (ማፈር ቀርቷል ብዬ ነው) መጠን እንደሚጨምር መረዳት ይችላል።

ቤተ ክርስቲያኒቱ ለስሙ ተቋማዊ ቅርጽ እንዳላት ከመነገሩ በቀር በሕጉ እና በሥርዓቱ የሚሠራ ነገር ማግኘት እጅግ ከባድ ነው። በዘመናዊ አረዳዱ ካየነው የቤተ ክርስቲያኒቱ ተቋማዊ ሕይወት መሥራት ቀርቶ መተንፈስ ከማይችልበት ደረጃ ደርሷል። ተቋማት ስል አካላዊ ብቻ ሳይሆን ሕሊናዊ/የማይዳሰሱትንም ጭምር ማለቴ ነው። መንግሥት ሁሉንም ተቋማት የእርሱ ተራ አሽከሮች እስኪሆኑ መቆጣጠር እንደሚፈልገው ሁሉ የቤተ ክርስቲያኒቱም “ተቋማት” ወይ በቁም እንዲሞቱ ተደርገዋል አለዚያም በተላላኪዎች ተሞልተዋል።

ብዙ ሰዎች “አባ ጳውሎስ እንዴት የራሳቸውን መንፈሳዊ ተጋድሎ ሐውልት ይመርቃሉ?” ብሎ ሲጠይቅ እሰማለሁ። ግን ከዚህ የባሰ ስንት ነገር መፈጸሙን እያወቅን የሐውልቱ ጉዳይ እንደማሳያ ካልሆነ እንደ ቁልፍ ችግር ባይቀርብ በወደድኩ ነበር። ሰውየው እኮ በቅርቡ “ሰማእት ዘእንበለ ደም” ተብለዋል፤ ይህንንም በምስጋና ተቀብለው ሐውልታቸው ስር ተጽፎላቸዋል። ይልቅ ጽላት በስማቸው ይቀረጽላቸው ሊባል እንደሚችል መጠበቅ የበለጠ ብልህነት ነው።

ስለዚህ የሐውልቱን ጉዳይ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሠረታዊ ችግር አስመስሎ ማቅረብም ሆነ በዚሁ ላይ ጉልበትን መጨረስ ኢላማውን የሳተ ተኩስ ነው እላለሁ። ከዚያ ይልቅ በቤተ ክርስቲያኒቱ አመራር እና በቤተ መቅደሱ ዙሪያ ለዘመናት የተጋገረውን የቀውስ ተራራ በድፍረት መመልከቱ ለቤተ ክርስቲያኒቱም ሆነ ለአገሪቱ ይጠቅማል፤ ራስን ከመዋሸትም ያድናል። የቤተ ክርስቲያኒቱ መሠረታዊ ችግር የመንፈሳዊ እና አስተዳደራዊ ድቀት ነው። ይህ ካልተፈታም ገና ብዙ እናያለን። ሐውልቱን ማናገር፣ ሐውልቱን መመርምር ባለሐውልቱን ከመጠየቅ ይሻላል።

2.ሐውልቱን አፍርሱ

ቀደም ሲል እጅግ በታመቀ መልኩ የገለጽኩት ቤተ ክርስቲያኒቱ የተዘፈቀችበት መንፈሳዊ እና አስተዳደራዊ ውድቀት በተለያየ መልኩ ይገለጻል። በተመሳሳይም የዚህ ውድቀት ምክንያቱ/ምንጩ ብዙ ነው። ስለዚህም የችግሮቹ ሁሉ ምንጭ አባ ጳውሎስ እና የቤተ ዘመድ አመራራቸው ብቻ እንደሆነ ማሰብ የችግሩን እውነተኛ ባህርይ እንዳንረዳው ይጋርደናል።

ከአባ ጳውሎስ ጋራ የግል ችግር ያለባቸውም ሆኑ በፖለቲካዊ አቋማቸው የሚቃረኗቸው ሰዎች እንደሚሉት የቤተ ክርስቲያኒቱ ድቀት ምንጩ አባ ጳውሎስ ብቻ አይደሉም። በተመሳሳይም ኢሕአዴግን/መንግሥትንም ዋናው ተጠያቂ ማድረግ የችግሩን ከፊል ገጽታ ሊጋርድ ይችላል። ችግሩን ሁሉ ወደ አባ ጳውሎስ መወርወር ቢያንስ የቤተ ክርስቲያኒቱን ታሪክና ያለችበትን ሁኔታ አለመረዳት ነው፤ ሲብስ ደግሞ እጅግ ጭፍንነት ነው። በቤተ ክርስቲያኒቱ ጥፋት የራስን ጠባብ አላማ ለማሳካት የመምረጥ ስግብግብነትም ሊሆን ይችላል።

አባ ጳውሎስ የመፍትሔው አካል ይሆናሉ ተብለው ሲጠበቁ (የፕሪንስተን ዶክትሬት ውሃ በላው!) የጥፋቱ ፊታውራሪ ሆነው መገኘታቸው የበለጠ ቢያስወቅሳቸውም ዛሬ የሚታየውን ችግር ሁሉ እርሳቸው ብቻ የፈጠሩት፣ እርሳቸው ብቻ ያጸደቁት፣ እርሳቸው ብቻ የሚፈቱት አስመስሎ ማቅረብ ስሕተት ነው። በአባ ጳውሎስ ላይ የሚሰነዘረው ትችት በሁለንተናዊው ትንተና ውስጥ የሚኖረውን ትክክለኛ ድርሻ በሚገባ አለመረዳት ሰውየው ከመንበራቸው ቢነሡ በአንድ ጀንበር ተአምር የሚፈጠር ያስመስላል። እፍኝ ከማይሞሉት በቀርስ ሌሎቹ ጳጳሳት ከእርሳቸው ይሻሉ ይሆን? ስንተዋወቅ አንተናነቅ።

አሁን ቤተ ክርስቲያኒቱን ተብትበው ያሰሯትና “ሊገድሏት” የሚተናነቁት ችግሮች አባ ጳውሎስ ወደ መንበሩ ከመምጣታቸውም በፊት የነበሩ ናቸው። ከእርሳቸውም በኋላ ይቀጥሉ ይሆናል። ነገር ግን የእርሳቸው አመራር እና ሌሎች ከባቢያዊ ሁኔታዎች (ፖለቲካዊ፣ ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ለውጦች) ችግሮቹን ለማመን በሚያስቸግር መጠን እና ስፋት አባብሰዋቸዋል። አባ ጳውሎስ ቀንደኛ የቀውሱ አካል መሆናቸው የሚያከራክር ባይሆንም ብቸኛው ተጠያቂ ማድረግ ርትእ ይጎድለዋል። ሐውልቱን አፍርሱ የሚለው ጩኸት የመንፈሳዊ እና አስተዳደራዊ ቀውሱን ተራራ እንደማይንደው ጥርጥር የለውም። ቀውሱ ከሐውልቱ ይጠልቃል፤ ይረዝማልም።

3.ሐውልቱን አታፍርሱት

የቤተ ክርስቲያኒቱ ችግሮች ስፋትና ጥልቀት በዚህ አጭር ጽሑፍ ለመዘርዘር የሚቻል አይደለም። ለዓመታት ሲነገር የኖረ በመሆኑም ጉዳዩን ለሚከታተሉ ለብዙዎቹ አንባብያን መድገሙ አስፈላጊ ሆኖ አላገኘሁትም። በአጭሩ ግን ተቋማዊ እና መንፈሳዊ ቀውሶች ብሎ ማጠቃለል ይቻላል። ቀደም ሲል ያነሣኋቸውም ሆኑ ሌሎች በመሠረታዊ ችግሩ ላይ የሚያተኩሩ ሐሳቦች መነሣታቸው ባይቀርም አንዳቸውም ዳር ደርሰው የመፍትሔ ፍንጭ ሲያሳዩ አልታዘብንም።

ከዚህ ይልቅ ግማሹ ችግሩ የሌለ እስኪመስል ድረስ በሌሎች ጉዳዮች ላይ ማተኮርን መርጦ ይታያል። ተስፋ በመቁረጥ እና ያለውን አቅም “ለውጥ ሊያመጣ በሚችል ነገር ላይ ማዋል ይሻላል” ከሚል እምነት ይመስላል። አሳዛኙ ነገር ግን እነዚህ ሰዎች የሚሠሩዋቸው ጠቃሚ ነገሮች (ገዳማትን መርዳት፣ ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋት፣ ቤተ ክርስቲያን ማሳነጽ ወዘተ) ዞሮ ዞሮ የቀውሱ ሰለባ መሆናቸው የማይቀር መሆኑ ነው። ሌሎቹ ደግሞ ቀውሱን ከመካድ የማይተናነስ ድብብቆሽ ይጫወታሉ፤ በአንድ በኩል “ቀውሱ በእዚአብሔር ፈቃድ የተፈጠረ ነው” የሚል መልእክት ያለው ትንተና በማቅረብ ራሳቸውን ከሐላፊነት ያሸሻሉ። ኹኔታውን ለመቀየር ከመጣር ይልቅ ችግሩን ስለመለማመድ ይሰብካሉ።

በሌላ ወገን ደግሞ ነገረ መለኮታዊ ቃና ያለው የሰማዩን ከምድሩ እያደባለቀ ብዥታን የሚያነግሥ ትምህርት ይሰማል። ይህም ዞሮ ዞሮ “አንተ/አንቺ/እኛ ማድረግ የምንችለው ነገር የለም ወይም ጥቂት ነው፤ መፍትሔውም በእኛ እጅ አይደለም” የሚል ነው። መፍትሔው አንድም ከራሳቸው ከችግሩ ፊት አውራሪዎች ወይም ከፈጣሪ ብቻ እንደሚመጣ በመስበክ ምእመኑን ከጨዋታው የሚያስወጣ አደገኛ ወጥመድ ነው። “ቤተ ክርስቲያን ፍጹም ናት” የሚለውን ትምህርት በግርደፉ በማቅረብ ምድራዊውን ችግር ሰማያዊ ጸጋ አስመስሎ ለመሰወር የሚሞክሩም አይጠፉም። ውጤቱን አርቀው ባለመመልከት ይህን መሰሉን ክርክር በቀናነት የሚያቀርቡ ቢኖሩም ያለው ሁኔታ ባለበት እንዲቀጥል የሚፈልጉ የቀውሱ መጋቢዎች ይህንኑ ሐሳብ ሲያቀርቡ መስማት የተለመደ ነው።

ቤተ ክርስቲያኒቱ ካለችበት ቀውስ አንጻር አሁን የሚያስፈልጋት ጥልቅ ራስን የምር የመፈተን ቁርጠኝነት ነው። የቤተ ክርስቲያኒቱን መሠረታዊ አስተምህሮዎች፣ ትውፊት እና ታሪክ ግምት ውስጥ ያስገባ የመንፈሳዊ እና ተቋማዊ ለውጥ አብዮት/ተሐድሶ ሊያመጣ የሚችል ራስን የመፈተሽ ተጋድሎ ይጠብቃታል። ሐውልት የሚቆምለት ተጋድሎም እርሱ ይሆናል። ይህ የለውጥ አብዮት ከየት ይነሣል፣ እነማን ያሥነሱታል፣ እንዴትና እንደ ምን ተጀምሮ በምን ይጠቃለል ይሆን? የሚሉት ጥያቄዎች ቀላል መልስ የላቸውም።

እስከዚያው ግን ቢያንስ ለድቀቱ ማስታወሻ ይሆን ዘንድ ለአባ ጳውሎስ የቆመው ሐውልት ባለበት ይቆይ። ባይሆን ከግርጌው የሰፈረውን ጽሑፍ መቀየር ይሻላል። “ወደ መንበሩ ከመጡ ጀምሮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የገባችበት መንፈሳዊ እና ተቋማዊ ድቀት በየዓመቱ 99.6 በመቶ እንዲያድግ ስላደረጉት መንፈሳዊና ስጋዊ ተጋድሎ ምስክር ይሆን ዘንድ ልጆቻቸው ይህንን ሐውልት አቆሙላቸው።” ሐውልቱን አታፍርሱት።

7 Responses to “ሐውልቱ፤ ባለሐውልቱ እና ሐውልተኞቹ- የድቀቱ ምስክሮች”

  1. Zemenew Woubalem 1 September 2010 at 12:51 am

    the link for Dereje Haile’s news is mistakenly connected to Googlenewspaper. Please, fix it. Otherwise, it is a superb online media!
    Keep it up!
    -

Leave a Reply

You must be to post a comment.

የአሜሪካው ሲኖዶስ ለዕርቁ ሦስት ቅድመ ኹኔታዎችን አስቀመጠ

በአቡነ መርቆርዮስ የሚመራው የአሜሪካው ሲኖዶስ የዕርቅ ሐሳቡን በመጀመርያ ቢያነሳም ለዕርቁ ተግባራዊነት እውን መኾን ሦስት ቅድመ ኹኔታዎችን መላኩን የአዲስ ነገር የቤተክርስቲያኒቱ ምንጮች ገልጸዋል። የመጀመርያው ቅድመ ኹኔታ በአቡነ መርቆሪዮስ የተመረጡት ዐሥራ ሦስት በአሜሪካ የሚገኙ ጳጳሳት በአዲስ አበባው ሲኖዶስ ተቀባይነት ማግኘት አለባቸው የሚል ሲኾን፤ ሁለተኛው ደግሞ አቡነ ጳውሎስ እና አቡነ መርቆርዮስ በክብራቸው እኩል ኾነው እንዲጠሩ እንዲኹም በመንበርም በእኩል ስፍራ እንዲቀመጡ ይጠይቃል። ሦስተኛው እና የመጨረሻው ቅድመ ኹኔታ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያናት ውስጥ በቅዳሴ ስማቸው እንዳይነሳ የተደረገው የአቡነ መርቆርዮስ ስም እንደገና እንዲካተት የሚል ነው

This post is available in: ኸንግሊስህ

በአዲስ አበባ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶስክ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ እና በአሜሪካ የሚገኘውን “ስደተኛው” እየተባለ የሚጠራውን ሲኖዶስ ለማስታረቅ በሚደረገውን የሽምግልና ሂደት የአሜሪካው ሲኖዶስ ሦስት ቅድመ ኹኔታዎችን ለመደራደርያ አቀረበ።

በአቡነ መርቆርዮስ የሚመራው የአሜሪካው ሲኖዶስ የዕርቅ ሐሳቡን በመጀመርያ ቢያነሳም ለዕርቁ ተግባራዊነት እውን መኾን ሦስት ቅድመ ኹኔታዎችን መላኩን የአዲስ ነገር የቤተክርስቲያኒቱ ምንጮች ገልጸዋል። የመጀመርያው ቅድመ ኹኔታ በአቡነ መርቆሪዮስ የተመረጡት ዐሥራ ሦስት በአሜሪካ የሚገኙ ጳጳሳት በአዲስ አበባው ሲኖዶስ ተቀባይነት ማግኘት አለባቸው የሚል ሲኾን፤ ሁለተኛው ደግሞ አቡነ ጳውሎስ እና አቡነ መርቆርዮስ በክብራቸው እኩል ኾነው እንዲጠሩ እንዲኹም በመንበርም በእኩል ስፍራ እንዲቀመጡ ይጠይቃል። ሦስተኛው እና የመጨረሻው ቅድመ ኹኔታ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያናት ውስጥ በቅዳሴ ስማቸው እንዳይነሳ የተደረገው የአቡነ መርቆርዮስ ስም እንደገና እንዲካተት የሚል ነው።

ይህንኑ የዕርቅ ጥያቄ እና ቅድመ ኹኔታ ሐምሌ 6 ቀን 2002 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያለው ሲኖዶስ ባደረገው ጉባዔ ተመልክቶታል።  በዚሁ ጉባዔ ላይ በአንደኛ እና በሦስተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡት ቅድመ ኹኔታዎች የማያስቸግሩ እና ለስምምነት የሚያበቁ ሐሳቦች በመኾናቸው ጉባዔው ተስማምቶ አሳልፏቸዋል። ነገር ግን በመንበር እና በክብር እኩል ይኹኑ የሚለው ላይ ጉባዔው ውሳኔ ለማሳለፍ እንደተቸገረ እና ለመቀበልም ቀላል ኾኖ እንዳልተገኘ ምንጮች ለአዲስ ነገር አስረድተዋል። ይኹንና ለቤተ ክርስቲያን ቅርብ የኾኑ ሰዎች “ይህንም ቢኾን መቀበል ካባድ ላይኾን ይችላል” ሲሉ ያብራራሉ። “አቡነ ጳውሎስ በሥልጣን እና በኀይል ፣ አቡነ መርቆርዮስ ደግሞ በክብር እና በመንበር እኩል ኾነው መቀጠል ይችላሉ” ይላሉ።

የጉባዔውን ውሳኔ ይዘው ሽምግልናው ለማካሄድ የተመረጡት  ጳጳሳት ወደ አሜሪካ እንዲላኩ መደረጉን የአዲስ ነገር ምንጮች ገልጸዋል። ወደዚያው ያመሩት ብፁዕ አቡነ ገሪማ፣ ብፁዕ አቡነ አትናትዮስ፣ መጋቤ ብሉይ ሠይፈ ሥላሴ ዮሐንስ እና ንቡረ ዕድ ኤልያስ አብርሃ ናቸው።

በሁለቱ ሲኖዶሶች መካከል ያለውን ልዩነት ለመፍታት የዕርቅ ሐሳብ መቅረብ ከጀመረ የቆየ ቢኾንም እስከ አሁንም መፍትሄ አላገኘም። በዚህ ዕርቅ ላይ ከቤተክርስቲያን ሰዎች ውጭ ሌሎችም ተሳትፎ እና ጥረት ማድረጋቸውን ምንጮች ለአዲስ ነገር ገልጸዋል። ከእነዚህም መካከል ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅ፣ አቶ አበበ ወርቄ እና አቶ ታምሩ ወንድም አገኘሁ ይገኙበታል።

ይህን ችግር ለመፍታት ለሽምግልና የተመረጡት ጳጳሳት በሁለቱም ወገን ቅሬታን የማያሳድሩ ናቸውም ተብሏል። ለዚህም ዋነኛው ምክንያት ሁለቱ ጳጳሳት አቡነ ጳውሎስ እና አቡነ መርቆርዮስ ሲለያዩ እና ችግሩ ሲፈጠር በቦታው የነበሩ እና ጉዳዩን ከሥር ከመሠረት የሚያውቁ ናቸው በሚል ነው። ይህን የዕርቅ ሐሳብ ያመጣው በሁለቱም ጳጳሳት ላይ የሚታየው የዕድሜ መግፋት እና ጤንነት ማጣት እንደኾነ ውስጥ አዋቂዎቹ ያስረዳሉ።

One Response to “የአሜሪካው ሲኖዶስ ለዕርቁ ሦስት ቅድመ ኹኔታዎችን አስቀመጠ”

  1. Zemenew Woubalem 1 September 2010 at 12:51 am

    the link for Dereje Haile’s news is mistakenly connected to Googlenewspaper. Please, fix it. Otherwise, it is a superb online media!
    Keep it up!
    -

Leave a Reply

You must be to post a comment.

Bad Behavior has blocked 1039 access attempts in the last 7 days.