ቴዲ አፍሮ በካምፓላ
ከአገሩ ከወጣ 20 ዓመት የኾነው አንድ ኢትዮጵያዊ “እኔ በአገሬ ላይ ቴዲን ለማየት ባልችል ወደ “አገሬ/ዩጋንዳ” ሲመጣ እንኳን ደህና መጣህልኝ ብዬ ለመቀበል ነው የመጣኹት። ዛሬ ሁሉም ዘፈን ቀርቶብኝ አንድ ዘፈን እንዲዘፍንልኝ እፈልጋለሁ። በቅርቡ የለቀቀውን “አልሞላውም ኪሴን” የሚለውን። እሱን ካልዘፈነ እናደድበታለሁ።” አለ። በዚህ ዘፈኑ ቴዲ ሞራሊስት መኾኑን እንዳረጋገጠለት ይናገራል። “እንደ ማኅበረሰብ ከፍተኛ የኾነ የሞራል ልሽቀት ውስጥ መኾናችንን በደንብ እየሳየን ነው። ለገንዘብ ስንል ማንነታችንን ጥለናል። እሴቶቻችን ረስተናል። ስግብግብ እና ቀጣፊዎች፣ ሌቦች እና ቀማኞች ኾነናል። በዚሁ ማንነታችንም ደስታን አጥተናል። ይሉኝታ እና ኅሊና ቢስ ከመኾን ይልቅ ማጣትን እመርጣለሁ እያለ ነው።” ይለዋል ለሞራሊስትነቱ ምክንያት ሲደረድር።
Read more

Recent Comments