በ“አምቼዎች” ዓለም ውስጥ፡ ፖለቲካ ፣ ማንነት እና ስደት
(ልዩ ጥንቅር)
አምቼነት ከኤርትራ ጋራ ብቻ አይቆራኝም። ከኢትዮጵያ በተለይም ከአዲስ አበባ ጋራ ባለው ጥልቅ ትሥሥርም ይገለጻል። አሥመራ ላይ “አምቼዎች” በነገረ ሥራቸው ተለይተው ይታወቃሉ። “ብዙ ኤርትራውያን አማርኛ ቋንቋን የሚናገረው አማራ ብቻ ይመስላቸው ነበር። ከ1990 ዓ.ም በኋላ ብዛት ያላቸው አምቼዎች ከኢትዮጵያ ተባርረው አሥመራን አጥለቀለቋት” ይላል ቢኒያም። ከዚያ በኋላ አምቼዎችን አሥመራ ውስጥ ለመለየት ቀላል ነበር። አማርኛ የሚናገሩ፣ በአረማመዳቸው፣ በአለባበሳቸው፣ በአንጻራዊ መልኩ በተላበሱት ግላዊ ነጻነት ይታወቃሉ። የአማርኛ ሙዚቃ በአሥመራ እንግዳ በኾነ መልኩ በስፋት የሚያዳምጡትም አምቼዎች ነበሩ።


Recent Comments