የአቶ መለስ ጸጉርና የሕገ መንግሥቱ ምሰሶዎች
መለስ ፖለቲካን የሚመለከቱት በጥቁርና ነጭ ቀለም ብቻ ነው። ይህም ንግግራቸውና አስተሳሰባቸው በጽንፋዊ አቋሞች እንዲሞላ ያደርገዋል። ሰውየው ሃይማኖተኛ ቢሆኑ ኖሮ አልሻባብን የመሰሉ ሴክቶችን በቀላሉ ሊቀላቀሉ ይችሉ እንደነበር እገምታለሁ። አሁንም ሕገ መንግሥቱን ስለማሻሻል ተጠይቀው የሰጡት መልስም እንዲሁ ያለ ነው፤ ቀላሉን አክርረው፣ ከባዱን አጥቁረው፣ በመጨረሻ የተሟላ ትርጉም የማይሰጥ የተምታታ ሐተታ አቅርበዋል። አቶ መለስ እርሳቸውና ፓርቲያቸው ሕገ መንግሥቱ “የሚሻሻል ምንም ነገር የለውም” ብለው እንደሚያምኑ፤ ነገር ግን “መለስተኛ ጉዳዮች ላይ ማሻሻያ ቢደረግ ጽጉሬን እነጫለሁ ማለት አይደልም፤ የሚነጭ ካለ” ብለዋል። የአዲሱ ፓርላማቸው አባላትም በሳቅ አጅበዋቸዋል።
በመጨረሻ አቶ መለስ ይህን ተንኳሽ መልእክት በዚህ ወቅት ማስተላለፍ የፈለጉበትን ምክንያት መጠየቅ ያስፈልጋል። ዋናውና አስቸኳዩ የአቶ መለስ ግብ ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ይሁኑ ከዚያ ውጭ ያሉ ተቺዎቻቸው ነክሰው የሚጮኹበትን አዲስ አጥንት/አጀንዳ መስጠት ነው። ይህም በአገሪቱ የሰፈነውን አፈናና የኢኮኖሚ ችግር በመጠኑም ቢሆን ያስረሳ ይሆናል ብለው አስልተው ይሆናል። ሁለተኛው የማብራሪያው ግብ “የአውራ ፓርቲ” ትምህርትን በመከለስ እርሳቸውና ፓርቲያቸው የማይፈልጉት፣ “በሰላማዊ መንገድ እታገላለሁ” የሚል ፓርቲ እንኳን ቢሆን የሚኖረው በእርሳቸውና በሥርዓታቸው ቸርነትና ሆደ ሰፊነት እንጂ ሕጋዊ መሠረት ኖሮት እንዳልሆነ በድጋሚ ለማረጋገጥ ነው። ይህም ቢሆን የዋህ ተቃዋሚዎችን ለማነጫንጭና ‘ለማስቆጣት’ በቂ ይሆናል።



Recent Comments