Blogs

RSS feed for this section

The Ethiopian Gaze

Derese Getachew/addisnegeronline.com

I always wonder if this ambivalent and pensive visual exchange, which never involves words, is an Ethiopian value in itself. Or is it ambivalence that Ethiopians find themselves in trying to reconcile their home grown norms of greeting everyone, including strangers with western values of greeting? Back home; people nod, wish you peace, or ask you how your evening has been when meeting you. In Ethiopia, passing by without greeting a bystander leaves a very eerie feel and a bad taste in the mouth of anyone.

Read more

ጥያቄው ከስኳር እና ከዋልድባ መምረጥ አይደለም

ቁሳዊ ልማትን የማፋጠን እና ታሪካዊ/መንፈሳዊ እሴቶችን የመጠበቅ ጉዳይ ሁልጊዜም አብረውና ተስማምተው ላይሄዱ ይችላሉ። አንዱን ለማሳደግ ሌላውን ዋጋ ማስከፈል የሚያስፈልግበት አጋጣሚ የመስተጋብሩ ቋሚ መገለጫ ይመስላል። ጥያቄውን በአንድ ነጠላ የልማት ፕሮጀክት አንጻር መመልከት ይቻላል። “ፕሮጀክቱ እገሌ የተባለውን ታሪካዊና መንፈሳዊ እሴት ያለው ቦታ/ሕንጻ… ይነካዋል አይነካውም? ከነካው ምን ያህል? ወዘተ” በሚሉ ጥያቄዎች ዙሪያ መነጋገርም መደራደርም ተገቢ ነው። ከዚህ መሰሉ ዝርዝር ንግግር በፊት ግን በመጀመሪያ ስለ “ልማቱ” እና ሰለ “እሴቶቻችን” ምንነትና ፋይዳ ዘርዘር አድርጎ መነጋገር ይገባን ነበር። ይህ በተለያዩ ወገኖች የሚሰጠው የተለያየ ሚዛን ቢያንስ ለሚቀጥሉት 100 ዓመታት በሚካሔዱ የልማት ክንውኖች መላልሶ እንደሚገጥመን አልጠራጠርም። ለዚህም ነው በቅድሚያ በሐልዮት ደረጃ ጉዳዩን ማብላላት አስፈላጊ ነው የምለው። የቁሳዊ ልማታችን እና የባህል ልማታችን ምንና ምን ናቸው?

Read more

የአድዋ ልጆች፤ ምኒልክ፣ መለስ እና እኔ

የታሪክ አጋጣሚ ሆኖ አድዋ ምኒልክን ብቻ ሳይሆን ጠቅላይ ሚኒስትር መለስንም ወልዳለች። ልጅነታቸው ግን ለየቅል ነው። ምኒልክ ለአድዋ የመንፈስ ልጅ ናቸው፤ መለስ የደምና የአጥንት ልጅ ናቸው። የደምና የአጥንት ልጆች የመንፈስ ልጅነትንም ደርበው የማግኘት እድል አላቸው፤ ሁልጊዜም ግን ላይሳካ ይችላል። ገብረ ሕይወት ባይከዳኝን አይቶ ድርብ ልጅነቱን ማድነቅ ነው፤ መለስን ተመልክቶ የደምና የአጥነት ሆኖ መቅረቱን መታዘብ ነው። መካ የተወልዶ ሁሉ በነብዩ መንፈስ እንደማይቃኝ፣ የቤተልሔሙ ልጅ ሁሉ በክርስቶስ መንገድ እንደማይሔድ መሆኑ ነው።

Read more

ከቢቢሲ ጋራ

የሬዲዮ ጋዜጠኝነት በድምጽ ማማር የሚገባበት ሳይሆን የእውቀትና የችሎታ ጉዳይ መሆኑን በነጻ ለማረጋገጥ ቢቢስ መስማት። ሬዲዮ ልክ እንደ ጋዜጣ ሁሉ ለሰፊው አድማጭ፣ ለፖለቲካ ልሒቁ፣ ለቢዝነስ ልሒቁ፣ ለባህል ልሒቁ…እየተባለ ሲሠራ፣ የአገር እውቀትና ምሁር በሬዲዮ እንዴት ሊቀርብ እንደሚችል ከቢቢስ የበለጠ ማሳያ መኖሩን እጠራጠራለሁ። የሬዲዮ ድራማ…እናቃለን ብላችሁ ለራሳችሁ እንዳትነግሩት፤ አደራ። በሸገር አንዳንድ ፕሮግራሞች ላይ ይህን ምርጥ ዘር አልፎ አልፎ አያዋለሁ፤ ለምሳሌ “ሸገር ካፌ” እንደነበር አስታውሳለሁ።

Read more

An Oromo Obama Revisited

by Derese Getachew

Here, I would like to recognize that the debate about the “Oromo question” and its fate in relation to the Ethiopian state has been a subject of household discussion among the Oromo elite itself. Recently, moderate voices about addressing the Oromo question are becoming loud and persuasive. We also heard about negotiations undertaken by the Ginbot 7 leadership and OLF factions (I don’t know how many factions are out there) about policy matters. Any Ethiopian from any political dispensation should welcome such moves and gestures NOT because G7 and OLF are the “sole and legitimate representatives” of non-Oromos and Oromos respectively. In lieu, they command significant following and posture in the opposition camp. Even if they do not, we welcome their moves as fellow concerned citizens.

Read more

Book Screw: Bereket Simon’s “Berkleaks”

I read Bereket’s propaganda book “Ye Hultet Mirchawoch Weg.” It is full of lies beyond proportion. I do not think any writer officially commissioned to fabricate lies can beat his record. Consequently, it does not worth any serious counter argument or fact check. You don’t give counter argument for a fairytale written based on true story. For instance, he wrote about Addis Neger newspaper.

Read more

የሽብርተኝነት ፖለቲካ እና የአቶ መለስ ቁማር

(ይህ ጽሑፍ አገር ቤት ለሚታተመው “ፍትሕ” ጋዜጣ የተጻፈና የወጣ ነው። የጋዜጣው አዘጋጆችካደረጓቸው አነስተኛ ማስተካከያዎች በቀር በጋዜጣው የወጣው ጽሑፍ ይኼው ነው። ጽሑፉን ለጋዜጣው ከላኩ በኋላ ያገኘኋቸውን መረጃዎችና ማስተካከያዎች እዚህ ተካተዋል።)

ከአንድ የሴናተሮች ቡድን ጋር የተገናኙ አንድ ምንጭ እንደሚሉት አሜሪካ የሁለቱን ጋዜጠኞችም ሆነ የሌሎቹን ኢትዮጵያውያን አቻዎቻቸውን መፈታት የምትፈልገው በኢትዮጵያ ያለው ሥርአት ዴሞክራሲያዊ ይሆናል በሚል እምነት አይደለም። የራሳቸውን ቃል ለመጠቀም “ጋዜጠኞቹ እንዲፈቱ የምንፈልገው ኢትዮጵያ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ትኩረት ውስጥ እንዳትገባ ለመከላከል ነው።” አራት ነጥብ። መለስ ከዚህ በተቃራኒው የዓለም አቀፉን ትኩረት በጨቋኝ ገጽታቸው መሳብ ይፈልጉ ይሆን? ካልፈለጉ ከነአሜሪካ ጋራ ይስማማሉ። ቀሪው የተለመደውን የማርያም መንገድ ፈልጎ ስዊድናውያኑን መፍታት ይሆናል። ኢትዮጵያውያኑ ጋዜጠኞች እስክንድር ነጋ፣ ርእዮት ዓለሙ እና ውብሸት ታዬስ? ጥያቄ ነው።
በኦብነግ በኩል ግን ዜናው “በረከተ መርገም” ነው። እዚህ ያነጋገርኳቸው የኦብነግ አባላት ፊት ለፊት ባይናገሩትም በጋዜጠኞቹ መያዝ ድርጅታቸው እንዳልከሰረ ይምናሉ። “በሁሉቱም መንገድ ማትረፋችን አይቀርም ነበር” ነው ሒሳቡ። ጋዜጠኞቹ ተሳክቶላቸው ዘገባቸውን ይዘው ቢወጡ በሆነ መንገድ መለስን የሚያጋልጥ እንደሚሆን ጥርጥር እንዳልነበረው አንድ የኦብነግ የወጣቶች ማኅበር መሪ አጫውቶኛል። ብዙ ተመልካቾች ኦብነግ ጋዜጠኞችን ለመርዳት የሚያነሳሳ ጠንካራና ምክንያታዊ (ሌጂቲሜት) ፍላጎት እንዳለው ይምናሉ። አሁን ጋዜጠኞቹ መያዛቸውም ቢሆን በተዘዋዋሪ የሚናገረው ኦጋዴን ውስጥ “ዓለም ሊሰማው የማይገባ” ነገር መኖሩን ይመስላል።

Read more

“አሸባሪሪነት!” የነጻነት እዳችን፤ የገዢነት እዳቸው

በመጨረሻው መጨረሻ የነጻነት ፈላጊዎች ጥያቄ ግፍን በማብዛት፣ አዲስ ስም በመለጠፍ፣ በማሰር፣ በመግደል፣ በማሰደድ ተሸንፎ እንደማያውቅ የተረጋገጠ ነው። እነአቶ መለስ ዛሬ ለማስፈራሪያ ጥቂቶቻችንን መረጡ እንጂ የአሸባሪሪነት “ወንጀሉ” ኢትዮጵያ የነጻነት አገር ሆና ለማየት የሚመኙና ባመኑበት መንገድ የሚሠሩት ዜጎች ሁሉ ነው። በዚህ ቀልደኛ ክስ መካታት የነአቶ መለስን ትኩረት የመሳብ ማረጋገጫ ከመሆን አልፎ ተከሳሾቹ ከሌሎች የበለጠ ለኢትዮጵያ የሚያስቡ/የምናስብ ወይም የታገልን ተደርጎ የሚያስቆጥር አይደለም። ወይም እንደዚያ አይነት ስሜት አይሰማኝም። ብዙ ሠርተው በክሱ የተካተቱ እንዳሉ ሁሉ፣ ምንም የሠራን (ያሸበርርን) ሳይመስለን የተካተተንም አለን። እርግጥ ማሸበርር መቻሌን ማወቄ አልከፋኝም። የእነአቶ መለስ ውቃቢ ተከሳሾቹን ከሌሎቹ “ወንጀለኞች” እንዴት አድርጎ እንደሚመርጥ ለማወቅ አልሞከርኩም፤ ትርጉም ስለሌለው። በክሱ ስማችን የተጠቀስነውም ሆንን ያልተጠቀሳችሁት ሚልዮኖች ነጻነትና ዴሞክራሲን በመጠየቁ “ወንጀል”ሁላችንም አንድ ነን፤ “እስክንድር ነጋ ነኝ! አንዱዓለም አራጌ ነኝ (I am Eskinder Nega, I am Andualem Arage. . .) እንደማለት! ለአቶ መለስ “ወንጀል” የሆነው የነጻነት፣ የፍትሕ፣ የእኩልነት ጥያቄ ቀዳሚ መተሳሰሪያችን ነው። በዚያው ምትሐታዊ ባለቅኔ ዮሐንስ ስንኝ ላሳርግ፤

ዘመን ቢያርቃችሁ፣
ስፍራ ቢለያችሁ፣
ዕንባ አጋጠማችሁ።

Read more

The ‘T’ Word: Terrorists’ of Ethiopia unite!

If you are one of those human beings concerned about matters of freedom, justice or democratic transition in Ethiopia: Beware, terrorism is lurking around your doors! It would come and turn you into a hobgoblin bent on societal destruction. Do you need advice? Stop thinking, then rest assured you will not be a suspect for terrorism.

Read more

የተለመዱትን ተጠርጣሪዎች እሰሩ!

የኦነግ እና የግንቦት 7፣ አልፎም የኦብነግ ጥያቄ የፖለቲካ ጥያቄ ነው። ድርጅቶቹን አሁን በተያዘው ፋሽን “ማዳከም ይቻላል” ተብሎ ታስቦ ይሆናል፤ ጥያቄዎቹን ማጥፋት ግን አይቻልም። የኢሕአዴግን ዘመቻ በተቃራኒው ካየነው ለእነዚህ ድርጅቶች የማያገኙት ድጋፍ እየሰጣቸው እንደሆነ መረዳት አይከብድም። በዚህም ልክ ኢሕአዴግ እንደደርግ በራሱ አንገት ላይ ገመድ እየጠመጠመ ይገኛል። የእነአቶ መለስ ትንቢትና ፍርሐት የሮበርት መርቶንን “ራሱን የሚፈጽም ትንቢት” (self-fulfilling prophesies) ያስታውሰኛል። መርተን እንደሚለው እነዚህ ትንቢቶች የሚደርሱት ዋናዎቹ ባለቤቶች “እውነት ናቸው፤ ይደርሳሉ” ብለው ስለሚያምኑ፤ በዚሁ እምነታቸው ላይ በመመሥረትም ተግባራዊ ምላሽ ስለሚሰጡ ነው። ለኢሕአዴግም በአጠቃላይ ተቃዋሚዎቹ በተለይ ደግሞ እነግንቦት 7 እና እነኦነግ በራሳቸው የሚፈጸሙ ትንቢቶች ሆነውበታል። ኢሕአዴግ እነዚህና ሌሎቹም ቡድኖች የሚያነሱትን የፖለቲካ ጥያቄ በፖለቲካዊ መንገድ ቢፈታ ቡድኖቹ/ጥያቄዎቹ እውነት ሆነው እንደሚያከስሩት፣ የጭቆና ስርአቱ ከስሩ እንደሚናድ ያውቃል። እነአቶ መለስ የዘነጉት ነገር እነዚህ ቡድኖች “በሕገ ወጥ” መንገድ ሊገለብጡዋቸው እንደሚችሉ መተንበይና ለትንቢቱም ምላሽ መስጠት በመጀመራቸው ከኪሳራው ሊያመልጡ የሚችሉበት እድል መዘጋቱን ነው። በሁለቱም በኩል ኢትዮጵያ አምባገነንነትን ከትከሻዋ አሽቀንጥራ ትጥላለች። ትንቢቱ ይደርሳል፤ ቀርቶም አያውቅም። እስከዚያው “የተለመዱትን ተጠርጣሪዎች” አሸብሩ፣ ክበቡ፣ እሰሩ፣ ግደሉ።

Read more

Vacancy Announcement

EQI looks for a senior statistical analyst with a strong background in economics and a good knowledge of the history of the Soviet Union. The remuneration is extremely attractive.

Read more

The New Ethiopia: Oligarchic Authoritarianism

Welcome to the emerging Ethiopia-an oligarchic authoritarian state that juggles the support and international assistance of an ambivalent west and a regardless China. In the tradition of Marx’s dialectical materialism (an orphan of modernity currently bashed for being Teleological, Universalist and Eurocentric), one thing is evident- every stage of societal development has systemic contradictions and hence sows its seeds of destruction.

Read more

We Killed You Because We could

“…Thirty-six protestors were killed, scores more injured, and thousands of young people across the country we rounded up and detained. Government officials were blunt about these tactics – to crackdown so hard that the momentum of protest would be halted. Once source surprisingly close to government went further. He told me that security forces had opened fire on demonstrators quite deliberately to show who was in charge.” Peter Gill, Famine and Foreigners

Read more

Migration and Democracy: India Vs. Ethiopia

Via Aidwatchers, political scientist Davesh Kapur provides an interesting theory as to why a diverse, multi-ethnic and populous country as India is able to sustain its democracy. Kapur argues that the migration of the country’s highly educated elite to the West has given previously excluded social groups more political power and rights. “Because older Indian [...]

Read more

[አንድ ለቅዳሜ!] ከብርቱካን እስር ወደ ብርቱካን ጥያቄዎች

ክርክሩ “ለምን ይቅርታ ጠየቀች” ሳይሆን በዋናነት ይቅርታ ለመጠየቅ ተጠቀመችበት የተባለው አገላለጽ ነው። በእውነትም አገላለጹ እርሷን ለማዋረድ፣ ደጋፊዎቿን ለማሳፈር ሆን ተብሎ የተቀመረ እንደሆነ የሚያከራክር አይደለም። በዚህ ጉዳይ ላይ የብርቱካንን ምስክርነት ሳንሰማ “ይህኛውን ቃል፣ ያኛው አረፍተ ነገር” ብሎ መከራከር ትርጉም ካለው መደምደሚያ ላይ ማድረስ አይችልም። ብርቱካን ይቅርታ በጠየቀችበት ደብዳቤ ውስጥ በጣም ያስገረመኝን አንድ አረፍተ ነገር ልጥቀስ። “…ወደዚህ ስህተት ልገባ የቻልኩት መንግሥት የውጭ ኀይሎችን ተጽእኖ በመፍራት ሊያስረኝ አይችልም፤ ካሰረኝም ተገዶ በአጭር ጊዜ ይፈታኛል በሚል የተሳሳተ ግንዛቤ ነው።” ቃላት ለአንድ ቀን እግር አውጥተው ወደየመጣችሁበት ተመለሱ ቢባሉ እነዚህ ቃላት የነብርቱካንን ሰፈር (ፈረንሳይ ለጋሲዮን) ዳገት ችለው ይወጡታል? ብርቱካን ይቅርታው ስለጠየቀችበት ከባቢያዊ፣ አካላዊ እና ስነ ልቦናዊ ሁኔታ የራሷን ቃል ሳንሰማ “ቢሆንም…ምንም ቢሆን…” ማለት ብዙዎችን ከወዲሁ የሚያሳጣ አመለካከት ይመስለኛል። ጊዜ ሰጥቶን ዝርዝሩን እንሰማለን።

ሁለተኛው የአመለካከት ዘርፍ “ዋናው መፈታቷ” ብሎ የሚቆመው ነው። ይህ ምልከታ ለብርቱካን ሰብአዊነት የበለጠ ቦታ ይሰጣል፤ ለከፈለችው ዋጋ ከፍተኛ ዋጋ በመስጠትም “እርሷ የበኩሏን አድርጋለች” ብሎ ሊያምንም ይችላል። ከዚያም ባለፈ ስል ልጇ እና እናቷ ወዘተ በማሰብ መፈታቷን የራሱ ግብ አድርጎ ያስቀምጠቃል።

Read more
[አንድ ለቅዳሜ!] ይቅርታ ለብርቱካን ወይስ ይቅርታ ከብርቱካን? ይቅር ባዩ ማነው?

[አንድ ለቅዳሜ!] ይቅርታ ለብርቱካን ወይስ ይቅርታ ከብርቱካን? ይቅር ባዩ ማነው?

በአጭሩ አቶ መለስ ብርቱካን “ድጋሚ ይቅርታ ትጠይቅና እንለቃታለን” እያሉን ነው። መለስ “ካለፈው ታሪኳ አንጻር ድጋሚ ይቅርታ ብትጠይቅ አይገርመኝም፤ መንግሥትም ከልምዱ አኳያ ይቅርታ ቢያደርግላት አይደኝቀንም” ብለዋል። ትርጉም ግልጽ መሰለኝ።እንዲያውም አይጋ ፎረም ላይ እንዳነበብኩት ከሆነ እርሷ ብቻ ሳትሆን ቤተሰብም፣ ጠበቃም…ስለእርሷ ተገብቶ ይቅርታ ሊጠይቅላት እንደሚችል አንቀጽ ተጠቅሶ “አቅጣጫው” ተብራርቷል። በአጭሩ ጥሪው “እርሷ እምቢ ማለቷ ስለማይቀር እባካችሁ አንዳችሁ ይቅርታ ጠይቁላትና እንገላገል” ይመስላል። በቀዳሚው የቅንጅት አመራሮች እስር ወቅት ፕሮፌሰር መንስፍ ወልደ ማርያም “ለኢሕአዴግ የማርያም መንገድ እንስጠው” በማለት ታሳሪዎቹ እንዲፈርሙ ሐሳብ አቅርበው ነበር ይባላል። ይህም ሌላ “የማርያም መንገድ” ጥያቄ ይሆን?

ሞራል በፖለቲካ ውስጥ ያለውን ቦታ ባስታወስኩ ቁጥር የዛሬዎቹ ይቅርታ ጠያቂ እና ሰጪዎች ልዩነት አብሮ ይመጣብኛል። ብርቱካ እና መለስ የሁለት ትውልድ ብቻ ሳይሆን የሁለት ዓለምም ሰዎች ናቸው (“መለስ” ስል አቶ መለስን ብቻ ማለቴ አይደለም፤ “ብርቱካን” ስል የእርሷን ሐሳብ የሚጋሩ በተለይም የትውልድ አቻዎቿን ማለቴ እንደሆነ ሁሉ)። በዚህ ጉዳይ ላይ በሌላ ጽሑፍ እመለስበት ይሆናል፤ መለስ፣ ብርቱካንን እና ቴዲን ሊረዷቸው ያልቻሉበትን ምክንያት ፍለጋ። ለመሆኑ አሁን ይቅርታ ጠያቂው ማነው? ይቅርታ ሰጪውስ? ብርቱካን የእነአቶ መለስን ይቅርታ ትፈልጋለች ወይስ እነአቶ መለስ የእርሷ ይቅርታ ይገባቸዋል? ዓለም ይህን አትፈቅድ ይሆናል እንጂ ለነገሩስ በአደባባይ ብርቱካንንም ሆነ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ መጠየቅ የነበረባቸው አሳሪዎቿ ነበሩ።

Read more

Opposition Politics: Beyond Pitfalls and Ahead

All of the blame on the current situation cannot be laid on the door of the incumbent. We have witnessed a relentless fall out and division of the opposition camp in recent years. Most of the times, these divisions are either about strategies or personalities.
…Much of what comes in leadership also depends on the followership. In my opinion, most people who sympathize, if not support, the Ethiopian opposition has adversely impacted the way the leadership attempted to operate, often out of positive intentions. One of the usual pitfalls is the urge to see immediate results and hence hurrying opposition parties to do this or that as soon as possible. I call it the temptation of time.

Read more

[አንድ ለቅዳሜ!] መለስ ኮሎምቢያ ፖፕ ቤኔዲክት እንግሊዝ

በነገራችን ላይ

የሰሞኑ የኢሕአዴግ ጉባኤ ምን ማለቱ ነው? እኛ እኮ ቻይና ሞዴላችን ናት ሲባል በኢኮኖሚ ብቻ መስሎን ነበር። ውይ በፓርቲ ልብስም ጭምር ሆነ እንዴ? ኮፍያው አልቀረ፤ ምንጣፉ አልቀረ። አይ እንዲህ ከሆነ አንድ ፊቱን አጠራርም ይቀየርልና። ሊቀ መንበር መሌ ይባልልን፤ ልክ ሊቀ መንበር ማኦ ወይም ሊቀ መንበር መንጌ እንዲል። ጉባኤው በኢቲቪ የተዘገበበት መንገድ ደግሞ በልጅነታችንን ያየነውን የኢሰፓ ጉባኤ የሚያስታውስ ነው። “አውራ ፓርቲ” በደንብ እየገባችን ነው።

ግን ግን ይሄ “አውራ ፓርቲ” የሚለው ስያሜ በድርጅቱ ሊቀ መንበር ታምኖበት የጸደቀ ነው? ትርጉሙ እኮ ያምታታል። ለምሳሌ “አውራ” የሚለው ዋና፣ ታላቅ፣ መሪ፣ የጫጩቶቹ ፓርቲዎች ሁሉ አባት የሚል በጎ ትርጉም ይሰጣል። እናቲቱን ዶሮ መፈለግ የሕዝብ ጉዳይ ነው።
ጸረ ልማትና ጸረ ሕዝብ ኀይሎች ግን “አውራ” የሚለውን “እንደልማድህ ለፍልፍ፣ ተናገር፣ ወሬ እንደሆን አያልቅብህም፣ አንተን ከማዳመጥ ሌላ ምን ምርጫ አለን አውራብን፣ ደሞ ጀመረህ በል አውራብን ልባችንንም አውልቀው” እያሉ የተሳሳተ ትርጉም ሊሰጡት ይችላሉ። እስቲ አሁን አንዱ ተንኮለኛ “አውራ ፓርቲያችን” ሲል ምን ማለቱ ነው? ደግሞስ ይህ ስያሜ አጋር የምንላቸውን ፓርቲዎች ጸረ ሕዝቦች “ጫጩት ፓርቲዎች” እንዲሏቸው በር አይከፍትም ወይ? በሒደት “አውራ ፓርቲ” ምስጋና መሆኑ ቀርቶ ስላቅ ሊሆን ይችላል። ስለዚህ ወይ ይህንን ቃል አለአግባባ አጥብቆ ወይም አላልቶ ማንበብን፤ እንዲሁም ለራስም ሆነ ለሌላ ሰው ከተፈቀደው ውጭ የሆነ ትርጉም ሊሰጥ በሚችል ወይም ሊሰጥ ይችላል ተብሎ በሚያስጠረጥር ቃናና ድምጽ መናገርን የሚከለክል ሕግ ማውጣት የአዲሱ ፓርላማ የመጀመሪያ ስራ ይሁን አለዚያም ሳይለመድ ይቀየር። አማራጭ መጠሪያዎችን እንቀበላለን። ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

Read more
DancingAnimals

So You Think You Can Dance? Try Politics!

The most daunting task is measuring how much the New Generation is ready to invest in order to set the country on the right track. Is the New generation politically matured and courageous enough to learn from history? What is the root cause of this generational obsession in our politics, anyway? Is it uninterrupted generation-wide dissatisfaction, or lack of intentional collaboration among generations?

There will not be any clear-cut, single-generation politics. Finding the right mix of generations, both at the party and national level, is the cardinal question of political succession. Anyone who “thinks s/he can dance” can join politics. So you think you can dance? Play politics.

Read more

Tradition and Modernity: A Faustian Bargain?

No wonder civility and celebrating dissent were the trademarks of Ethiopian society when it comes to a very crucial issue potentially divisive and violent-our understanding of God. Some serious criticisms about Ethiopia’s modern intellectuals on my last articles have made me question whether I (as an individual) and us (as a collective) have the courage to declare that our understanding of any notion is by no means a monopoly of the truth. This is an obvious truism, which is seldom translated into action.

Read more

Some Thoughts About Mass Protest(Part 1)

The problem is that sequential protests can happen only in authoritarian regimes with a relative degree of apprehension to use the oppressive machinery of the state early and decisively. The Sene 1 protests show how a brutal early response (killing 42 people in less than 4 hours) thwarted the formation of positive cascades, or worse, created the reverse effect(fence-sitters constructing even higher fences). Compare that to Haile Selassie’s meek responses to the sequence of protests before the revolution and how it made students and other members of social groups think that dissent was not ruthlessly punishable.

Read more

On Abune Paulos Statue and Birhanu Nega’s Paper

As it is the act of the patriarch and his people, most of those who debate the statue’s meaning and validity do so only in terms of the tenets of the church’s teaching and its history. They take it as an internal debate; something that “others” have no standing in. But the truth is this: this is not a bust erected in a compound of a church. It is in a public space in one of the trendiest areas of our capital. Monuments and statues in cities have profound human value. They not only represent the human condition; they are part of the condition itself.

Read more

Ethiopia’s Leadership Void

When was the last time where we saw mothers or fathers being appreciated for being model parents? Which religious leader deserves to be called an advocate of human rights and justice in Ethiopia out of conviction for a socially relevant belief? Do we have somebody anywhere close to personalities like Archbishop Desmond Tutu? How successful have we become in producing successful athletes, musicians, artists, philosophers and thinkers that we can look up to as leaders? When was the last time we have read famous literary works in the ranks of “Fikir Eske Mekaber” or “Adefris”? In almost every aspect of our national life, there is a decline and, even worse, a glaring lack of iconic leaders-role models that the young generation could look up to.

Read more
ሐውልቱ፤ ባለሐውልቱ እና ሐውልተኞቹ- የድቀቱ ምስክሮች

ሐውልቱ፤ ባለሐውልቱ እና ሐውልተኞቹ- የድቀቱ ምስክሮች

ቤተ ክርስቲያኒቱ ካለችበት ቀውስ አንጻር አሁን የሚያስፈልጋት ጥልቅ ራስን የምር የመፈተን ቁርጠኝነት ነው። የቤተ ክርስቲያኒቱን መሠረታዊ አስተምህሮዎች፣ ትውፊት እና ታሪክ ግምት ውስጥ ያስገባ የመንፈሳዊ እና ተቋማዊ ለውጥ አብዮት/ተሐድሶ ሊያመጣ የሚችል ራስን የመፈተሽ ተጋድሎ ይጠብቃታል። ሐውልት የሚቆምለት ተጋድሎም እርሱ ይሆናል። ይህ የለውጥ አብዮት ከየት ይነሣል፣ እነማን ያሥነሱታል፣ እንዴትና እንደ ምን ተጀምሮ በምን ይጠቃለል ይሆን? የሚሉት ጥያቄዎች ቀላል መልስ የላቸውም።

እስከዚያው ግን ቢያንስ ለድቀቱ ማስታወሻ ይሆን ዘንድ ለአባ ጳውሎስ የቆመው ሐውልት ባለበት ይቆይ። ባይሆን ከግርጌው የሰፈረውን ጽሑፍ መቀየር ይሻላል። “ወደ መንበሩ ከመጡ ጀምሮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የገባችበት መንፈሳዊ እና ተቋማዊ ድቀት በየዓመቱ 99.6 በመቶ እንዲያድግ ስላደረጉት መንፈሳዊና ስጋዊ ተጋድሎ ምስክር ይሆን ዘንድ ልጆቻቸው ይህንን ሐውልት አቆሙላቸው።” ሐውልቱን አታፍርሱት።

Read more

Can ESAT Be Our Al Jazeera?

I am sure the owners of ESAT have thought seriously about the fantastic weapon they have built. They ought to be thanked by all Ethiopians who are eager to see a robust public sphere and alternative media in Ethiopia. Just before the start of the World Cup, the Spanish sports newspaper Marca had this amazing headline: “Spain Are the Best in the World; Now Prove It.” ESAT is a great idea; now prove it.

Read more

Bad Behavior has blocked 2470 access attempts in the last 7 days.