ከፍ ያለ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ተደረገ
– የኑሮ ውድነትን በማባባስ ማህበራዊ ምስቅልቅል እንዳይፈጥር ተሰግቷል::
በሊትር 12.36 ብር ሲሸጥ የነበረው ነጭ ጋዝ (ኬሮሲን) ከዛሬ ጀምሮ በ14.05 ብር መሸጥ ጀምሯል፡፡ የአንድ ሊትር ቤንዚን ዋጋ ሲሸጥበት ከነበረው 16.50 ወደ 18.33 በማሻቀብ የ1ብር ከሰማኒያ ሳንቲም ግሽበት አሳይቷል፡፡ በሊትር 13.94 ብር ይገኝ የነበረው የነጭ ናፍታ ዋጋ አሁን ወደ 16.37 አሻቅቧል፡፡
(ኤፍሬም ካሳ)
ከመጋቢት 1 እስከ 30 2003 ዓ.ም ተግባራዊ የሚኾን አዲስ የዋጋ ጭማሪ ተመን ትላንትን ይፋ ተደረገ። በዚህ መሰረት ቤንዚን፣ነጭ ጋዝ/ኬሮሲን/ እና ነጭ ናፈታ ከፍ ያለ የዋጋ ማሻቀብ አሳይተዋል። ናፍታ በሁለት ብር ከ45 ሳንቲም እንዲሁም ነጭ ጋዝ 1 ብር ከ70 ሳንቲም ጨምሯል፡፡
ትናንት ምሽት በመንግስት መገናኛ ብዙሃን ለሕዝብ ይፋ በተደረገው ጭማሪ መሠረት በሊትር 12.36 ብር ሲሸጥ የነበረው ነጭ ጋዝ (ኬሮሲን) ከዛሬ ጀምሮ በ14.05 ብር መሸጥ ጀምሯል፡፡ የአንድ ሊትር ቤንዚን ዋጋ ሲሸጥበት ከነበረው 16.50 ወደ 18.33 በማሻቀብ የ1ብር ከሰማኒያ ሳንቲም ግሽበት አሳይቷል፡፡ በሊትር 13.94 ብር ይገኝ የነበረው የነጭ ናፍታ ዋጋ አሁን ወደ 16.37 አሻቅቧል፡፡
የነዳጅ ምርቶች ላይ የተደረገው ጭማሪ ትላንት አመሻሽ 12፡00 ሰዓት ላይ በይፋ እንደተደረገ በማግስቱ ከሚገጥማቸው ጭማሪ ለመዳን የአዲስ አበባ የነዳጅ ማደያዎችን በረጃጅም ሰልፎች ያጨናነቁ ባለመኪናዎች ተሳክቶላቸው ነዳጅ ሊቀዱ አልቻሉም፡፡ የነዳጅ ማደያዎቹ በማግስቱ የሚያገኙትን ትርፍ በማሰብ ምርቶቻቸውን ይዘው የለም ማለቱን መርጠዋል፡፡ የታክሲ ትራንስፖርትን በተመለከተ ከአጭር መንገድ እስከ ረጅም መንገድ የሚጓዙ ባለ ታክሲዎች ከ 5ሣንቲም እስከ 20 ሣንቲም ጭማሪ አድርገዋል፡፡
አዲስ አበባ አራት ኪሎ በሚገኘው ኮቢል ነዳጅ ማደያ ውስጥ በነዳጅ ቀጀነት የሚተዳደሩ አንድ ሰራተኛ”‹‹ እስቲ አስበው! እኔ ከሥራዬ ልምድ እንዳየሁት የነዳጅ ምርት ዋጋ ሲጨምር የኑሮም ነገር በዚያው ልክ እሳት ይሆናል፡፡ አሁንስ እንዴት እንደምንዘልቀው እንጃ!?” ብለዋል ለሪፖርተራችን።
በዚሁ የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ጭማሪ ሳቢያ በሸቀጦች ላይ የተደረገው “የዋጋ ንረት ማረጋጊያ ተመን እርባና ቢስና ፍሬ-አልባ ሊሆን እንደሚችል አዲስ ነገር ያነጋገራቸው አንድ የምጣኔ ሀብት ባለሞያ ይናገራሉ። ‹‹ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ከዋጋ ግሽበት ጋር በተያያዘ እየተከሰቱ ያሉት እንግዳና ተከታታይ ኢኮኖሚያዊ ኹነቶች የኢህአዴግ መንግሥት ኑሮውን ማረጋጋትና ምጣኔ ሀብታዊ ጉዳዮችን በብቃት መምራት እንደተሳነው ጠቋሚ ናቸው›› ይላሉ።
ባለሞያው ‹‹ የነዳጅ ዋጋ ንረት ከኑሮ ውድነትና ፖለቲካዊ እመቃ ጋር ተደምሮ ሕዝባዊ ንቅናቄን ሲያስከትል በአገራችንም ሆነ በዓለም ያልተለመደ ክስተት አይደለም›› በማለት የቀዳማዊ ኃይለሥላሴን ሥርዓት ውድቀትና የ1970ዎቹ የአረቡን ዓለም እና የኃያላን አገራት ማህበራዊ ምስቅልቅል በአስረጅነት ያቀርባሉ፡፡
የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ የትራንስፖርት ዋጋን በማናር ብቻ አያበቃም፡፡ የቀጥታ ተፅዕኖውን በሸቀጦች ዋጋ ላይ ያሳርፋል። የትራንስፖርት ዋጋ መጨመር ተከትሎ በአገር ውስጥ የሚመረቱ እህሎችና ሌሎች መሰረታዊ ሸቀጦች ዋጋም ይጨምራል፡፡ “ይህ በተዘዋዋሪ ሥራ አጥነት በተንሰራፋበት እና አብዛኛው ሕዝብ በድህነት በሚኖርባት አገራችን ላይ የሚያስከትለው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ አያጠያይቅም “ይላሉ ባለሞያው።
በቅርቡ በግብፅና በቱኒዚያ የተካሔዱት አብዮቶች ዋነኛ መንስኤ የዋጋ ንረት፤ሥራ አጥነት፤ ጭቆናና አምባገነንነት ናቸው። ሁሉም መንሳኤዎች በኢትዮጰያ ተንሰራፍተዋል። ከትላንት ምሽት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች ላይ የተደረገው ጭማሪ እና ተያይዞ ሊመጣ የሚችለው የኑሮ ግሽበት የአዲስ አበባ ነዋሪ አበይት ርእሰ ወሬ ኾኖ ውሏል።
የተደረገው ጭማሪ ካለፈው ሐምሌ ጀምሮ ተግባራዊ ሲደረግ የአሁኑ ለዘጠነኛ ጊዜ መኾኑ ነው፡፡
we cant do any thing we dont have oil ….
its not only for ethiopia its in all over the world
you know here in england 0.10 peney
0.10X28=2.80
what do you mean we have no oil, do you think the whole country have oil, first of all you have to have mind to realize this thing. anyways everything has its consequence and may be it become the reason.
its shame to judge own people with bad impression.
Dear Mel, don’t forget how much u earn per hour in England! and that is the point if u can understand.
Let the Derg kills me than povert kills me.If I shut my mouth at least i live. Under woyane you can shut your mouth but still poverty kills you, kills you alive. Look at ethiopians, they are very thin and don’t look healthy. Bekum memot yihe new.
Don’t worry! Ato Meles has exceptional knowledge of Economics. He will handle it. lol
mel
Why we should always take it that way? “Yes of-course it is for all countries” but, why don’t we see the other way – meaning “the governments inability to improve the financial capability of the people so that we would be able to deal with such hardship”. If the government had done that, it would have not been a serious issue for the people to discuss. But, everyday our income is decreasing in relative terms and our expenses are going up. on the other hand, this is not the case in England or in any other developed nation. The governments there work a lot in improving their people’s income. So, the people often don’t blame the issue on the government. But, in our case we have the right to blame it on the Government since they have not done well in raising people’s income. ሜልዬ እኛ ግን የልማት ወሬ ብቻ እኮ ነው የተረፈን መሰረታዊ ለውጥ በከን ተቀን ህይወታችን ውስጥ ማየት አልቻልንም
ዝም ብሎ ማየት የሚጠቅም ይመስለኛል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ የነዳጅ ፍለጋ ጥረቶችን አስመልክቶ ባስረዱበት የፓርላማና የፕሬስ መግለጫዎች ላይ ነዳጅ ቢገኝ ጥሩ ነው የሚጠላ የለም፤ ባይኖርም ከእድገት ግስጋሴያችንን የሚገታው አይሆንም የሚል ነው፡፡ ይህ አባባል ተገቢ ቢመስልም ውስጠ ወይራ ነው፡፡ ምክንያቱም ስለሌለው ሳይሆን ስላለው የሚገባውን ያህል ጥረት አልተደረገምና ነው፡፡ የካሉብ ጋዝ በደርግ የተጀመረ ፕሮዤ ቢሆንም ዛሬም ድረስ ወደ ምርት አልገባም፡፡ ከዚህ የሚገኘው የውጭ ምንዛሬ ባያጠግብ እንኳን እንዲህ ዓይነቱን ክፉ ጊዜ ለማምለጥ የሚያስችል አይሆንም ብሎ መናገር ግን አይቻልም፡፡
ኢሕአዴግ እጅግ ፈታኝ ነገር እየገጠመው ነው፡- የባለሥልጣናቱ ሙሰኝነትና ስግብግብነት በሕዝብ አስተዳደር ፍትሕን እያሳጣ ነው፡፡ በኢኮኖሚው ውስጥ የገበያ አለመረጋጋትን እያመጣ ነው፣ ነዳጅ ሕዝብን እንደ እሳተ ገሞራ እየናጠ ነው፡፡ ምናልባት ሰላማዊ በሆነ መንገድ ይህን ክፉ ቀን ለማለፍ የሚቻልበት የሠለጠነ ምክክርና የሥልጣን ሽግግር ይደረግ ይሆን? አይደፈሬው ደርግ በጠብመንጃ ወደቀ አይደፈሬው ኢሕአዴግ በዚህ ውጥንቅቅ በዝረራ ከጨዋታ ውጪ ይሆን? አይሆንም ትተሽ … ይላል የአገር ሰው ስለሆነም መንግሥት ራሱ ለዚህ ጉዳይ በአስተዋይ ልቡና ሊያስብበት ይገባል፡፡ ባልተደራጀ የሕዝብ ተቃውሞ ስም የሚመጣው መከራ ከጥላቻ ያልዘዘለ ከሆነ ጥፋቱ ወደር ላይገኘለት ይችላልና፡፡
ሰላም ለአገራችን ኢትዮጵያ ሰላም ለሕዝባችን
ገንዘቡን ከሚበሉት ኣይደጉሙበትም በጣም ነው የሚያሳዝነው መናገር ክምችለው በላይ የሚያሳዝን ነገር ነው እየተከሰተ ያለው/ ኢህኣዴግ መጨረሳውን ቢያሳምር ሳይሳለው ኣይቀርም
Mel you seem to support the failing regime of Ethiopia. If you can really think, in UK or here in America most of the people (remember most of the people) are working and the effect has less impact but In our country, most of the people do not have work or constant income generation mechanism so what ever is added the effect is termandous.
Moreover here in US or there in Europe whatever the government says is for the sake of serving the people but in the case of Ethiopia , whatever is said by mele’s is for the sake of giving one more day in Menilik’s palace …
Take it easy, this is the outcome of two digits growth per year. No income but ever increasing expense.. Go Mele go to the edge of the cliff
me!
Ayito Woyane
You can’t do any thing?
Time is approaching when you do something.
Another topic to divert the hot issue of ‘public uprising’. A ready-made religous conflict in South West Ethiopia is costing the life of innocent poor Ethiopians. It seems that these two events are taking our attention effectively. Both situation show the failure of the system. The regime needs to change and a truly concerned government will solve all kinds of conflicts.
The regime want to project that it is confident even in the face of public uprising in middle east and North Africa.That is why the price hike now! The suffering and pain of poors would not matter.
Regrettably, Meles is a mentally sick man. Often times he doesn’t even remember what he said publicly. Back in December 2003 E.C., he told us that Ethiopia’s economy was growing at a healthy rate. In January he told his parliamentarians that he needed to impose price controls and restrictions on several goods because Ethiopia’s economy was “on the verge of collapse”. Last month, he was showing us his economics know-how by forcing merchants to cut their prices by half. This month his mastery of economics is revealed in the form of raising price of oil. Trust me, the ingenious Meles will come at the end of the year to tell us that the economy grew 14% in 2003 E.C. If you dare to remind him of his “on the verge of collapse” speech, he will tell you that you misread or mispronounce his phrases. Anybody remember his infamous “fiscal”/“physical” joke with Bulcha Demeksa’s remarks last year?
I think this is the right time to stand together we lost our freedom,Economy, country and ourselves i don’t know what we are waiting for??
I don’t understand why people are shouting at the government. We live in an era of globalization.
Today, OIL price is $100 per barrel. THIS is price of crude oil; Not benzene yet.
1 barrel = 117 liters
i.e. $0.85 for one liter. OK!
When you add refinery cost and transportation cost – it goes beyond $1.30. OK!
Today 1USD = 16.67 ETB
Therefore, in Ethiopia, 1 liter petroleum has to be sold at 21.67 ETB. The government still subsidizes the reminder.
This is The truth, the whole truth and nothing but the truth!!
Teklay !!
You are underestimating the expenses. You are fool and dumb like all other woyane foot soldiers. No doubt you are not even aware that you are supposed to add add port fee for Ethiopia who does not have port outlet. The blood thirsty Meles is just dumb like you. You do not see the value of a port for a country and simply give it away just like your poo…
Teklay
What is truth? The traders were also mentioning this very same truth you spoke about. They say we cannot sell good at the government’s price line since we get it at high cost. If the governments price increase is fair to the government and you, so it is for the merchants.
On another point, if you follow internation price for goods, also take international numeration for workers. You just cannot take one thing and drop the others. The truth is TPLF could not run the country. They were only good at fighting. The Derg even was much better in managing the country. Were it not for socialist ideaology, the country would have been in a much better shape. It is amzing that there comes a time where we even strat to praise the cruel Derg comparing with the incompetent woyanies.
Today no one is immune from the high cost of living. Is it not shame that year after year ethiopian cannot feed themselves. Even the TPLF cadres that get thousands of birr cannoit feed themselves, because the prices of goods has increased by 1000%.
Thanks Teklay!… I can see many of us are wildly blind to analyze things!… every person tries to politicize every thing!… I don’t know why!