"; _gaq.push(['_trackPageview']);(function() { var ga = document.createElement('script'); ga.type = 'text/javascript'; ga.async = true; ga.src = ('https:' == document.location.protocol ? 'https://ssl' : 'http://www') + '.google-analytics.com/ga.js'; var s = document.getElementsByTagName('script')[0]; s.parentNode.insertBefore(ga, s); })();

“ፈርጀ ብዙ ድህነት”-የ19 ዓመታት ፍሬ?

የኢትዮጵያ መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት በሁለት ዲጂት ኢኮኖሚው እያደገ መኾኑን በተደጋጋሚ ይገለጻል፡፡ ይኹንና አሁንም የማክሮ ኢኮኖሚ አለመረጋጋት እና አስተዳደራዊ ድክመት ዋነኞቹ የአገሪቱ መለያ እንደኾኑ አሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት 5.2 ሚልዮን ሕዝብ አስቸኳይ ርዳታ የሚሻ ነው፡፡ ባለፈው ሳምንትም ይፋ የኾነው የ“Investing Across Borders” ሪፖርት እንዳመለከተው አገሪቷ ከሰሃራ በታች ከሚገኙት አገራት ንጽጽር እንኳ ስትታይ በዝቅተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ ለውጭ የቀጥታ ኢንቨስትመንት አበረታች ያልኾነች አገር ተብላም ተፈርጃለች፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አውታር ችግሮች መፍትሄ ለመፈለግ  የኢኮኖሚ ባለሞያዎችን እና የኀልዮቶችን (Theories) ድጋፍ የሚሹበት ምክንያት ያላቸው አይመስሉም፡፡ ዘወትር እንደሚያደርጉት ኢኮኖሚውን “ያባብሉታል” ወይም ደግሞ በመሳይ የኢኮኖሚ ዕድገት ምጣኔዎች ከለላ ባለጉዳዩን ሕዝብ ያዘናጉታል፡፡ አልፎ አልፎም ለተወሰነ ግብ ታልመው የጸደቁ ሕግጋትን በመጠቀም ኢኮኖሚውን እንዳሻቸው ይመሩታል፡፡ ሰሞኑንም ተመሳሳዩን ነገር ከመድገም አልቦዘኑም።

ከዐሥራ አምስት ቀናት በፊት ያልተሟላውን በጀት የመጨረሻው ተሰናባች ሸንጎ እንዲያጸድቅ ባደረጉበት ወቅት ተጨማሪ በጀት ለማስጸደቅ ዕቅድ እንዳላቸው ተናግረው ነበር፡፡ የዕቅዱን ዓላማ በአንድ ነገር አስደግፈው ግልጽ አደረጉ። ለተከታታይ ዓመታት በኑሮ ውድነት ሲጎሳቆል የኖረውን ሠራተኛ መደጎም ነው አሉ፡፡ ይህ ቀላሉ የመፍትሄ አማራጭ/መንገድ ነው፡፡ ብዙ ውጣ ውረድን አይጠይቃቸውም፡፡ ወደ ብሔራዊ ባንኩ ገዢ መደወል ብቻ ለቅለቱ በቂ ማስረጃ ይኾናል፡፡ እዚያ መፍትሄ አለ፡፡ በ2000 ዓ.ም ተሻሽሎ የጸደቀው “የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ አዋጅ” ገደብ ያልተበጀለት የመበደር አቅምን ለመንግሥት ሰጥቷል፡፡ አሁንም በድጋሚ የኾነው ይኼው ነው፡፡ በሳምንት ውስጥ 772 ሚሊዮን ብር ለሠራተኞች ደመወዝ በሚል መዝገብ ለ2003 ዓ.ም ሌላ በጀት ተዘጋጅቷል፡፡

ይህ ተጨማሪ በጀት በምን ያህል መጠን የሠራተኛውን ኑሮ እንደሚደጉም፣ የዋጋ ግሽበቱን እንዳያባብስ ስለሚወሰዱ ርምጃዎች እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ የማክሮ ኢኮኖሚ ችግሮች ዳሰሳ አልተደረገም፡፡ ብቻ ደመወዝ ይጨመራል፡፡ ይህ “ጊዜያዊ የማስታገሻ” ለ19 ዓመታት የተስተዋለ የመንግሥት ብቸኛ መፍትሄ ነው፡፡ እነዚህ የ“ሰነፍ እረኛ . . .” ዐይነት ተግባራት አጠቃላይ ድምር ላይ አዎንታዊ ለውጥ ሊያሰሙም ኾነ ሊያመጡ አልቻሉም፡፡ ኢኮኖሚው አሁንም የድኻውን ኑሮ ከማሻሻል ይልቅ የድኻውን ቁጥር በማብዛት ላይ ከመጠመድ አባዜው የሚያላቅቀው አልተገኘም።

ባለፈው ሳምንት የተሰማው አዲሱ የዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ጥናት ውጤት ደግሞ አገሪቷን የዓለም ጭራ በማድረግ የአቶ መለስን የ19 ዓመት የኢኮኖሚ “ኀልዮት” አፈር ያለበሰዋል፤ አፈር ይለውሰዋል፡፡ ይፋ የኾነው አዲሱ የድህነት መሥፈርት መለኪያ ከኢትዮጰያ አጠቃላይ ሕዝብ 90 በመቶ ያህሉ በከፍተኛ ድህነት ውስጥ የሚዳክር እንደኾነ ያረጋግጣል፡፡ ይህ ፈርጀ-ብዙ የድህነት መጠን አመልካች (Multidimensional Poverty Index-MPI) የሚል ሥያሜ የተሰጠው አዲስ የድህነት መሥፈርት በኦክስፎርድ የድህነት እና ልማት ኢኒሼቲቭ (Oxford Poverty and Human Development Initiative -OPHI) እና በተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) የጋራ ትብብር የተሠራ ሲኾን ከዚህ ቀደም ይሠራበት የነበረውን “በቀን አንድ ዶላር ” የድህነት መሥፈርት ውድቅ የሚያደርግ ነው፡፡

ከዚህ ቀደም ይሠራበት የነበረው “በቀን አንድ ዶላር” መሥፈርት በግለሰቦች ገቢ ላይ ተመሥርቶ የሚሰላ ሲኾን 1.25 የአሜሪካ ዶላርን የድህነት ወለል መለኪያ የሚያደርግ ነው፡፡  ከ1990ዎቹ ጀምሮ እየተሰራበት ያለው ይሄው መስፈርት ቀደም ሲል “አንድ ዶላር” እንዲሁም  ከግንቦት 2008 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ “በቀን 1.25 ዶላር”ን ለድኻ አገራት የኑሮ ደረጃ ማመላከቻ ያደርጋል፡፡ መሥፈርቱ ከገቢ ባሻገር ሌሎች ሰብአዊ የልማት ጉዳዮቹን የማያካትት መኾኑ በኢኮኖሚ ባለሞያዎች ሲያስተቸው ቆይቷል፡፡

በመጪው ጥቅምት ወር በተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም የ2010 ሪፖርት ጋራ ተያይዞ ይቀርባል ተብሎ የሚጠበቀው አዲሱ የድህነት መሥፈርት ግን ዋና የሰብአዊ አመልካች የሚባሉትን ትምህርት፣ ጤና እና የኑሮ ደረጃን በዐሥር ተዛማጅ ኢኮኖሚያዊ መመዘኛዎች በማስቀመጥ በቤተሰብ ደረጃ ሊኖር የሚችልን የድህነት መጠን ይለካል፡፡ የንጹህ ውኃ አቅርቦት፣ ንጽህና፣ የኀይል አቀርቦት እና የመሳሰሉት አገልግሎቶች የአዲሱ መለኪያ ማሳያ በመኾን ያገለግላሉ፡፡ “ማን ነው ድኻ?” ከሚለው የተለመደ የኢኮኖሚ ጥያቄ ባሻገር “ለምን ድኻ ኾነ?” የሚለውንም መመለስ ግድ ይኾናል፡፡

ይኼው ጥናት እንደሚያሳየው፤ መረጃ በተሰበሰበባቸው 104 አገራት የድህነት መጠኑ እና ዐይነቱ የበዛ ሲኾን ከአንድ ዶላር በቀን መሥፈርት ጋራ ሲነጻጸር 1.3 ቢሊዮን ሕዝብ በተጨማሪ በፈርጀ ብዙ ድህነት መሥፈርት የዝቅተኛ ደረጃ መለኪያ ውስጥ ወድቋል፡፡ ኢትዮጵያ ከእነዚህ አገራት አንዷ ስትኾን የፈርጀ ብዙ ድህነት አመለካቿ 0.58 ነው፡፡ ይህም በድኻዎች ቁጥር ብዛት እና ወደ ድህነት በሚወስዱ ምክንያቶች ብዛት የድኾች ሁሉ ድኻ እንድትኾን አድርጓታል፡፡ 70 ሚሊዮን ሕዝብ ወይም ደግሞ ዘጠና በመቶ ሕዝብ በፈርጀ ብዙ ድህነት ውስጥ የሚገኝ ነው፡፡ ይህ ደረጃ ከጎረቤት ሶማልያ እጅግ ያነሰ ኾኖ ነው የሚገኘው፡፡ ከሶማልያ የፈርጀ ብዙ ድህነት አመለካቿ 0.51 ሲኾን ይህም ከኢትዮጵያ የተሻለ የኑሮ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ ያመለክታል፡፡ ምጣኔው ከፍ እያለ ሲሄድ ውስብስብ ድህነትን ያመለክታል፡፡ ኬንያም የተሻለ ነጥብ አስመዝግባ ኢትዮጵያን በብዙ ርቀት እየመራቻት ነው፡፡

በድህነት የሚማቅቀው ማኅበረሰብ በትምህርት፣ በጤና እና በማኅበራዊ አገልግሎቶች የሚያገኘው ድርሻም እንዲሁ ዝቅተኛ ነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ መንግሥት ሪፖርት ከኾነ በተጠቀሱት መሥፈርቶች አመርቂ ውጤት አግኝቷል፡፡ አዲሱ ጥናት እንደሚገልጸው ግን በድህነት ስብስብ ውስጥ ከታቀፈው ማኅበረሰብ ከ20 በመቶ ያልበለጠው ብቻ የአምስተኛ ክፍል ደረጃን ያጠናቅቃል፡፡  በተመሳሳይ ዕድሜያቸው ከ1 እስከ 8 ከኾናቸው ሕጻናት 84.9 በመቶ የሚኾኑት ወደ ትምህርት ቤት የመሄድ ዕድል የላቸውም፡፡

በማኅበራዊ አገለግሎት ዘርፎችም መልካም የሚባል ወጤት አልተገኘም፡፡ በድህነት ማዕቀፍ ውስጥ ከሚገኙት ዜጎች 85.7 በመቶ ያህሉ የመብራት ኀይል አገለግሎት የማያገኙ ሲኾኑ 89 በመቶ ያህሉ ደግሞ ኩበት እና ፍግ ለምግብ ማብሰያነት የሚጠቀሙ ናቸው፡፡ 88.7 በመቶ ያህሉ ደግሞ ሬዲዮ፣ ቴሌቪዥን፣ ቴሌፎን እና የመሳሰሉት ንብረቶች የሏቸውም፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት በሁለት ዲጂት ኢኮኖሚው እያደገ መኾኑን በተደጋጋሚ ይገለጻል፡፡ ይኹንና አሁንም የማክሮ ኢኮኖሚ አለመረጋጋት እና አስተዳደራዊ ድክመት ዋነኞቹ የአገሪቱ መለያ እንደኾኑ አሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት 5.2 ሚልዮን ሕዝብ አስቸኳይ ርዳታ የሚሻ ነው፡፡ ባለፈው ሳምንትም ይፋ የኾነው የ“Investing Across Borders” ሪፖርት እንዳመለከተው አገሪቷ ከሰሃራ በታች ከሚገኙት አገራት ንጽጽር እንኳ ስትታይ በዝቅተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡  ለውጭ የቀጥታ ኢንቨስትመንት አበረታች ያልኾነች አገር ተብላም ተፈርጃለች፡፡

በኑሮ ሪፖርትም ይኹን በአጠቃላይ አገራዊ ኹነት አገሪቷ ያላት ምስል እየደበዘዘ ይገኛል፡፡ ይህም ኾኖ ከዓለም አቀፍ ጉባኤዎች ለአፍታም የማይጠፉት አቶ መለስ ዜናዊ ዛሬም የጥንድ ቁጥሮች የዕድገት ምጣኔን ዋነኛ መከራከሪያቸው ከማድረግ አልቦዘኑም፡፡ ነገም የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚያስመዘግቡ ቃል ገብተዋል፡፡ ነገ ቃላቸውን እንደሚጠብቁ ምንም መረጋገጫ የለም፡፡ ይህ ማለት ግን በመጪውም ጊዜ ለፓርላማ የሚቀርብ የ10 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት የለም ማለት አይደለም፡፡ ዕድገት እና ድህነት እጅ ለእጅ ተያይዘው የሚጓዙ ይመስል!?

2 Responses to ““ፈርጀ ብዙ ድህነት”-የ19 ዓመታት ፍሬ?”

  1. gud saysema meskerem aytebam !

  2. Good observation thank u z.

Leave a Reply

You must be to post a comment.

“ብርኒሂጎ” – የሌሊት ወፍ ማስታወሻ

በወዲ አፍሮ የተዜመው “ብርኒሂጎ” የተሰኘው ዜማ ከዓመታት በፊት በሀውልቲ አዳራሽ ውስጥ አቶ መለስ ራሳቸው ነጠላ አጣፍተው ድንቅ ተወዛዋዥ እንደሆኑ ያሳዩበት ዜማ ነው፡፡ ራስን በሚያሞግስ ዜማ መወዛወዝ ምን ስሜት ይፈጥር ይሆን? ይህን ዜማ ተከትሎ “ብርንሂጎ” የሚለው ቃል ተወዳጅ ከመሆኑ የተነሳ “ብርንሂጎ” የሚሉ የመለስ ፎቶ የታተመባቸው ብዙ ስቲከሮች ተሰርተው በታክሲዎችና ባጃጆች ላይ ተለጥፈዋል፡፡ በነገራችሁ ላይ ብርንሂጎ ትርጉሙ “የመስቀል ወፍ” ማለት ነው፡፡

የመስቀል ወፍና ዜናዊ መለስ
ቃልኪዳን ዳ’ላቸው ዳግም ለመንገስ
ማን ያውቃል?!

ሚያዚያ 30 ቀን 1947 ማለዳ አቶ መለስ ዜናዊ ተወለዱ፡፡ ከሁለት ወር በፊት 55ኛ የልደት በዓላቸውን አከበሩ፡፡ የዕድሜያቸውን ሲሶ ያሳለፉት ኢትዮጵያን በመምራት ነው፡፡ እንደ እኔ እንደ እኔ ሰውየው እረፍት ያስፈልጋቸዋል! ከአሁን በኋላ አነሰ ቢባል 5 ዓመት ይህችን አስቸጋሪ አገር ይመራሉ፡፡ በቃኝ ካሉ ከወንበራቸው ሳይነሱ 25 ዓመት ይሆናቸዋል፡፡ ሕዝቡ ግን “ያለ እርስዎ በሌላ አንመራም” ብሎ የቤት ውስጥ ነውጥ ከጀመረ ታሪኩ ሌላ ይሆናል፡፡ የሚወዱትን ሕዝብ “በእኔ ጉዳይ አያገባህም” ካሉት ግን ልክ የ60 ዓመት ሸንቃጣ አዛውንት ሆነው መንበራቸውን ለቅርብ ወዳጅ በአደራ መልክ ሊሰጡ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን እንደ ቴሌቪዥናችን አንዳንድ ፕሮግራሞች “አመራርዎ በሕዝብ ጥያቄ ይደገም” ከተባሉ ሺህ ዓመት ይመሩናል፡፡ ረዥም ዘመን መንገሥ የሚወዱ መሪዎችን ፈጣሪ ቶሎ ለምን እንደማይጠራቸው አሁን እየገባኝ ነው፡፡ እዚያም ያስቸግሩታል መሰለኝ፡፡

ከወጣትና ሴቶች ሊግ አባላት የሚወጡ የቅርብ ዜናዎች እንደሚጠቁሙት ከአራት ዓመት በኋላ የሚካሄድ በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ሰልፍ እየተሰናዳ ነው፡፡ አቶ መለስን “የጀመሩትን ይጨርሱ” ብሎ ለመማፀን፡፡ሰውየው የሚያልቅ ነገር ነው እንዴ የጀመሩት? የዚህ ታላቁ ሰልፍ አስተባባሪ ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ነው ሲሉኝ ግን ደነገጥኩ፡፡

እኚህ ሰው ይህችን አገር በመሩ ቁጥር የሚማረሩ እንዳሉ ሁሉ ከራሳቸው ዕድሜ ቆርጠው ለእርሳቸው ለመስጠት የማያቅማሙ አፍቃሪዎችም ሞልተዋቸዋል፡፡ ከእነዚህ የልብ አድናቂዎቻቸው መሀል በአመዛኙ የሚኖሩት በትግራይ ነው፡፡ ከሆነ ዓመት በፊት ለስራ ጉዳይ ከአዲስ አበባ ወደ አድዋ ስሄድ ከፊት ወንበር ቦታ ደረሰኝ፡፡ የተሳፈርኩባትን አውቶብስ ይሾፍራት የነበረው ሾፌር ተግባባኝ፡፡ ያደርንበት ሀይቅ የምትባል ሚስኪን ከተማ ነበረች፡፡ ራት አብረን በላን፡፡ አሳ ኮተሌት፡፡ ወደየመኝታችን ከመሄዳችን በፊት አይናችንን ለማድከም ቲቪ እያየን ነበር፡፡ ቲቪው በአንድ ስብሰባ ላይ አቶ መለስ ከቶኒ ብሌየር ጋር በእንግሊዝኛ መግለጫ ሲሰጡ ያሳይ ነበር፡፡ ሾፌሩ አይኔ እያየ አለቀሰ፡፡ የምሬን ነው፤ አ-ለ-ቀ-ሰ፡፡ በእንግሊዝኛ የተናገሩት ነገር ልቡን ነክቶት ይሆን ብዬ “ምን ሆንክ?” አልኩት፡፡ ዕንባውን እያበሰ እንዲህ አለኝ፡፡ “ወዲ ዜናዊን ሳየው ዕንባዬን መቆጣጠር አልችልም” አለኝ፡፡ እየቀለደ አልነበረም፡፡

በአዲሳባ አንድ ጎረምሳ ወደ ኪዮስክ ጠጋ ብሎ እስኪ ሲጋራ ስጠኝ ይላል፡፡ በመቀሌ አንድ ኮበሌ በአቅራቢያው ወደሚገኝ አንድ ፎቶ ቤት ሄዶ “ናይ መለስ ፎቶ ሀበኒ” ይላል፡፡ ሁለቱም የጠየቁትን ያገኛሉ፡፡ በመቀሌ አንድ የአቶ መለስ ጉርድ ፎቶ ከሁለት ዓመት በፊት በ 1.50 ብር ይሸጥ ነበር፡፡ አሁን ኑሮ ተወዶ ሦስት ብር ገብቷል፡፡ ለኑሮ ውድነቱ ግን ፎቶው ላይ ያሉት ሰውዬ ሀላፊነት አይወስዱም።

አንዳንዶች “እርሳቸው ዲሞክራሲን ለአፍሪካ ያስተዋወቁ ሰው ናቸው” ይላሉ፡፡ ሙግታቸውንን በማስረጃ ሲያግዙ ደግሞ ይህንኑ የፎቶ ንግድ ዋቢ በማድረግ ነው፡፡ አዲሳባ አራት ኪሎ ጎዳና ‹‹ጃ ያስተሰርያል›› ብሎ የዘፈነ፣ ጎዳና ተዳዳሪን የገጨ አዝማሪ፣ ስንት ሺህ ወጣት የፈጀው ባለመለዮው መንግስቱ፣ ፎቷቸው ከመለስ ጎን በአንድ ላይ ተዘርግቶ ይቸበቸብ የለምን? ለያውም ይህ እየሆነ ያለው አቶ መለስ በስራ ብዛት እንቅልፍ አጥተው ከሚገላበጡበት መኝታ ቤታቸው በትንሽ ርቀት በምትገኘው አራት ኪሎ አደባባይ ነው፡፡ ታድያ በዚህች አገር ዲሞክራሲ የለም ይባላል? ዕድሜ ለብርኒሂጎ!!!

መቀለ ከአክሱም ሆቴል ቁልቁል የሚገኘው መንገድ መልከ መልካም ካፌዎችና ትኩስ ልጃገረዶች ይበዙበታል፡፡ በዚህም የተነሣ ስፍራውን አዘወትረዋለሁ፡፡ እንደኔው ይህን ስፍራ የሚያዘወትሩ ጠና ያሉ የኔ ቢጤ አሉ፡፡ አቦይ ይባላሉ፡፡ ብዙ ሰው ያውቃቸዋል፡፡ በረንዳ ላይ ቁጭ ብለው ማክያቶ የሚጠጡትን ተስተናጋጆች በየተራ እየተጠጉ “ስለ አቡናረጋዊ” ይላሉ፡፡ ከፊሉ ‹‹ይርደአኹም›› ይላቸዋል፡፡ ‹‹እግዜር ይስጥልኝ›› ማለት ነው በአገሬው ቋንቋ፡፡ ከፊሉም ሳንቲም ይበትንላቸዋል፡፡ እኚህ አዛውንት በተጠጉኝ ቁጥር ከአንገታቸው ላይ ያንጠለጠሉትን ማህተብ እያየሁ እደመማለሁ፡፡ የአቶ መለስ ፎቶ ነው፡፡ እርሳቸውን በአካል አቶ መለስን በቲቪ ሳቃቸው ይኸው ስንት ዘመኔ፡፡ እንዴት በዚህ ሁሉ ዘመን አይለወጡም? መህተቡም ባለማህተቡም ማለቴ ነው፡፡

የአቶ መለስ ተክለ-ስብእና በትግራይ እየጎመራ እንጂ እየከሰመ አልሄደም፡፡ የእነ ሀየሎምና ስዬ የጦር ሜዳ ጀብዶች ድሮ ድሮ የመለስን ግዝፈት ጋርደውት እንደነበር የተረዳሁት አንደኛው በሞት ሌላኛው በህይወት ከህዝቡ ከተለዩት በኋላ ነው፡፡ አሁን አንድም የትግል አጋራቸው የመለስን ያህል ገዝፎ አይታይም፡፡ “ተራራውን ያንቀጠቀጠው ትውልድ” “ተራራውን ያንቀጠቀጡት ሰው” ወደሚል አፈታሪክ እየተቀየረ መሰለኝ ፡፡

የመለስ ወዳጆች ስለእርሳቸው ሲያወሩ ራሳቸውን ለመሳት ብዙም አይቀራቸውም፡፡ ልዕለ-ሰብ እንደሆኑ ሽንጣቸውን ገትረው የሚከራከሩላቸው የቤት እመቤቶችና የእውቀት ባላባቶች የትየለሌ ናቸው፡፡ ምሁራኑ ሙግታቸውን በቲዮሪ ይተውሩታል፣ ቤተ-ሙከራ ይዘውት ይገባሉ፣ ሲወጡ ያልነው ትክክል ነበር ይላሉ፡፡

መቀሌ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ቢሮ ውስጥ የአቶ መለስ ያረጀ ፎቶ ተሰቅሏል፡፡ እኔ መጀመርያ ሳየው ሰቅሎ የቀረ የድሮ ተማሪ እንጂ እርሳቸው አልመሰሉኝም ነበር፡፡ የኋላ ኋላ በየሄድኩበት መስሪያ ቤትና በየረገጥኩት ስራ አስኪያጅ ቢሮ ሁሉ ምስላቸው ሲከተለኝ ሰውየው የዋዛ እንዳልሆኑ ተረዳሁ፡፡ ተማሪዎች የእርሳቸውን ምስል ከደረታቸው አይነጥሉም፡፡ ልባቸውም ውስጥም አሉ፡፡ ሾፌሮች የቁልፍ ማንጠልጠያቸው ወዲ ዜናዊ ናቸው፡፡ በየጋራዥ ቤቱ፣ በየካፌው፣ በየጉልቱ፣ በፍሪጅ ላይ፣ በታክሲና ባጃጆች ውስጥ በስቲከር መልክ አቶ መለስ አሉ፡፡ “ሺህ ዓመት ይኑሩልን-እንወዶታለን” የሚለው የእርሳቸው ፖስተር በጀብሎ ነጋዴዎች ዘንድ እንኳ አይታጣም፡፡ በአንድ የከባድ መኪና ላይ “ገብሬል ተከተለኝ” ተብሎ የሚጻፍበት ቦታ የአቶ መለስ ፎቶ ገጭ ብሎ ሳይ ግን ይህን ጽሑፍ መጻፌ ያስቀስፈኝ ይሆን የሚል ስጋት ሸንቆጥ አደረገኝ-፡፡

ትግራዮች አመለሸጋ ናቸው፡፡ የመሀል አገር ሰው ይወዳሉ፤ ያቀርባሉ፡፡ የፖለቲካ ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው ፖለቲካም ያወራሉ፡፡ ትግራይ እንደተረሳች ሊያሰረዱ ይሞክራሉ፡፡ በመሀል አገር ሰው ስማቸው ያላግባብ እንደጠፋ ያስረዳሉ፡፡ ይህን ጊዜ እንግዳው ሰው የልብ ልብ ተሰምቶት ብዙ ሊያወራ ይችላል፡፡ አየተደመጠ እንደሆነ ሲያስብ መለስንም ሸንቆጥ ሊያደርጋቸው ይሞክራል፡፡ ይሄኔ ተሳሳተ፡፡ ለትችትም ለከት አለው፡፡ እንግዳው ሰው ወዲ ዜናዊን የትችቱ አካል አድርጎ ማውራት በጀመረበት ቅፅበት ብዙ ሰው እያስቀየመ እንደሆነ ሊረዳ ይገባው ነበር፡፡

በዚህ አካባቢ ብዙኀኑ በዐይኑና በመለስ እንዲመጡበት አይሻም፡፡ የአገሬው ሰው የተቃዋሚ ፓርቲ አባል ወይም ቅልጥ ያለ የህወሓት ተቺ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ ማለት ግን የወዲ ዜናዊ ተቃዋሚ ነው ማለት አይደለም፡፡ በዚህ ሰፈር ኤሕአዴግ ላስመዘገባቸው አንፀባራቂ ድሎች አቶ መለስ ይወደሳሉ፡፡ ለፈጸማቸው ቀይ ስህተቶች ግን ውግዘቱ የሚላከክባቸው የበታች ባለሥልጣናት ይፈለጋሉ፡፡ ለምሳሌ አለቃ ፀጋይ፡፡

ከምርጫው ወዲህ ትግራይን ለመጎብኘት የመጣ እንግዳ የትግራይ ከተሞች በአቶ መለስ ፎቶ መጥለቅለታቸውን ልብ ላይል አይቻለውም፡፡ የእርሳቸው ፎቶ የሌለበት ስፍራ ከወዴት ይገኛል? ለምሳሌ ሁሉም መቀሌ ፎቶ ቤቶች እየተሸኮረመሙ ”ሞዴላዊ” ፎቶ ከተነሱ ኮረዶች መሀል አንድ ግዙፍ የመለስ ፎቶ አይታጣም፡፡ ይህ ያልሆነበት አንድም ፎቶ ቤት አይገኝም፡፡አንድም፡፡ (ለበለጠ መረጃ ፎቶዎችን ይመልከቱ)

ለወዲ ዜናዊ ክብር የተዜሙ ሙዚቃዎች ከእለት እለት ቁጥራቸው አየበረከተ ቢሆንም በዋናነት ተደማጭ የሆኑት በድምፃዊ የማነ (ወዲ ኣፍሮ) የተዜመው “ብርኒሂጎ” የተሰኘው ዜማና የድምፃዊ ተወልደ የማነ ‹‹ይንገሰለይ ደኣ›› የተሰኘው ባህላዊ የትግርኛ ዜማ ነው፡፡ ሁለቱም ሙዚቃዎች በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ልማትና ስኬት በተወራ ቁጥር አየር ላይ ይውላሉ፡፡ በትግራይ ኤፍ ኤሞች ደግሞ ፍቅረኛሞች ይገባበዙታል፤ ዘፈን ምርጫ ፕሮግራም ላይ፡፡

በወዲ አፍሮ የተዜመው “ብርኒሂጎ” የተሰኘው ዜማ ከዓመታት በፊት በሀውልቲ አዳራሽ ውስጥ አቶ መለስ ራሳቸው ነጠላ አጣፍተው ድንቅ ተወዛዋዥ እንደሆኑ ያሳዩበት ዜማ ነው፡፡ ራስን በሚያሞግስ ዜማ መወዛወዝ ምን ስሜት ይፈጥር ይሆን? ይህን ዜማ ተከትሎ “ብርንሂጎ” የሚለው ቃል ተወዳጅ ከመሆኑ የተነሳ “ብርንሂጎ” የሚሉ የመለስ ፎቶ የታተመባቸው ብዙ ስቲከሮች ተሰርተው በታክሲዎችና ባጃጆች ላይ ተለጥፈዋል፡፡ በነገራችሁ ላይ ብርንሂጎ ትርጉሙ “የመስቀል ወፍ” ማለት ነው፡፡

የመስቀል ወፍና ዜናዊ መለስ
ቃልኪዳን ዳ’ላቸው ዳግም ለመንገስ
ማን ያውቃል?!

11 Responses to ““ብርኒሂጎ” – የሌሊት ወፍ ማስታወሻ”

  1. gud saysema meskerem aytebam !

  2. Good observation thank u z.

Leave a Reply

You must be to post a comment.

የኢኮኖሚ ዕድገቱ ሲፈተሽ

በቅርቡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማህኅበር በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ዓመታዊውን አለም አቀፍ ኮንፈረንስ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ ስብሰባው ከሌሎች አመታት በተሻለ በጥራትም ሆነ በብዛት ወረቀቶች የቀረቡበት በመሆኑ የሚደነቅ ነበር፡፡…ጥናቶቹ እንደሚያሳዩት የግብርና ምርታማነት ዕድገት ከዓመት ዓመት እየቀነሰ ነው፡፡ ገበሬው የተሻሻሉ የምርት ግብዓቶችን የመጠቀም ፍላጎቱም እጅግ ዝቅተኛ ሲሆን፣ ከግብርና ልማት ሠራተኞች ጋር ያለው ትብብርም አመርቂ አይደለም፡፡ እውነታው እንዲህ ከሆነ፣ ጥያቄው፣ “በየቀኑ የሚደሰኮርልን ተስፈንጣሪ የምርት ዕድገት ከየት መጣ?” ነው፡፡

በቅርቡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማህኅበር በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ዓመታዊውን አለም አቀፍ ኮንፈረንስ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ ስብሰባው ከሌሎች አመታት በተሻለ በጥራትም ሆነ በብዛት ወረቀቶች የቀረቡበት በመሆኑ የሚደነቅ ነበር፡፡

በስብሰባው ላይ ከቀረቡት ጥናታዊ ጽሑፎች ዋነኛ ትኩረት የነበረው የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ ዕድገትና የወደፊት አቅጣጫ፣ እንዲሁም ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ እና ከገጠር ወደ ከተማ ተደረገ የተባለውን መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር የሚመለከት ነበር፡፡

በርካታዎቹ ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡት በዓለም አቀፍ የምግብ ፖሊሲ ምርምር ኢንስቲትዩትና በአቶ ነዋይ ገ/አብ በሚመራው የኢትዮጵያ የልማት ምርምር ተቋም ትብብር በሚመራው የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ድጋፍ ፕሮግራም ተመራማሪዎች ነው፡፡ ጥናቶቹ በበለጠ በባለሙያዎቹ ሊተነተኑ እና ክርክር ሊደረግባቸው የሚገቡ ቢሆንም፣ እንደ ታዛቢ በጣም አነጋጋሪ የሆኑ ሁለት ጉዳዮችን ላንሳ፡፡

የመጀመሪያው የግብርና ምርታማነትን የሚመለከት ነው፡፡ ጥናቶቹ እንደሚያሳዩት የግብርና ምርታማነት ዕድገት ከዓመት ዓመት እየቀነሰ ነው፡፡ ገበሬው የተሻሻሉ የምርት ግብዓቶችን የመጠቀም ፍላጎቱም እጅግ ዝቅተኛ ሲሆን፣ ከግብርና ልማት ሠራተኞች ጋር ያለው ትብብርም አመርቂ አይደለም፡፡ እውነታው እንዲህ ከሆነ፣ ጥያቄው፣ “በየቀኑ የሚደሰኮርልን ተስፈንጣሪ የምርት ዕድገት ከየት መጣ?” ነው፡፡ ኢሕአዴግ በዚህ ጉዳይ እውነቱን ሊነግረን አይፈቅድም፤ ምርታማነት መቀነሱ ሲገለጽ ደግሞ የታረሰው መሬት በእጅጉ በመጨመሩ ምርታችንም ጨምሯል ይለናል፡፡ ምርታማነት እንዲህ እያሽቆለቆለ ባለበት ሁኔታ የግብርና ምርት ለአምስት ዓመታት በአማካይ በየዓመቱ በ8.5 በመቶ ዕድገት እንዲያሳይ የታረሰው መሬት መጠን ምናልባትም በእጥፍ መጨመር ሳይኖርበት አይቀርም፡፡ ይህ እንዳልሆነ እኛም ካድሬዎቹም እናውቀዋለን፡፡

ታዲያ ችግሩ ምን ይሆን? የተለያዩ መላ ምቶች ሊቀርቡ ይችላሉ፡፡ ይህን ተቃርኖ ያመጣው የኢሕአዴግ ቀሽም የውሸት ስታትስቲክስ ነው፡፡ ውሸቱ እድገት ሳይኖር አለ መባሉ አይመስለኝም፤ አለ የሚባለው ዕድገት እጅግ የተጋነነ መሆኑ እንጂ፡፡ ቀሽምነቱ ደግሞ የሚመስል ውሸት መዋሸት አለመቻሉ ነው፡፡ ማጣፊያው ያጠረው፣ ድሮም የነበሩት የምርታማነት ችግሮች እንዳሉ ሆነው፣ እንዲያውም ብሶባቸው ሳለ አደግን ለማለት ከመቸኮሉ የተነሳ የምርቱን መጠን በእጥፍ እጥፉ ጨምሯል ብሎ የውሸት አኀዝ ማቅረቡ ነው፡፡ ምናልባት ከዋሹ አይቀር ምርታማነቱም ጨምሯል ብለው ሊያሞኙን ቢሞክሩ ሳይሻላቸው አይቀርም ነበር፡፡

ሁለተኛው ጉዳይ ኢኮኖሚው ምን ያህል /በተለይ ከገጠር ወደ ከተማ/ መዋቅራዊ ሽግግር አድርጓል የሚለው ነው፡፡ በዚህ ረገድም በካድሬዎቹ የሚቀርብልን መረጃ ከአገሪቱ ጠቅላላ ገቢ የግብርና ድርሻ ወርዶ 42 በመቶ ስለደረሰ እና የአገልግሎት ዘርፉ ስለበለጠው፣ ኢኮኖሚው መዋቅራዊ ሽግግር እንዳደረገ ያሳያል የሚል ነው፡፡ በተጨማሪም በመንገድ ግንባታ ዘርፍ ከፍተኛ እመርታ በመታየቱ ከዋና መንገድ በአጭር ርቀት ላይ የሚገኙ ቦታዎች ቁጥር ጨምሯል፣ ስለሆነም ሀገራችን ከገጠርነት ወደ ከተማነት በመቀየር ላይ ነች ይባላል፡፡ ይሁንና፣ ይህን ለማሳየት የሚቀርቡት ጥናቶች ራሳቸው እንደሚያረጋግጡት፣ የግብርናው ድርሻ ዝቅ ብሏል ቢባልም አሁንም 85 በመቶ የሚሆነው ሕዝብ የሚተዳደረው በግብርና ነው፡፡ 84 በመቶ የሚሆነው ሕዝብ የሚኖረውም በገጠር ነው፤ ስለሆነም መዋቅራዊ ሽግግር ሲያልፍም አልነካን፡፡ በተጨማሪም የኢንዱስትሪው ዘርፍ የዕድገት መጠን የረባ ለውጥ አላሳየም፡፡ ከፍተኛ ዕድገት አሳይቷል የሚባለው የአገልግሎት ዘርፍ መነሻው የመንግሥት መዋዕለ ንዋይ ነው፡፡ ይህም አሁን ባለው መጠን ሊቀጥል ስለማይችል መንግሥት እጅ ያጠረው ጊዜ ዘጭ ብሎ የሚወርድ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር የመንግሥት ኢንቨስትመንት ከኢኮኖሚው ቢወጣ እሱን ተክቶ ኢኮኖሚውን ቀጥ አድርጎ የሚይዝ የግል ዘርፍ የለንም፡፡ ስለሆነም አለ የሚባለው ዕድገት እንኳንስ መዋቅራዊ ሽግግር ሊያመጣ፣ የሚጨበጥ እና ዘላቂ እድገት ነው ለማለት አያስደፍርም፡፡

ይህን ስል ግን የኢኮኖሚ ዕድገት የለም እያልኩ እንዳልሆነ ይታወቅልኝ፡፡ እድገት አለ፣ ግን እንደሚባለው የተጋነነ አይደለም፡፡ በትምህርት፣ ጤናና መሠረተ ልማት ላይ ብዙ ወጪ ተደርጓል፣ ድህነት ተኮር ስራ ተሰርቷል፤ ነገር ግን ግብታዊ እና ነባራዊ ሁኔታን ያላገናዘበ እንቅስቃሴ በመሆኑ ከፍ ያለ የጥራት ችግር ታይቷል፡፡ ግብታዊነቱ ጎልቶ የሚታየውም አሁን ያለው ሁኔታ በረዥም ጊዜ በኢኮኖሚው ላይ የሚኖረው አንድምታ በደንብ አለመታሰቡ ነው፡፡

በሌላ አነጋገር አሁን የያዝነው መንገድ የት እንደሚያደርሰን የተሟላ ስዕል የለም፤ ከብዥታ በቀር፡፡ የመንገድ፣ የኃይል፣ የትምህርትና የጤና አገልግሎትን ሽፋን መጨመሩ ጥሩ ነው፡፡ ግን ከዚያ በኋላስ? የምናስመርቀውን በመቶ ሺህ የሚቆጠር ባለሙያ የሚቀጥር የግል ዘርፍ አለን? ግማሹ ባለሙያ ስራ ፈጣሪ ሆኖ ባለሀብት እንዲሆን የተመቻቸ ሁኔታ አለን? የቁጠባ እና የኢንቨስትመንት ሁኔታችን ምን ይመስላል? ምርታማነቱ ያሽቆለቆለ እና የራሱን ሕዝብ መመገብ ያቃተው ግብርና ይዘን እንዴት ነው የአግሮ ኢንዱስትሪ አብዮት የምናካሒደው? በመንግሥት የሚደጎሙና መወዳደር የማይችሉ አነስተኛና ጥቃቅን ማህበራትን ይዘን እንዴት ነው ኢኮኖሚውን የሚለውጥ የሀገር ውስጥ ባለሀብት እንዲፈጥሩ የምንጠብቀው? ለመሆኑ የረባ ኢንዱስትሪ አለን? ከአየር ባየር ነጋዴዎች፣ ከገዢው ፓርቲ ድርጅቶችና ጥቅመኛ ባለሀብቶች ውጪ ይህ ነው የሚባል የግል ዘርፍ ባጭር ጊዜ ይኖረናል? የምናሰብው አብዮት በውጭ ኢንቨስትመንት ሊመጣ ይችላል? እነዚህን ጥያቄዎች ለማንሳት ኢኮኖሚስት መሆን የሚያስፈልግ አይመስለኝም፡፡ ለመልሱ ግን የዘርፉ ባለሙያዎች ትንተናና አስተያየት ወሳኝ ነው፡፡

የኢኮኖሚ ለውጥን ማቀድ የአገልግሎት ሽፋንን እንደማሳደግ ቀላል አይደለም፤ እንዲህ አይነቱ ለውጥ የብዙ ተዋናዮች እንቅስቃሴ ድምር ውጤት ስለሆነ፡፡ ኢህአዴግ በመንገድ፣ በትምህርትና በጤና አገልግሎት ማደግ ሲኩራራ ዋናውን ጉዳይ የዘነጋው ነው የሚመስለው፡፡

ይህ እንዳለ ሆኖ፣ ወቅታዊው አሳሳቢ ጉዳይ ስለኢኮኖሚው እውነተኛና አስተማማኝ መረጃ የሚገኘው እንዴት ነው? የሚለው ነው፡፡ ብቸኛው የመረጃ ተቋም የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ በሆነበትና ከዚያ የሚገኘው መረጃ እርስ በርሱ በሚቃረንበት ሁኔታ እንዴት አድርገን ስለ ኢኮኖሚው ትክክለኛ ስዕል ማግኘት እንችላለን? የኢኮኖሚክስ ትንተናውስ ውሸትን ከማጋለጥ አልፎ እውነታውን ምን ያህል ሊያሳየን ይችላል? የኢኮኖሚ ባለሙያዎች፤ እስቲ ያለንን ተስፋ ንገሩን።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

ቴዲ አፍሮ እና ኢዮብ መኮንን ወደ አሜሪካ አቀኑ

ዝነኞቹ ድምጻውያን ቴዎድሮስ ካሳሁን እና ኢዮብ መኮንን በዋሽንግተን ዲሲ በሚካሄደው ዓመታዊ የኢትዮጵያውያን የእግር ኳስ ጨዋታ ላይ ለመገኘት እና የሙዚቃ ሥራዎቻቸውን ለማቅረብ ከባንዶቻቸው ጋራ ወደዚያው አቀኑ።

ዝነኞቹ ድምጻውያን ቴዎድሮስ ካሳሁን እና ኢዮብ መኮንን በዋሽንግተን ዲሲ በሚካሄደው ዓመታዊ የኢትዮጵያውያን የእግር ኳስ ጨዋታ ላይ ለመገኘት እና የሙዚቃ ሥራዎቻቸውን ለማቅረብ ከባንዶቻቸው ጋራ ወደዚያው አቀኑ። በመጀመርያ አልበሙ በብዙ አድማጮች ዘንድ ተቀባይነትን ያገኘው እና እስከ አሁንም እንደ አዲስ እየተደመጠለት ያለው ኢዮብ መኮንን ማክሰኞ ሰኔ 21 ቀን 2002 ዓ.ም ከዛየንስ ባንድ ጋራ ወደ አሜሪካ ተጉዟል። ታዋቂው እና ተወዳጁ ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን ደግሞ ከአቡጊዳ ባንድ ጋራ በደቡብ አፍሪካ ያቀረበውን ኮንሰርት በማጠናቀቅ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት እንደገና ከባንዱ ወደ ዋሽንግተን አቅንቷል። በዚሁ ዓመታዊ የእግር ኳስ ውድድር ላይ የሙዚቃ ሥራዎቻቸውን እንዲያቀርቡ ግብዣ የተደረገላቸው ሌሎች ድምፃውያንም በቅርቡ ወደዚያው እንደሚያቀኑ የቅርብ ምንጮች ገልጸዋል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

ኤፍሬም እንዳለ “የዘመን ዱካ” የተሰኘ ረዥም ልብ ወለድ ሊያቀርብ ነው

ለበርካታ ዓመታት በፀደይ መጽሔት እና በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ “እንጨዋወት” በሚለው ዐምድ ሥር በሚያቀርባቸው ጽሑፎቹ እና በትርጉም ሥራዎቹ የሚታወቀው ኤፍሬም እንዳለ “የዘመን ዱካ” የተሰኘውን ሁለተኛውን የረዥም ልብ ወለድ በመጭው ወር መጀመርያ ላይ ለገበያ እንደሚያቀርብ ገለጸ። ደራሲ እና ተርጓሚ ኤፍሬም “ሕይወት በክር ጫፍ” በተሰኘው የመጀመርያው ልብ ወለዱ የሚታወቅ ሲኾን፤ “ፍዳ”፣ “ሰቆቃ”፣ “ሽሽት”፣ “ቤርሙዳ ትርያንግል” እና “በሰላይ [...]

ለበርካታ ዓመታት በፀደይ መጽሔት እና በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ “እንጨዋወት” በሚለው ዐምድ ሥር በሚያቀርባቸው ጽሑፎቹ እና በትርጉም ሥራዎቹ የሚታወቀው ኤፍሬም እንዳለ “የዘመን ዱካ” የተሰኘውን ሁለተኛውን የረዥም ልብ ወለድ በመጭው ወር መጀመርያ ላይ ለገበያ እንደሚያቀርብ ገለጸ።

ደራሲ እና ተርጓሚ ኤፍሬም “ሕይወት በክር ጫፍ” በተሰኘው የመጀመርያው ልብ ወለዱ የሚታወቅ ሲኾን፤ “ፍዳ”፣ “ሰቆቃ”፣ “ሽሽት”፣ “ቤርሙዳ ትርያንግል” እና “በሰላይ ላይ ሰላይ” የሚሉ የትርጉም ሥራዎችም አሉት። ከዚህ በተጨማሪ አራት የእንግሊዝኛ ንግግር ማስተማርያ መጻሕፍትን ለኅትመት አብቅቷል። አዲሱ “የዘመን ዱካ” የተሰኘው መጽሐፉ በ192 ገጾች የተጠናቀረ ነው።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

የበእውቀቱ ስዩም “መግባት እና መውጣት” የመጀመርያ ዕትም በሦስት ቀናት ውስጥ አለቀ

ባለፈው ሳምንት ለገበያ የቀረበው የደራሲ እና ገጣሚ በእውቀቱ ስዩም መውጣት እና መግባት የመጀመርያ ዕትም በሦስት ቀናት ውስጥ አልቆ ከገበያ ጠፍቷል። ደራሲው ለበርካታ ሳምንታት በ “አዲስ ነገር” ጋዜጣ ላይ ሲያቀርባቸው የነበሩትን ጽሑፎች አሻሽሎ እና በአዲስ መልክ ሥነ ጽሑፋዊ መልክ አስይዞ 210 ገጽ ያለው መጽሐፍ ለኅትመት አብቅቷል። በእውቀቱ ስዩም የመጽሐፉን ከገበያ መጥፋት አስመልክቶ በዚህ ሳምንት 10,000 ኮፒ [...]

ባለፈው ሳምንት ለገበያ የቀረበው የደራሲ እና ገጣሚ በእውቀቱ ስዩም መውጣት እና መግባት የመጀመርያ ዕትም በሦስት ቀናት ውስጥ አልቆ ከገበያ ጠፍቷል። ደራሲው ለበርካታ ሳምንታት በ “አዲስ ነገር” ጋዜጣ ላይ ሲያቀርባቸው የነበሩትን ጽሑፎች አሻሽሎ እና በአዲስ መልክ ሥነ ጽሑፋዊ መልክ አስይዞ 210 ገጽ ያለው መጽሐፍ ለኅትመት አብቅቷል።

በእውቀቱ ስዩም የመጽሐፉን ከገበያ መጥፋት አስመልክቶ በዚህ ሳምንት 10,000 ኮፒ ለኅትመት እንደሚበቃ ገልጿል። በሦስት ቀናት ውስጥ ያለቀው የመጀመርያው እትም 5,000 ኮፒ እንደነበርም ታውቋል። ይህን መጽሐፍ ያሳተመው አይናለም የመጻሕፍት መደብር ሲኾን በእውቀቱ ስዩም መጽሐፉን በአሁኑ ሰዓት ከኅትመት ውጭ ለኾነው የአዲስ ነገር ጋዜጣ ባልደረቦቹ በማስታወሻነት ማበርከቱ ይታወሳል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

“ግማሽ ሰው” የተሰኘ አዲስ ፊልም ሊመረቅ ነው

በኢማሆስ የፊልም ፕሮዳክሽን የተሠራው “ግማሽ ሰው” የተሰኘው አዲስ ፊልም ሰኞ ሰኔ 28 ቀን 2002 ዓ.ም ከቀኑ በ11፡00 ሰዓት በብሔራዊ ቴአትር ይመረቃል። የዚህ ፊልም ዳይሬክተር ዮናስ ብርሃነ መዋ ሲኾን ደራሲ እና ፕሮዲዩሰሩ ዳንኤል ገለታ ነው። ፊልሙን ለመሥራት ከአንድ ዓመት በላይ እንደፈጀባቸው የፕሮዳክሽን ማኔጀሩ አቶ ዐብይ . . . ገልጸዋል። 1፡45 ደቂቃ የሚፈጀው ይኸው ፊልም በሁለት ጓደኛሞች [...]

በኢማሆስ የፊልም ፕሮዳክሽን የተሠራው “ግማሽ ሰው” የተሰኘው አዲስ ፊልም ሰኞ ሰኔ 28 ቀን 2002 ዓ.ም ከቀኑ በ11፡00 ሰዓት በብሔራዊ ቴአትር ይመረቃል። የዚህ ፊልም ዳይሬክተር ዮናስ ብርሃነ መዋ ሲኾን ደራሲ እና ፕሮዲዩሰሩ ዳንኤል ገለታ ነው። ፊልሙን ለመሥራት ከአንድ ዓመት በላይ እንደፈጀባቸው የፕሮዳክሽን ማኔጀሩ አቶ ዐብይ . . . ገልጸዋል። 1፡45 ደቂቃ የሚፈጀው ይኸው ፊልም በሁለት ጓደኛሞች ቤተሰቦች ላይ የሚያተኩር የትራጄዲ ፊልም መኾኑም ታወቋል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

“ፍለጋ” ቴአትር ለእይታ በቃ

በእድሳት ምክንያት ከግንቦት 16 ቀን 2002 ዓ.ም ጀምሮ ማንኛውንም ኪነ ጥበባዊ ትዕይንት ለተመልካች ማሳየት አቋርጦ የነበረው የአዲስ አባባ ቴአትር እና ባህል አዳራሽ እሁድ ሰኔ 22 ቀን 2002 ዓ.ም በኤርምያስ ሽታ ደራሲነት እና በአልማዝ ልመንህ አዘጋጅነት “ፍለጋ” በሚል የተሠራውን ቴአትር በማሳየት ሥራውን ጀምሯል

በእድሳት ምክንያት ከግንቦት 16 ቀን 2002 ዓ.ም ጀምሮ ማንኛውንም ኪነ ጥበባዊ ትዕይንት ለተመልካች ማሳየት አቋርጦ የነበረው የአዲስ አባባ ቴአትር እና ባህል አዳራሽ እሁድ ሰኔ 22 ቀን 2002 ዓ.ም በኤርምያስ ሽታ ደራሲነት እና በአልማዝ ልመንህ አዘጋጅነት “ፍለጋ” በሚል የተሠራውን ቴአትር በማሳየት ሥራውን ጀምሯል።

ዐሥር ተዋንያን የተካፈሉበት ይኸው የትራጄዲ ቴአትር በማንነት ጥያቄ፣ በፍቅር ፍለጋ እና ዕጦት ላኢ ያተኩራል። የዚሁ ቴአትር ደራሲ ኤርምያስ ሽታ ከዚህ በፊት በራስ ቴአትር “ዙራዙር” የተባለውን ቴአትር ለሕዝብ ማቅረቡ ይታወሳል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

“ሠማያዊ ዐይን” የተሰኘው ቴአትር በ75ኛው የአገር ፍቀር ቴአትር የአልማዝ ኢዮቤልዩ ዕለት ሊቀርብ ነው

በኢትዮጵያ የመጀመርያ የኾነው የሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት 75ኛውን የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል ሊያከብር ነው። በዚሁ ክብረ በዓል ላይ “ሠማያዊ ዐይን” የተሰኘው አዲስ ሽሙጣዊ ቴአትር ለዕይታ ይበቃል::የቴአትሩ ደራሲ ተስፋዬ ከዚህ ቀደም “ጣምራ በቀል”(በብሔራዊ ቴአትር)፣ “ጥንድ መንገደኞች”እና ‘ስንብት” የተሰኙትን (በሀገር ፍቅር ቴአትር) ለዕይታ አቅርቧል።

በኢትዮጵያ የመጀመርያ የኾነው የሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት 75ኛውን የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል ሊያከብር ነው። በዚሁ ክብረ በዓል ላይ “ሠማያዊ ዐይን” የተሰኘው አዲስ ሽሙጣዊ ቴአትር ለዕይታ ይበቃል። በተስፋዬ ሽመልስ ተደርሶ በተስፉ ብርሃኔ የተዘጋጀው ይኸው ቴአትር ተስፉ ብርሃኔን፣ ባዩሽ ዓለማየሁን እና አበበ ተምትምን ከዚያው ቴአትር ቤት፤ እንዲኹም ታምሩ ብርሃኑን እና ሜሮን ጌትነትን በተጋባዥነት አሳትፏል።

የቴአትሩ ደራሲ ተስፋዬ ከዚህ ቀደም “ጣምራ በቀል”(በብሔራዊ ቴአትር)፣ “ጥንድ መንገደኞች”እና ‘ስንብት” የተሰኙትን (በሀገር ፍቅር ቴአትር) ለዕይታ አቅርቧል። አዘጋጁ ተስፉ ብርሃኔ ደግሞ “ፎርፌ” የተባለውን ሙዚቃዊ ድራማ ከተሻለ ወርቁ እና ከኪዳኔ ምስጋናው ጋራ አዘጋጅቶ በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት እንዲታይ ያደረገ ሲኾን “የቆሰሉ ምሽቶች” እና ሌሎች አምስት ያህል የሕጻናት ቴአትሮችንም አዘጋጅቷል። “ሠማያዊ ዓይን” በፍቅር እና በማሕበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ቴአትር ሲኾን  ሰኔ 27 ወይም ሰኔ 4 ቀን 2002 ዓ.ም እንዲቀርብ መታሰቡም ታውቋል።

ለዚህ ጽሑፍ አስተያየት በመስጠት የመጀመሪያ ይሁኑ!

Leave a Reply

You must be to post a comment.

Bad Behavior has blocked 1039 access attempts in the last 7 days.