"; _gaq.push(['_trackPageview']);(function() { var ga = document.createElement('script'); ga.type = 'text/javascript'; ga.async = true; ga.src = ('https:' == document.location.protocol ? 'https://ssl' : 'http://www') + '.google-analytics.com/ga.js'; var s = document.getElementsByTagName('script')[0]; s.parentNode.insertBefore(ga, s); })();

Posts by Tsegaye ZeOromay

“ኤርትራን ያስገነጠልነው ኢትዮጵያን ከመበታተን ለማዳን ነው” የአቶ መለስ አዲስ ግኝት

አቶ መለስ በትጥቅ ትግሉ ወቅት ህወሓት ከሻዕቢያ ጋር ለምን እንደወገነ ሲመልሱ “ኢትዮጵያን ከመበታተን ለማዳን ነው” ብለውናል፡፡ ይህ መቼም በጣም የሚያስገርም ግኝት ሳይሆን አልቀረም፡፡ አቶ መለስ አሳምረው እንደሚያውቁት፣ አቦይ ስብሐትም በቅርቡ ሲናገሩ እንደተደመጡት፣ ህወሓት የኤርትራ ጥያቄ “የቅኝ ግዛት ጥያቄ” መሆኑን ተቀብሎ ለኤርትራ ነጻነት ሲታገል የነበረ ድርጅት ነው፡፡ እንዲያውም የኤርትራን ነጻነት ከራሱ ከሻዕቢያ ሳይቀር የታደገ መሆኑን አቦይ ስብሐት በግልጽ አረጋግጠዋል፡፡ ይህ ዓላማ ኢትዮጵያን ከመበታተን ከማዳን ጋር አንዳችም ግንኙነት የለውም፡፡ ሲጀመር ስሙ እንደሚያመለክተው ህወሓት ትግራይን /እና ኤርትራን/ ነጻ ለማውጣት የተቋቋመ ድርጅት እንጂ የኢትዮጵያ አንድነት ጉዳይ ጉዳዩ የነበረ/የሆነ ድርጅት አልነበረም፡፡ ስለሆነም ህወሓት ትብብሩን የሚያራምደው “የትግራይን ሕዝብ” መብት ከማስጠበቅ አንጻር እንጂ የኢትዮጵያ አንድነት አስጨንቆት አልነበረም፡፡ …ሙሉውን ለማነበብ የድረ ገጹን የአማርኛ ክፍል ይጎብኙ።

Read more

ኢህአዴግና ዲያሌክቲክስ

የአብዮታዊ ዲሞክራሲ መሠረት አንድ እግር መሠረት ማርክሲዝም ነው፡፡ የማርክሲስቶች ፍልስፍና የሆነው ዲያሌክቲካል ማቴሪያሊዝም ደግሞ ሕይወት የተቃርኖ መገለጫ ናት ይላል፡፡ እና ምናልባት ኢሕአዴግ ሆን ብሎ በዲያሌክቲክስ ሕጎች በመመራት ለመገመት የሚያስቸግሩና እርስ በርስ የሚቃረኑ ነገሮችን እያደረገ ቢሆንስ? ሙሉውን ጽሑፍ ለማንበብ ወደ አማርኛው ክፍል ይሂዱ ወይም እዚህ ይጫኑ።

Read more

Bad Behavior has blocked 779 access attempts in the last 7 days.